Get Mystery Box with random crypto!

AHADU RADIO FM 94.3

የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3 A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3
የሰርጥ አድራሻ: @ahaduradio
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.04K
የሰርጥ መግለጫ

አሐዱ ራድዮ 94.3
Your source for top local and international news and analysis.
"Voice of Ethiopian"
የአሐዱ የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ በመሆን ወቅታዊና እውነተኛ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2023-02-28 16:55:56 ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ተፈናቅለው የሚመጡ ዜጎችን መቀበል ከክልሉ አቅም በላይ እንደሆነ ተገለጸ፡፡
ከጊዜ ወደ ጊዜ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እየተፈናቀሉ ወደ ክልሉ የሚመጡ ዜጎች ቁጥር መናሩን በማስታወስ ከሰሞኑም በአዲስ አበባ ከተማ ዙሪያ እየተደረገ የሚገኘውን የቤት ማፍረስ ሂደት ተከትሎ በርካታ ዜጎች ወደ ክልሉ እየገቡ መሆኑን የገለጹት የአማራ ክልል የአደጋ ስጋት ስራ አመራራ ኮምሽን ቅድመ ማስጠንቀቂያ እና ምላሽ ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ዘውዱ ገልጸዋል፡፡
የተፈናቃይ ዜጎች ቁጥር በማሻቀቡ የመጠለያ ጣቢያዎች ከሚችሉት አቅም በላይ ዜጎችን መያዛቸውን እና በምግብና የተለያዩ ቁሳቁሶች ለተፈናቃዩ በማድረስ ረገድም ከተፈናቃይ ዜጎች ቁጥር አንጻር ክልሉ ከአቅም በላይ እንደሆነበት ለአሃዱ ተናግረዋል፡፡
በክልሉ ለአደጋ ጊዜ ተብለው የተቀመጡ አስፈላጊ የምግብ ክምችቶች የነበሩ ቢሆንም ያንን ሙሉ ለሙሉ አሟጦ ከመጠቀም ባለፈ በማህበረሰቡ ድጋፍ እና ርብር እንዲሁም የእርዳታ ድርጅቶችን በማስተበበር እስከ ዛሬ የተቻለውን ሁሉ ሲደረግ እንደ ነበር የገለጹት አቶ ብርሃኑ አሁን ባለው ነባራዊ እውነታ ግን ያንን ለማድረግ የሚያስችል አቅም ባለመኖሩ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ እንደተቸገሩም አስታዉቀዋል፡፡
በተለይ ከኦሮምያ ክልል እየተፈናቀሉ ወደ አማራ ክልል የሚሄዱ ዜጎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሻቀበ መምጣቱ በተደጋጋሚ የሚነሳ ጉዳይ ቢሆንም በፌደራል መንግስቱ በኩል ግን ትኩረት ሲሰጠው አይስተዋልም፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
1.4K views13:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-28 16:47:48
ከቤት ማፍረስ ጋር በተያያዘ ያጋጠሙ የሰብዓዊ መብት ቀውሶች ምንድናቸው የሚለው ጉዳይ ላይ ምርመራ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮምሽን አስታወቀ፡፡
በአዲስ አበባ እና ዙሪያዋ ህገ ወጥ ናቸው በሚል ቤት የሚፈርስባቸው ዜጎች እየተንገላቱ እና ወደ ሌሎች ቦታዎች እየተሰደዱ ሲሆን ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ተፈናቅለው የስነ ልቦና ጫና እየደረሰባቸውም ይገኛል፡፡
አሀዱም ስለ ጉዳዩ የጠየቃቸው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮምሽን የኢኮኖሚ እና ማህበራዊ መብቶች የስራ ክፍል ዳይሬክተር ዶክተር ብራይትማን ገብረሚካኤል አዲስ አበባ እና ዙሪያዋ የፈረሱ ቤቶችን በተመለከተ ህጋዊ ናቸው ወይም አይደሉም የሚለውን ለማጣራት ኮምሽኑ ምርመራ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ከቤት ማፍረስ ጋር በተያያዘ የጉዳዩን አሳሳቢነት መገንዘብ ችለናል ያሉት ዶክተር ብራይትማን እየተደረገ ባለዉ ምርመራ ዜጎች መኖሪያ ቤትን ከማግኘት አንጻር መብታቸው ተጥሷል ወይስ አልተጣሰም የሚለውን እና ቅድመ ማስጠንቃቂያ ከመስጠት አንጻርስ ምን እርምጃ ተወስዷል የሚለውን እንደሚካተትም አንስተዋል፡፡
በአጠቃላይ ቤት የማፍረስ ዘመቻዉ ምን አይነት የሰብዓዊ መብት ቀውሶችን አስከትሏል የሚለው ጉዳይ በብዙ ዘርፉ ምረመራ እየተደረገበት እንደሆነ አንስተዉ ሳይጠናቀቅ ግን በዚህ ጉዳይ መደምደሚያ መስጠት አይቻልም ነው ያሉት፡፡
አሁን ላይ መረጃ የመሰብሰብ ስራ እየተሰራ ሲሆን በዚህ ጉዳይ ምረመራው ሲጠናቀቅ ለሚመለከተው አካል ምክረ ሃሳብ ኮምሽኑ እንደሚሰጥም ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ በመሆን ኮምሽኑ ክትትልና ምርመራ እያደረገ ነዉ ያሉት ዳይሬክተሩ ከኮሚሽኑ መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ ማህበረሰቡ በትዕግስት እንዲጠብቅም አሳስበዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር
1.8K views13:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-24 14:48:19 ቀድሞ ከነበረው 206 ጽህፈት ቤቱ ዉስጥ አሁን ላይ 4 ብቻ እንደቀሩ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ ) አስታወቀ፡፡
የሸኔ ቡድን ዘርፈ ብዙ ጉዳት እያደረሰ ስለመሆኑ በመንግስት አካላት ቢነገርም በንጹሃን ዜጎች ላይ ግን ጥቃት የምፈጽመው እኔ አይደለሁም በማለት ሲያስተባብል ይስተዋላል፡፡
ይሄን በተመለከተ እውነታው ምንድነው የማጣራት ስራስ ተሰርቷል ወይ የሚል ጥያቄ በትላንትናው እለት በአሃዱ መድረክ ላይ ለተገኙት ኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጥርነህ ገምታ ተነስቶላቸዋል፡፡ በምላሻቸውም እኛም እንደሌላው ሰው በወሬ ደረጃ የምንሰማው እንጂ እርግጠኛ ሆነን በዚህ ጉዳይ ላይ ምላሽ መስጠት የሚያስችል ማረጋገጫ የለንም ነዉ ያሉት፡፡
ጉዳዩን አለም አቀፍም ሆነ ሀገር አቀፍ ገለልተኛ ቡድን ሊያጣራው እንደሚገባ የተናገሩት አቶ ጥሩነህ ሰላም ፤ዲሞክራሲ በሌለበት የፖለቲካ ምህዳሩ ጠባብ በሆነበት ሀገር ላይ አምጸው የትጥቅ ትግል የሚያደርጉም እንዳሉ እና በኢትዮጵያ የተጀመረ እንዳልሆነም አንስተዋል፡፡
የፖለቲካ ምህዳሩ መጥበብ አስቸጋሪ ወይም እንቅፋት ከሆነባቸው ፓርቲዎች በካከል አንዱ የኦሮሚያ ፌደራልሲት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ነው ያሉት ዋና ጸሀፊው ፓርቲው ቀድሞ ከነበረው 206 ጽህፈት ቤቱ አሁን ላይ 4 ብቻ እንደቀሩት ተናግረዋል፡፡
ከ206 ጽህፈት ቤቱ 4 ብቻ መቅረቱ የሚያሳየው የፖለቲካ ምህዳሩ መጥበብን እንደሆነ አንስተው ጽህፈት ቤቶቹ በመንግስት አካላት ተሰብረው የተዘረፉ ሲሆኑ ቀሪዎቹ ደግሞ ፓርቲው እየደረሰበት ካለው ተጽኖ አንጸር የተዘጉ ናቸው ብለዋል፡፡
ሀገሪቱ እስካሁን ድረስ ከግጭት እና ጦርነት አልወጣችም ያሉት ዋና ጸሃፊዉ ሰላምን ለማምጣት የሚደረገውን ስምምነት ፓርቲው እንደሚደግፈዉም ጠቁመዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_2
2.6K views11:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-24 14:42:01
በቦረና ዞን የተከሰተውን ድርቅ ተከትሎ በቀንድ ከብቶች ሞት ምክንያት 33 ቢሊየን የሚገመት ብር ዞኑ ማጣቱ ተገለጸ፡፡
በድርቁ ምክንያት በዞኑ ከ3 ሚሊየን በላይ እንስሳት እንደሞቱ እና ከዚህ ውስጥ 85 በመቶዎቹ የቀንድ ከብቶች መሆናቸው የገለጹት የቦረና ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አብዱል ሰላም ዋሪዮ የቀሩትን 230ሺ የቀንድ ከብቶች ለመታደግ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን በማስታወስ ለ3 ወር የቀንድ ከብቶቹን ለመታደግ ቢያንስ 4 ነጥብ 4 ሚሊየን እስር ሳር ማቅረብ እንደሚያስፈልግ ለአሃዱ ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪም 135ሺ ኩንታል መኖ የሚያስፈልግ ቢሆንም ማቅረብ የተቻለው ግን አንድ በመቶ ብቻ መሆኑን ተከትሎ ከፍተኛ የሆነ የመኖ እጥረት እንደገጠማቸውም የዞኑ ምክትል አስተዳደሪ አክለው ገልጸዋል።
በዞኑ የተከሰተውን ድርቅ ተከትሎ እየተደረገ ያለው ድጋፍ በቂ ባለመሆኑ የታሰበውን ያህል ችግር ውስጥ የሚገኙ ከብቶችን መታደግ ከባድ ሊሆን እንደሚችል የተናገሩት ምክትል አስተዳዳሪው አሁንም ቢሆን ያለውን ችግር ከግምት ውስጥ በስገባ መልኩ አፋጣኝ ድጋፍ ሊደረግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
በአካባቢው የተከሰተውን ድርቅ ተከትሎ እስካሁን ድረስ ዞኑ በቀንድ ከብቶች ሞት ምክንያት 33 ቢሊየን የሚገመት ብር ማጣቱ ተነግሯል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
2.5K views11:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-24 14:38:38 በኮንስትራክሽን ዘርፉ ላይ የሚገኙ አካላትን የአሰራር ሂደት በሚገባ መከታተል እና ቅጣት መጣል የሚያስችል አዲስ መመሪያ ተዘጋጅቶ ስራ ላይ መዋሉ ተገለጸ፡፡
እስካሁን ድረስ በስራ ላይ የነበረው የኮንስትራክሽን የቅጣት እና የክትትል መመሪያ የደህንነት ቅድመ ሁኔታዎችን ማሟላት የማይችል እንደሆነ እና በዚህም ምክንያት ኮንስትራክሽን ዘርፉ ላይ የሚፈጸሙ የህግ ጥሰቶችን ተከትሎ የሚጣለዉ ቅጣት አነስተኛ እንዲሆን አድርጎትም ነበር ፡፡
በቅጣት አወሳሰንና አተገባበር ላይ የነበሩ ክፍተቶችን ለማስተካከል የቅጣት መመሪያው እንደ አዲስ መሻሻሉን በግንባታ ፍቃድ እና ቁጥጥር ባለስልጣን የግንባታ ክትትልና ቁጥጥር ዳይሬክተር ኢንጂነር ከማል ጀማል ተናግረዋል፡፡
በስራ ላይ የነበረው መመሪያ በባለስልጣኑ ህግ መሰረት መስራት በማይችሉት ላይ አነስተኛ ቅጣት ሲጥል የነበረ እንደሆና በዚህም ምክንያት ተቋራጮችና አሰሪዎች ከህግ ውጪ እንዲሆኑ አድርጎ መቆየቱን አንስተዋል፡፡
አሁን ላይ እንደ አዲስ የተሻሻለዉ መመሪያ ከዚህ ቀደም ተግባራዊ ሲሆን የነበረውን ሂደት በመቀየር የክትትል እና የግምገማ ሂደቱ ይበልጥ ግልጽ የማድረግ አቅም አለው ብለዋል ዳሬክተሩ፡፡
ነባሩ መመሪያ አልሚውን ብቻ የሚቀጣ ሲሆን ይሄኛው መመሪያ አልሚውም፣ ኮንትራክተሩን እና አማካሪውን የጋር ተጠያቂነትን የሚጥልባቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ከዚህ ቀደም ሲተገበር የነበረው መመሪያ አነስተኛ የገንዘብ ቅጣት የሚጥል ሆኖ በመገኘቱና ህገወጥ ድርጊቶች በመበራከታቸዉ መመሪያ ቁጥር 3/2015 በሚል እንደ አዲስ መሻሻሉን ጠቅሰዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.1K views11:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-24 14:35:15
ከዚህ አመት ጀምሮ የአድዋ ድል በአል አከባበር ስነ ስርአት በመከላከያ ሚንስቴር መሪነት እንደሚከበር ተገለጸ፡፡
በየአመቱ የካቲት 23 ቀን በታላቅ ድምቀት የሚከበረው የአድዋ ድል በአል አከባበር ስነ ስርአት ከዚህ ቀደም በባህል እና ቱሪዝም ሚንስቴር ከዚያም በባህል እና ስፖርት ሚንስቴር በኩል ይመራ እንደነበረ ይታወቃል፡፡ ከዘንድሮው አመት ጀምሮ ግን የአድዋ ድል በአል ሙሉ በሙሉ በመከላከያ ሚንስቴር አስተባባሪነት እንደሚከበር የባህል እና ስፖርት ሚንስቴር የህዝብ ግንኙነት እና የኮሚኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሀይማኖት አለማየሁ ለአሁዱ ተናግረዋል፡፤
ባህል እና ስፖርት ሚንስቴርም የመከላከያ ሚንስቴር በሚያወጣው የአከባበር መመሪያ መሰረት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸው በእለቱም በዳግማይ ሚኒሊክ አደባባይ እና በአድዋ ድልድይ አካባቢ ከሚኖረው የአበባ ጉንጉን የማስቀመጥ እና የመታሰቢያ ዝግጅቶች በተጨማሪም በመስቀል አደባባይ ትልቅ ዝግጅት እንደሚኖር ጠቁመዋል፡፡
አክለውም በመስቀል አደባባይ በሚኖረው አከባበር ላይ ከሚጠበቁት መሰናዶዎች መካከል በአሉን የሚያስታውሱ ቁሳቁሶች የሚታዩበት ኤግዚሸን እና የኪነጥበብ ዝግጅቶች እንደሚገኙበትም ገልጸዋል፡፡
በዓሉ በመላው ኢትዮጵያ በታላቅ ድምቀት ለማክበር በቂ ዝግጅት ተደርጓል ተብሏል፡፡ እስካሁን በትግራይ ክልል አድዋ ተራራ ላይ ስለሚደረገዉ የበዓሉ አከባበር የተባለ ነገር የለም፡፡ ባለፉት ሁለት አመታት በሰሜኑ ክፍል ጦርነት ምክንያት ጉዞ አድዋ እና በአድዋ ተራራ ስር የሚከበረዉ አመታዉ በዓል ሳይከናወን መቅረቱ የሚታወስ ነዉ፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
2.4K views11:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 14:42:14
በብራዚል ጎርፍና የመሬት መንሸራተት 36 ሰዎችን መግደሉ ተሰምቷል፡፡
በብራዚል በሳኦፖውሎ ግዛት የጣለው ከባድ ዝናብ ያስከተለው የጎርፍና የመሬት መንሸራተት አደጋ ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ የ36 ሰዎችን ህይወት መቅጠፉ ነው የተገለጸው፡፡
የብራዚል ቴሌቪዥንና የማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን እንዳሳዩት ሴባስቲያኖ ከተማና አጎራባች አካባቢዎች በውሃ ተጥለቅልቀዋል በርካታ ተሸከርካሪዎች በከባድ ነፋስ እየተሰበሩ በሚወደቁ ዛፎች እንዳይሆኑ ሆነው መወደማቸው ተነግሯል፡፡
የሴባስቲያኖ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ በሰጡት ማብራሪያ ከተማዋ ክፉኛ መጎዳቷን ገልጸዉ በርካታ ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል ተፈናቅለዋለ ነው ያሉት፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.6K views11:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 14:39:20
የዓለማቀፉ ድንበር የለሽ የሀኪሞች ቡድን በቡርኪናፋሶ አገልግሎቱን ማቆሙን አስታውቋል፡፡
በአሸባሪዎችና በታጣቂ ሀይሎች የንጹሃን ሰዎች ህይወት በየጊዜው የሚቀጥፉበት የምዕራብ አፍሪካ ቀጣናዋ ሀገር ቡርኪናፋሶ በበጎ ፈቃደኞች የሚሰጣትን አገልግሎት ማጣቷ ነው የተገለፀው፡፡
በተለይም ደግሞ ሁለት የድንበር የለሹ የሀኪሞች ቡድን ሀኪሞች በአሸባሪዎቹ ታጣቂ ሀይሎች በጭካኔ መገደላቸውን ተከትሎ የዓለማቀፉ የድንበር የለሹ የሀኪሞች ቡድን በቡርኪናፋሶ ሲሰጥ የነበረውን አገልግሎት ማቋረጡን ነው የገለፀው፡፡
በዚህ በተያዘው ወር ታጣቂዎቹ ሀኪሞቹን አሳፍራ ስትጓዝ በነበረችው ተሸከርካሪ ላይ ተኩስ ከፍተው ሁለቱን መግደላቸውን የዘገበው ፎክስ ኒውስ ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.4K views11:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 14:34:21
በ1 ሺህ 662 መጠለያዎች ውስጥ የሚገኙ ወደ 1 ነጥብ 3 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች ወደ ቀያቸው ሊመለሱ እንደሚችሉ ተመላከተ፡፡
ይህንን ግምት ያስቀመጠዉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስደተኞች ኮሚሽን በኢትዮጵያ ነዉ፡፡ ባስቀመተዉ ትንበያም 1 ነጥበን 3 ሚሊየን ዜጎች ወደ ቀድሞ ቀያቸዉ ሊመለሱ እንደሚችሉ ገልጻል፡፡
በኢትዮጲያ ከ2 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የተፈናቀሉ ሲሆን በዚህም በ2 ሺህ 120 መጠለያዎች ውስጥ ወደ 2 ነጥብ 72 ሚሊዮን የሚጠጉ ተፈናቃይ ዜጎች መኖራቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ኮሚሽን በኢትዮጲያ ለአሃዱ በላከው መግለጫ አስታዉቋል፡፡
በተለያዩ የሃገሪቱ አካባቢዎች የድርቅ ፣ የግጭት እንዲሁም የምግብ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መናር ለተፈናቃዮች ቁጥር መጨመር በምክንያትነት ያስቀመጠ ሲሆን ይህም በተለያዩ የሃገሪቱ አካባቢዎች የችግሩ ገፈት ቀማሽ የሆኑ ዜጎች ለከፋ ሰብአዊ ቀውስ መዳረጋቸውን የገለጸው፡፡
ከሰሜኑ የሃገሪቱ ክፍል ባሻገር በኦሮምያ ፣ ሶማሌና ደቡብ ክልል አካባቢዎች ችግሩ በከፋ ሁኔታ መስተዋሉን የጠቆመው ተቋሙ በተለይም ግጭት ባሉባቸው የእነዚህ ክልል አካባቢዎች ሳይፈናቀሉ በአካባቢው ያሉ ነዋሪዎችንም ችግር ላይ መጣሉን አመልክቷል፡፡
በተለይም በኦሮምያና ደቡብ ክልል አካባቢዎች ችግሩ አሁንም መቀጠሉን ገልጾ በዚህ ሂደት ውስጥ ሴቶችና ህጻናት ዋነኛ የችግሩ ገፈት ቀማሽ መሆናቸው ሁኔታውን አሳሳቢ እንዳደረገውም ገልጻል፡፡
በሃገሪቱ የተጀመሩትን የሰላም ጥረቶች ተከትሎ በቀጣይ በ1 ሺህ 662 መጠለያዎች ውስጥ የሚገኙ ወደ 1.3 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች ወደ ቀያቸው ሊመለሱ እንደሚችሉም ግምቱን አስቀምጧል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
2.0K views11:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 14:31:53
መንግስት ሉአላዊነትን የሚጻረሩ ችግሮችን ችላ ማለቱ ተገቢ አይደለም ሲሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ፡፡
በተለያዩ የሃገሪቱ አካባቢዎች በተለይም ደግሞ በጋምቤላ ፣ ቤንሻንጉልና ደቡብ ምእራብ ክልሎች የሱዳንና ደቡብ ሱዳን ታጣቂ ሃይሎች በተደጋጋሚ ጥቃት ሲፈጽሙ የሚስተዋል ቢሆንም መንግስት ግን በሚፈለገው መጠን ትኩረት እየሰጠው አይደለም ሲሉ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ገልጸዋል፡፡
አሃዱ ያነጋገራቸው የእናት ፓርቲ ዋና ጸሃፊ አቶ ጌትነት ወርቁ የኢትዮጲያ ሉአላዊነት ጉዳይ ለድርድር እንደማይቀርብ በማንሳት መንግስት ግን ተገቢውን ትኩረት አለመስጠት ብቻም ሳይሆን በጆሮ ዳባ ልበስ የተወው ጉዳይ ሆኗል ሲሉ ወቅሰዋል፡፡
ሌላኛው አሃዱ ያነጋገራቸው የኢትዮጲያ ብሄራዊ ፓርቲ ሊቀ-መንበር አቶ ዘሪሁን ገብረእግዚያብሄርም የአቶ ጌትነትን ሃሳብ በመጋራት ዜጎች በየጊዜው በሚፈጸምባቸው ጥቃት ሳቢያ ለሞትና ለአካል ጉዳት እንዲሁም ለንብረት ውድመት እየተጋለጡ ቢሆንም በስልጣን ላይ ያለው መንግስት ግን በተለይ ከላይ በተጠቀሱት አካባቢዎች የተወረሩ መሬቶችንም ሆነ ዜጎች ላይ እየደረሱ ያሉ ችግሮችን ሊያስቆም አልቻለም ሲሉ ተናግረዋል፡፡
የሱዳን እንዲሁም የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች ቀደም ሲል በተገለጹት የሃገሪቱ አካባቢዎች ሰርጎ በመግባት ተደጋጋሚ ጥቃት የሚፈጽሙ ሲሆን በዚህም ዜጎች ከአካል ጉዳትና ንብረት ውድመት ባለፈ ለሞት የሚጋለጡበት ሁኔታም ሰፊ ስለመሆኑ በተደጋጋሚ ይገለጻል፡፡
አሃዱ ጉዳዩን አስመልክቶ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴርን ለማነጋገር ተደጋጋሚ ጥረት ቢያደርግም ለጊዜዉ አልተሳካም፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
1.8K views11:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ