Get Mystery Box with random crypto!

AHADU RADIO FM 94.3

የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3 A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3
የሰርጥ አድራሻ: @ahaduradio
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.04K
የሰርጥ መግለጫ

አሐዱ ራድዮ 94.3
Your source for top local and international news and analysis.
"Voice of Ethiopian"
የአሐዱ የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ በመሆን ወቅታዊና እውነተኛ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2023-02-21 14:29:56
የምርጫ ህግ ጥሰቶች እንደነበሩ በምርጫ ታዛቢዎች ሪፖርት በመቅረቡ ውጤት የማረጋገጥ ስራን በታቀደበት ጊዜ ለማጠናቀቅ እንዳልተቻለ ተገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች ማለትም በኮንሶ፣ በደቡብ ኦሞ፣ በወላይታ፣ በጋሞ፣ በጌዴኦ፣ በጎፋ እና በአምስት ልዩ ወረዳዎች በቡርጂ፣ በባስኬቶ፣ በአሌ፣ በአማሮ፣ በደራሼ ላይ የህዝበ ዉሳኔ ማካሄዱ ይታወቃል፡፡

ያካሄደውን የሕዝበ ውሣኔ ጊዜያዊ ውጤት የማዳመር ሥራ በሁሉም ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ላይ አጠናቆ በዞንና በልዩ ወረዳ ደረጃ ጊዜያዊ ውጤቶች ይፋ ማድረጉን በማስታወስ ቦርዱ የመጨረሻውን ውጤት የማጣራትና የማረጋገጥ ሥራ ከየካቲት 6 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ አርባ ምንጭ ከተማ በሚገኘው የሕዝበ ውሣኔው ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት እየሰራ እንደሚገኝ ከቦርዱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ሆኖም ግን ቀደም ሲል ቦርዱ የመጨረሻውን በቦርድ የተረጋገጠ ውጤት የካቲት 8 ቀን 2015 ዓ.ም ይፋ እንደሚያደርግ የገለፀ ቢሆንም በርከት ያሉ ግድፈቶችና የምርጫ ህግ ጥሰቶች በቦርዱ የምርጫ ክትትል ቡድን እንዲሁም በምርጫ ታዛቢዎች ሪፖርት በመቅረቡ የማጣራት እና ውጤት የማረጋገጥ ስራን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ አልተቻለም፡፡

በዚህም የውጤት ማጣራትና ማረጋገጥ ስራ የደራሼ፣ አሌ፣ ደቡብ ኦሞ፣ባስኬቶ፣ ኮንሶ እና ቡርጂ ውጤቶችን የማጣራትና የማረጋገጥ ስራ ተጠናቆ ውጤታቸው በቦርዱ የጸደቀ ሲሆን በቀጣይም በቀሪዎቹ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ማለትም በአማሮ፣ በወላይታ፣ በጋሞ፣ በጌዴኦ እና የጎፋ ጊዜያዊ ውጤቶች የማጣራትና የማረጋገጥ ሂደት እንደተጠናቀቀ ቦርዱ ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አሀዱ ከምርጫ ቦርድ ባገኘው መረጃ ማረጋገጥ ችሏል፡፡
2.2K views11:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-17 17:14:41

1.1K views14:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-17 15:02:22
የተጀመረው የክስ ሂደት እንደማይቋረጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የህግ እና ችሎት ጉዳዮች ጊዚያዊ ኮሚቴ ገለጸ፡፡
የቤተ ክርስቲያኗን ቀኖና ጥሰው በህገ ወጥ መንገድ ሲኖዶስ የመሰረቱትን አካላት ተከትሎ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የበርካታ ምዕመናን ህይወት ማለፉን እና እንዲሁም ቤተ ክርስቲያኖች ተሰብረው መዘረፋቸው የሚታወቅ ነዉ፡፡
ይህንኑ ተከትሎ የተፈጸሙትን ወንጀሎች በህግ አግባብ ለመዳኘት ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ስራ ከገባ ሞቆየቱን የገለጹት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የህግ እና ችሎት ጉዳዮች ጊዚያዊ ኮሚቴ አባል ጠበቃ እና የህግ አማካሪ አቶ አያሌው ቢታኔ ምንም እንኳን አሁን ላይ ችግሮቹን ለመፍታት ስምምነቶች ላይ ቢደረስም የተፈጸሙት አስተዳደራዊ ወንጀሎችን ተከትሎ ክሱ እንደሚቀጥል እና በዛ ላይ ምንም አይነት ለውጥ እንደሌለ ለአሃዱ ተናግረዋል፡፡
የቤተ ክርስቲያኒቷን ስርአት በጠበቀ መልኩ ስምምነት ቢደረግም ህጋዊ ምላሽ ማግኘት ያለባቸው ጉዳዮች በህግ አግባብ ምላሽ ማግኘት እንዳለባቸው ያስታወሱት አቶ አያሌው የክስ ሂደቱም በዚህው አግባብ መሰረት እንደሚቀጥል አክለው ገልጸዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_2
1.9K views12:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-17 14:45:31
የከተማ አውቶቢሶቹ ግዢ የሃገሪቱን ምጣኔ-ሃብታዊ እውነታ ያላገናዘበ ነው ሲሉ የምጣኔ ሃብት ባለሞያዎች ገለጹ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት ባሳለፍነው ከቀናት በፊት ከ3 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው እጅግ ዘመናዊ የተባሉ 100 የከተማ አውቶቢሶችን ወደ ስራ ያስገባ ሲሆን ይህም በመዲናዋ በየጊዜው እየጨመረ ያለውን የህዝብ ብዛት ተከትሎ ማህበራዊ እንቅስቃሴን ለማሳለጥ በማለም መከናወኑን መግለጹ ይታወሳል፡፡ የአዉቶቢሶቹ መገዛት ለሚታየዉ የትራንስፖርት እጥረት አጋዥ መሆኑ የሚታመን ቢሆንም ለግዢ ወጣ የተባለዉ የብር መጠን አንዱ በ19 ሚሊየን ብር መሆኑ ብዙዎችን እያነጋገረ ነዉ፡፡
አሃዱ ያነጋገራቸው የምጣኔ ሃብት ባለሞያው አቶ ያሬድ ሃይለመስቀል ግዢው ሃገሪቱ አሁን ያለችበትን ምጣኔ ሃብታዊ እውነታ ያላገናዘበ በመሆኑ የውጪ ምንዛሬ እጥረቱን ይበልጥ ያባብሰዋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ማንኛውም ግዢ ሲፈጸም የራሱ ህግና ወቅታዊ የምጣኔ ሃብት ግምገማ የሚደረግ ቢሆንም ይህ ግዢ ግን እጅግ የተጋነነ ሆኖ ተገኝቷል ሲል ሙያዊ አተያያቸዉን አብራርተዋል፡፡
ሌላኛው አሃዱ ያነጋገራቸው የምጣኔ ሃብት ባለሙያ አቶ ፋሲል ጣሰው በበኩላቸው የአቶ ያሬድን ሃሳብ በመጋራት መሰል የህዝብ መገልገያዎች ግዢ ሲፈጸም አዎንታዊ ጎን ቢኖረውም የሃገሪቱን ሁኔታና ግዢው ከተፈጸመ በኋላ ሊኖሩ የሚችሉ የጥገናና መሰል ተያያዥ ወጪዎችን ባገናዘበ መልኩ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር በመዲናዋ የሚስተዋለውን የትራንስፖርት ችግር ለማቃለል ይቻል ዘንድ 100 የከተማ አውቶቢሶችን ግዢ ከሃገር ውስጥ አቅራቢዎች የፈጸመ ሲሆን አሃዱም ይህንን በተመለከተ የከተማ አስተዳደሩን ለማነጋገር ተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርግም ለጊዜዉ ሳይሳካ ቀርቷል፡፡
1.8K views11:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-17 14:40:52 የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የልዩ ፍላጎት አካቶ ትምህርት ክፍል ሀላፊ ዶክተር አለመየሁ ተክለ ማሪያም በትናንትናው እለት በአሀዱ መድረክ ጋር በነበራቸው ቆይታ የመምህራንን ትምህርት እና ስልጠና ያልቀየረ ሀገር የህዝብን ህይወት መቀየር አችልም ብለዋል፡፡
ለትምህርት እድገት ጥራት እና ለውጥ ቁልፍ ነገሩ መምህራን ላይ መስራት ነው ያሉት ዶክተር አለማየሁ በሌሎች አለም ሀገራት ከፍተኛ ውጤት ያላቸው ግለሰቦች የመምህርነት የስራ ዘርፍ ላይ እንደሚሰማሩም አንስተዋል፡፡
በምንም መልኩ የመምህራንን ህይወት የመቀየር ስራ መስራት እንደሚስፈልግና በሌሎች ሀገሮች መምህር ለመሆን የሚገኘው እድል ጠባብ እንደሆነም ያለዉን ተሞክሮ አብራርተዋል፡፡
የስነ ምግባር ትምህርቶችን ማስተማር ተማሪዎች በራሳቸው ቋንቋ ትምህርትን እንዲረዱ ማድረግ ኩረጃን ማስቀረት እንዲሁም ለትምህርት አስፈላጊ ቁሳቁሶችን ማሟላት እንደሚያስፍልግም
ሌላኛው በመድረኩ የተገኙት የትምህርት ባለሙያው ዶክተር መክብብ ጣሰው በትምህርት ዘርፉ ላይ ጠንካራ አመራር እንዲኖር ማድረግ ያስፍለጋል ብለዋል፡፡ በሌሎች አለም ሀገራት የግል ዘርፉ ለትምህርት እድገት የሚያደርጉት አስተዋጾ ከፍተኛ በመሆኑ እነሱን ከማሳደድ ይልቅ መደገፍ እንደሚገባ አመላክተዋል፡፡
የትምህርት ስርዓቱን መፈተሸ ተማሪዎች ያኙትን ውጤት የአከባቢው ማህበረሰብ እንዲሁም ወላጅ እንዲያውቀው ማድረግ ያስፈልጋልም ሲሉ አንስተዋል፡፡
በትምህርት ዘረፉ ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ፤ አስተዳደሩን ወይም አመራሩን መፈተሸ የመምህራን አቅምን ማሳደግ ፤ወላጆችን ማሳተፍ ፤ከፖለቲካ ጣልቃ ገብነት እንዳይኖረው ማድረግ እና ሌሎችንም በጥናት በመለየት መስራት እንደሚያስፍልግ ምሁራኑ ጠቁመዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
1.8K views11:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-16 14:45:06
በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ከተማ ወረዳ 6 በመኖሪያ ቤቶች ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ 9 መኖሪያ ቤቶች ላይ ጉዳት መድረሱ ተገለፀ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ከተማ ወረዳ 6 ልዩ ቦታዉ 31 ቀበሌ እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ በመኖሪያ ቤቶች ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ 9 መኖሪያ ቤቶች ላይ ጉዳት መድረሱን የአዲስ አበባ ከተማ እሳት እና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
አደጋዉ ከረፋዱ 4 ሰዓት ላይ የደረሰ ሲሆን የእሳት አደጋዉ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ማዋሉ መቻሉን ገልጸዉ በእሳት አደጋዉ በሰዉ ህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት የለም ብለዋል።
የእሳት አደጋዉን ለመቆጣጠር 5 የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪና የአደጋ ጊዜ መቆጣጠር ባለሙያዎች የተሰማሩ ሲሆን የእሳት አደጋዉ ተስፋፍቶ የከፋ ጉዳት ሳይደርስ በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታዉቀዋል።
በአደጋዉ ምክንያት በንብረት ላይ የደረሰዉ የዉድመት መጠን እና የአደጋዉ መንስኤ እየተጣራ መሆኑን አቶ ንጋቱ አክለዉ ተናግረዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
3.2K views11:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-16 14:43:06
በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ተፈጥሮ በነበረው ጦርነት ምክንያት ተጠፋፍተው የነበሩ ቤተሰቦችን ማገናኘት መቻሉን የኢትዮጵያ ቀይመስቀል ማህበር አስታወቀ፡፡
የኢትዮጵያ ቀይመስቀል ማህበር ከአለማቀፉ ቀይመስቀል ማህበር ጋር በመተባበር በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን ከቤተሰቦቻቸው ጋር ማገናኘቱን የኢትዮጵያ ቀይመስቀል ማህበር የሰብአዊ ዲፕሎማሲና ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት ኃላፊ አቶ መስፍን ደረጀ ተናግረዋል፡፡
በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በነበረው ጦርነት አማካኝነት በርካታ ዜጎች በማሀል ሀገር እና በዛም በሰሜኑ ክፍል ከነበሩት ቤተሰቦቻቸው ጋር ተጠፋፍተው እንደነበር በማስታወስ በአሁኑ ወቅት እነዚህን ዜጎች መልሶ ማገናኘት መቻሉን ነው የገለጹት፡፡
ዜጎችን የማገናኘት ስራው መቀጠሉን እና ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠር ከማስቻል አኳያም ከሚመለከታቸው ጋር በመተባበር እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙም ተናግረዋል፡፡
የሰላም ስምምነቱ መፈጸሙን ተከትሎ የብዙ ቤተሰቦች ህይወት በመረጋጋት ሁኔታዎችን እየተሻሻሉ መምጣታቸውን ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.8K views11:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-16 14:41:46 ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ የሚወስደው መንገድ ቢከፈትም አሁንም እየተጉላላን ነው ሲሉ አሽከርካሪዎች ቅሬታ አቀረቡ፡፡
ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ ከተማ በሚወስደው መንገድ ልዩ ስሙ ጎሃ-ጺዮን የተሰኘው አካባቢ የአማራና ኦሮሚያ ክልሎችን የሚያዋስን ሲሆን አካባቢውን አልፈው መንገደኞችን ጭነው የሚመጡ አሽከርካሪዎች ግን የነዋሪነት መታወቂያቸው እየታየ እንዳያልፉ መደረጉን በተደጋጋሚ ቅሬታ አቅርበዋል፡፡
ማለፍ ባለመቻላቸው ካለፈው ሃሙስ ጀምሮ ለ 5 ቀናት ያህል በከፍተኛ እንግልት ውስጥ መቆየታቸውን የሚናገሩት ቅሬታ አቅራቢዎቹ ‹‹መንገዱ ከማክሰኞ ጀምሮ ተከፍቷል ቢባልም አሁንም እየተጉላላን ነው›› ሲሉ ቅሬታቸውን ለአሐዱ አቅርበዋል፡፡
ይህንን በተመለከተ አሐዱ ያነጋገራቸው የደጀን ወረዳ የህዝብ ግንኙነት ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጌታሁን ጋሻዬ በበኩላቸው የአማራ ክልል መንግስት በተለይም የደጀን ወረዳና አካባቢው አስተዳደር ከኦሮምያ ክልል መንግስት ጋር ባደረገው ተደጋጋሚ ውይይት መንገዱ ከማክሰኞ ዕለት ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ክፍት በመደረጉ ምንም አይነት ችግር የለም ሲሉ ተናግረዋል፡፡
መንገዱ ክፍት ቢደረግም አሁንም መጉላላት እንዳለ አሽከርካሪዎች እየገለጹ ነውና ያለው ተጨባጭ ሁኔታ ምንድነው በሚል ከአሐዱ ለተነሳላቸው ጥያቄም ‹‹እንደሚባለው አይደለም አሁን ላይ መንገደኞች በሰላማዊ ሁኔታ እያለፉ ነው›› የሚል ምላሻቸውን ሰጥተዋል፡፡
ካለፉት ቀናት የተሻለ ሁኔታ ቢኖርም አሁንም እንግልት እየደረሰባቸው መሆኑን የሚናገሩት ቅሬታ አቅራቢዎቹ ሁሉንም መንገደኛ ማሳለፍ ያልተቻለበት ምክንያት ምን እንደሆነ ግልጽ አይደለም ነው ያሉት፡፡
አሐዱም የኦሮምያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽንን በዚህ ዘገባ ላይ ለማካተት ተደጋጋሚ ጥረት ቢያደርግም አልተሳካም፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.3K views11:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-16 14:38:33
የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና ላይ የሚካተቱ የትምህርት አይነቶች ተለይተው ዝግጅት እየተደረገባቸው እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡
በ2015 ዓ/ም ተመራቂ ተማሪዎች የሚጀምረው እና ከህግ እና ጤና ትምህርት ክፍሎች ውጪ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሰጠው የከፍተኛ ት/ት መውጫ ፈተና ሰኔ መጨረሻ እና ሀምሌ ውስጥ ለመስጠት በሚያስችል መልኩ ወደ ትግበራ የተገባ መሆኑን በማስታወስ በፈተናው ላይ የሚካተቱ የትምህርት አይነቶች ተለይተው ዝግጅት እየተደረገባቸው እንደሆነ ለአሐዱ የገለጹት በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ብቃት እና ጥራት ማሻሻያ ዴስክ ሀላፊ አቶ ሰይድ መሃመድ ተፈታኝ ተማሪዎች ይህንን ከግምት ውስጥ ባስገባ መልኩ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ለሁሉም ትምህርት ተቋማቶች አስቀድመው ማሳወቃቸውንም ገልጸዋል፡፡
ከዚህ ቀደም በነበረው ተሞክሮ በህግ እና ጤና ትምህርቶች ላይ ብቻ ይሰጥ የነበረውን የመውጫ ፈተና ለሌሎች ትምህርት ክፍሎችም እንዲሰጥ ተወስኖ ወደ ትግበራ የተገባው በህግ እና በጤናው መስክ የተመዘገበውን ውጤታማነት መሰረት በማድረግ መሆኑን ያወሱት ሃላፊው የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ ረገድ የመውጫ ፈተናው የጎላ አበርክቶ እንዳለውም ገልጸዋል፡፡
ትምህርት ሚንስቴር የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ እየሰራሁ ነው ከሚለው ዋና ትኩረቱ መካከል የከፍተኛ ት/ት ተቋማት የመውጫ ፈተና ዝግጅት አንዱ ነው፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
2.1K views11:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-16 14:35:39
በሀገሪቱ በሚፈጠሩ ማንኛውም ችግሮች የዜጎች ሰብዓዊ መብት መጣስ የለበትም ሲል የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ አሳሰበ፡፡
በማንኛውም ቦታ በሚፈጠሩ የጸጥታ ችግሮች የአዲስ አበባን የነዋሪነት መታወቂያ ካልያዛችሁ ወደ መዲናይቱ መግባት አትችሉም በሚል በተደጋጋሚ ዜጎች ሲንገላቱ እና ቅሬታም ሲያነሱ ይደመጣል፡፡
በሚፈጠሩ ችግሮች ዜጎችን ከቦታ ወደ ቦታ እንዳይንቀሳቀሱ መገደብ በገዛ ሀገራቸው እንደሌላ ሀገር ዜጋ እንዲቆጠሩ ማድረግ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ነው ያሉት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ ምክትል ስራ አስፈጻሚ አቶ ዘየደ ገብረ ጻዲቅ ናቸው፡፡
ከደንብ አስከባሪዎች ጀምሮ የጸጥታ አካላትም የሰብዓዊ መብትን ያለማወቅ እና ያለመረዳት ችግር እንዳለም ማረጋገጥ ይቻላል ነው ያሉት፡፡
ንጹሃን ዜጎችን ከማንገላታት ይልቅ ጥፋተኛው ላይ እርምጃ የመውሰድ ጸጥታ እና ሰላምን የማስጠበቅ ስራ ላይ መተኮር አለበት ባይ ናቸው፡፡
አሁን ላይ ግን በዜጎች ላይ እየተፈጸመ ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ህገ መንግስቱን፤ አህጉራዊ እንዲሁም ዓለማቀፋዊ የሰብዓዊ መብቶች ስምምነትን በመጣስ የሚፈጸም አንደሆነ እና የሰብዓዊ መብት ጥሰት የሚፈጽሙ የጸጥታ ሀይሎችም ላይ ይሁን ለጸጥታ ችግር ምክንያት የሆኑ ታጣቂዎች ላይ መንግስት እርምጃ መውሰድ አለበትም ሲሉም አንስተዋል፡፡
የዜጎች ሰብዓዊ መብት እንዳይጣስ በዚህ ረገድ የሚንቀሳቀሱ ተቋማት ምን አይነት ሀላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል ሲል አሐዱ ላነሳላቸው ጥያቄም በዚህ ረገድ የሚንቀሳቀሱ ሲቪል ማህበራትን የማዋከብ ፤ የማንገላታት፤ የማሸማቀቅ ድርጊት እየተፈጸመ በመሆኑ ይሄ አካሄድ ደግሞ መታረም አለበት ሲሉ ጨምረው ገልጸዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
2.0K views11:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ