Get Mystery Box with random crypto!

AHADU RADIO FM 94.3

የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3 A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3
የሰርጥ አድራሻ: @ahaduradio
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.23K
የሰርጥ መግለጫ

አሐዱ ራድዮ 94.3
Your source for top local and international news and analysis.
"Voice of Ethiopian"
የአሐዱ የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ በመሆን ወቅታዊና እውነተኛ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-06-30 17:19:38
በሚቀጥለው በጀት ዓመት ሙሉ ለሙሉ የዲጅታል መታወቂያን ተደራሽ አደርጋለሁ ሲል የአዲስ አበበ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወሳኝ ኩነትና ምዝገባ ኤጀንሲ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ አማካሪ አቶ መላክ መኮንን ለአሐዱ እንደገለጹት፣ በአዲስ አበባ ከተማ ለሚኖሩ መስፈርቱን ለሚያማሉና እድሜያቸው መታወቂያ ለማውጣት ለደረሱ ዜጎች የዲጅታል መታወቂያ ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ ነው፡፡
ኤጀንሲው ከሶስት አመት በፊት ጀምሮ የዲጂታል መታወቂያ ተደራሽ ለማድረግ ታቅዶ እየተሰራ ሲሆን ፣ እስካሁን ባለው ወይንም መረጃው እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ በአዲስ አበባ ከተማ በ11 ክፍለ ከተሞች በሚገኙ በ114 ወረዳዎች የድጂታል መታወቂያው እየተሰጠ ቢሆንም፣ 14 ወረዳዎች ተደራሽ እንዳልሆኑ አማካሪው ጠቁመዋል፡፡
አማካሪው አክለውም በኢንተርኔት መሰረተ ልማት ዝርጋታ ጋር በተያያዘ ችግሮች በመኖራቸው የዲጂታል መታወቂያውን በተያዘለት ቀነ ገደብ ተደራሽ ማድረግ አልተቻለም ብለዋል፡፡
ኤጀንሲው እስካሁን ባለው ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ሰዎችን የዲጅታል መታወቂያ ተደራሽ ማድረግ እንደተቻለ ከመስረተ ልማት ጋር ያሉ ችግሮችን በመቅረፍ በቀጣይ በ2016 በጀት ዓመት በመጀመሪያዎቹ ሩብ ዓመታት የዲጅታል መታወቂያውን ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
4.5K views14:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-30 14:39:11
በአንድ ሚንስቴር መስሪያ ቤት ብቻ የጎዳና ተዳዳሪነትን ችግር ሙሉ ለሙሉ መፍታት እንደማይቻል ተገለፀ፡፡
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በከተሞች ላይ ኑሮአቸውን በጎዳና ተዳዳሪነት የሚገፉ ህጻናት ቁጥር እየጨመረ የሚገኝ ሲሆን ከችግሩ ስፋት አኳያ በአንድ ሚንስቴር መስሪያ ቤት ብቻ መፍትሄ እንዲያገኝ ማድረግ እንደማይቻል የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የሴቶችና ሕፃናት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ወ/ሮ አለሚቱ ኡምድ ለአሐዱ ገልጸዋል፡፡
በአገር አቀፍ ደረጃ በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ጎዳና የሚወጡ ህፃናት ከየት አካባቢ እንደመጡ እና ምክንያቶቻቸው ላይ ሰፊ ጥናት በማድረግ ወደ ቤተሰቦቻቸው እንዲመለሱ የማድረግ እንዲሁም አማራጭ ለሌላቸው ደግሞ በጊዜያዊነት ከጎዳና ህይወት ተላቅቀው የሚኖሩበትን መንገድ የማመቻቸት ስራ እየተሰራ ሲሆን ከችግሩ ስፋት አኳያ ግን በቂ የሚባል እንዳልሆነ አስታውቀዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
4.2K views11:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-30 09:39:06
የተሸሻለው የቤት ግብር ክፍያ ሂደቱ አቅመ ደካሞችን እና ጡረተኞችን ከግምት ባስገባ መልኩ እንደሚከወን ተገለጸ፡፡
የቤት ግብር ክፍያን በተመለከተ በቅርቡ የወጣውን አዋጅ ተከትሎ በሀገሪቱ ያለውን ነባራዊ እውነታ ያገናዘበ አይደለም በሚል በርካታ ቅሬታዎች ሲነሱ እንደ ነበር ይታወሳል፡፡
ይህንኑ ጉዳይ አስመልክቶ ከአሐዱ መድረክ ጋር ቆይታ ያደረጉት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የታክስ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ ዘገየ በላይነህ በማህበረሰቡ ዘንድ የሚነሱ ቅሬታዎች ተገቢ መሆናቸውን አስታውሰው ሆኖም ግን የተጣራ መረጃን ካለማግኘት በሚፈጠር የግንዛቤ እጥረት የሚነሱ ቅሬታዎችን ግንዛቤን በመፍጠር ለማስተካካል እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ከዚህ ባሻገር የግብር ክፍያ ሂደቱ በማህበረሰቡ ላይ ጫና እንዳያሳድር የረጅም ጊዜ የክፍያ ሂደት እንዲኖር በማድረግ ዜጎች በረዥም ጊዜ ውስጥ ተረጋግተው የሚከፍሉበት አሰራር እንዲኖር መደረጉን ገልጸዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
4.1K views06:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-29 11:40:22
በሀዋሳ ከተማ ህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይት መስፋፋቱ ተገለፀ፡፡
በመላ ሀገሪቱ የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የተለያዩ እንከኖችን መቀነስ ቢቻልም እንኳን በተለያዩ አካባቢዎች ያለዉ ህብረተሰብ ቴክኖሎጅዉን የመቀበል አቅም በተወሰነ ደረጃ ዝቅ ማለት ህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይትን ለመቆጣጠር ተግዳሮት እንደሆነ ተነስቷል፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘ በሀዋሳ ከተማ ያለዉ ህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይት ከፍተኛ መሆኑን የገለፁት በነዳጅ እና ኢነርጅ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ ናቸዉ፡፡
ከዚሁ የህገ-ወጥ ንግድ ጋር በተያያዘ በሻሸመኔ እና ሀዋሳ አካባቢዎች የሚገኙ 5 ማደያዎች በጊዜያዊነት መታገዳቸዉም የሚታወስ ሲሆን ከተማዋ ካላት የተጠቃሚ እና በስራ ላይ ያሉ ማደያዎች ቁጥር አለመመጣጠን ጋር ተያይዞ የአቅርቦት ችግር እንዲጨምር አያደርግም ወይ ሲል አሐዱ ዳይሬክተሯን ጠይቆ ባገኘው ምላሽ፤ በሙሉ አቅማቸዉ የሚሰሩ ማደያዎች ቁጥር አነስተኛ መሆን ችግር ሊፈጥር እንደማይችል ተናግረዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
4.3K views08:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-29 10:56:00
ወንጀለኞችን ተጠያቂ የማድረግ ስራ የአንድ ተቋም ብቻ ሀላፊነት እንዳልሆነ የፍትህ ሚኒስቴር አስታወቀ፡
ወንጀለኞችን በቁጥጥር ስር ስታውሉ እንጂ አስተማሪ እርምጃ ስትወስዱ እየታየ አይደለም የሚል ጥያቄ እና አስተያየት ማህበረሰቡን ጨምሮ ከተለያየ አካላት እየተነሳ ነው ያሉት የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊሲ የኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ሀላፊ አቶ ጄላን አብዲ ፤
የፖሊስ ስራ መረጃን አሰባስቦ ወንጀለኛን ለሚመለከተው አካል ማቅረብ እንጂ አስተማሪ እርምጃ የመውሰድ ሀላፊነት የፍርድ ቤት ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡
በዚህ ጉዳይ ላይ አሐዱ የጠየቃቸው የፍትህ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት እና የኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ አወል ሱልጣን ወንጀለኛን ተጠያቂ የማድረግ ስራ ለአንድ ተቋም ብቻ የሚሰጥ ሳይሆን የፖሊስ፤የፍርድ ቤት ፤የአቃቤ ህግ እንዲሁም የማረሚያ ቤት የጋራ ስራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የግልጸኝነት እና የተጠያቂነት መርህ በሁሉም ተቋም ተግባራዊ መደረግ እንዳለበት የተናገሩት አቶ አወል ፖሊስ ምርመራውን ካከናወነ በኃላ ጉዳዩ ምን ላይ ደረሰ የሚለውን ማወቅ እና ማሳወቅ ይጠበቅበታል ነው ያሉት፡፡
ፖሊስ በተለያየ ወንጀል የጀመረውን የምርመራ ስራ ለአቃቤ ህግ ካስተላለፈ በኃላ በመጨረሻ የሚሰጠው ውሳኔ አይመለከተኝም ማለት ስለማይችል የሚሰጠው ውሳኔ ምንም ይሁን ምን እንደ ስኬት ሊያየው እንደሚገባ ገልጸው አቃቤ ህግ ክስ ስለመመስረቱ ፍርድ ቤት ስለመቅጣቱ የመጨረሻውን ውሳኔ ለማህበረሰቡ የማሳወቅ ሀላፊነት እንዳለበት ገልጿል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
4.1K views07:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-27 17:09:17
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደንና የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ የስልክ ውይይት ማድረጋቸው ተገልጿል፡፡
የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ሰፊ የስልክ ውይይት ማድረጋቸው ሲነገር የውይይታቸው ዋና ጭብጥ በወቅታዊነት በሩሲያ ሰላለው ሁኔታ መሆኑም ነው የተዘገበው፡፡
የዩክሬኑ ፕሬዝዳንትና የአሜሪካው አቻቸው በውይይታቸው አሜሪካ ለዩክሬን ያልተገደበ የወታደራዊ እና የሰብዓዊ ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል ተግባብተዋል፡፡
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ለዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ እንደገለጹላቸው ከሩሲያ ወረራ ነፃ ለመውጣት የምታደርገው ሁሉንም ትግሏን በፅናት ትወጣ ዘንድ መተማማኛቸውን ሰጥተዋቸዋል፡፡
የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎድሞር ዘለንስኪ በበኩላቸው ቅዳሜ እለት አመሻሽ በሰጡት ማብራሪያ ማንም ቢሆን በክፋት ተነስቶ ሌሎችን ለማጥፋት ቢሰራ ራሱን እንደሚያጠፋ ሊገነዘብ ይገባዋል ማለታቸው ይታወሳል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
4.8K views14:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-27 11:47:02
ድብደባ ደርሶባቸዉ አካል ጉዳተኛ የሆኑ የፓርቲ አባላት እንዳሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገልጿል፡፡
የተለያየ የፓርቲ አባል ናችሁ በሚል ከሚደርሰዉ አፈናና ማስፈራሪያ ባሻገር ድብደባ ደርሶባቸዉ አካል ጉዳተኛ የሆኑ፤ የስነ ልቦና ቀዉስ የደረሰባቸዉና ፓርቲዎችን እንዳይቀላቀሉ የተደረጉ ግለሰቦች መኖራቸውን የተናገሩት የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ዋና ፀሀፊ ዶክተር ራሄል ባፌ ናቸዉ፡፡
ካለፈዉ አምስት አመት ወዲህ እያንዳንዱ ፓርቲና ፖለቲከኛ የራሱን ርዕዮት ይዞ በመምጣት የተሻለ ስርአት ይኖራል የሚል ተስፋ ተጥሎ የነበረ ቢሆንም መልሶ ወደ ቀድሞው ስርአት እንዲመለስ ሆኗልም ብለዋል፡፡
በተለይም በክልሎች በፓርቲ አባላትና አመራሮች ላይ እየደረሰ ያለዉ የሰብአዊ መብት ጥሰት አደገኛ እንደሆነ እና እየደረሰ ያለዉ ጫናም ቢሆን የፖለቲካ ስርአቱን የሚያዛባ ነዉ ሲሉ የችግሩን አሳሳቢነት የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ዋና ፀሀፊ አብራርተዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
4.7K views08:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-27 10:46:08
የአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ መቆራረጥ ችግርን ይፈታል የተባለ የኤሌክትሪክ ማሻሻያ ስራ በሚቀጥለው አመት እንደሚጠናቀቅ የአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ በቀለ ክፍሌ ለአሐዱ እንዳሉት የአዲስ አበባን ኤሌክትሪክ መቆራረጥ ችግር ያስወግዳል ተብሎ ባለፈው ዓመት የተጀመረው የኤሌክትሪክ ማሻሻያ ስራ በተያዘው አመት ይጠናቀቃል ተብሎ የነበረ ቢሆንም በውጭ ምንዛሬና በሲሚንቶ እጥረት ምክንያት ተፈትኖ ቆይታል ብለዋል፡፡
የኤሌክትሪክ ማሻሻያ ስራው በአለም ባንክ ድጋፍና ብድር አማካኝነት በቻይና ባለሙያዎች የሚከናወን ሲሆን፣ በአዲስ አበባ ከተማ በሁሉም አከባቢዎች ተደራሽ እንደሚያደርግና የማሻሻያ ስራው የመስመር ዝርጋታ መቀየር፣ የኤሌክትሪክ ኃይል ማሻሻል፣የኤሌክትሪክ መስመር ፖሎችን መቀየር እንዲሁም ሌሎች ማሻሻያዎችን እንደሚያካትት የኮምኒኬሽን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
4.2K views07:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-26 17:29:20
የስርአት ለዉጥ አለመኖሩ ፓርቲዎች በሚገባ መንቀሳቀስ እንዳይችሉ አድርጓል ሲል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጹ፡፡
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድም ሆነ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በፓርቲዎችና መንግስት መካከል እንዲሁም በብልፅግና ፓርቲ በኩል ያሉትን ችግሮች ለመፍታት ጥረት እየተደረገ ቢሆንም ያለዉ የፖለቲካ ስርአት ያልተለወጠ መሆኑ አዳጋች አድርጎታል ሲሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ዋና ፀሀፊ ዶክተር ራሄል ባፌ ገልፀዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ እየተንቀሳቀሱ ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሀገራዊ ተሳትፎም ይሁን በፓርቲያቸዉ የዉስጥ ጉዳይ ለመነጋገር፤ አባላትን ለማፍራትና የደጋፊዎቻቸዉን ቁጥር ለመጨመር ጥረት በሚያደርጉበት ወቅት ለወከባና እስር በመዳረጋቸዉ የተነሳ ፓርቲዎች እንዲዳከሙ እያደረገ ነዉ ብለዋል፡፡
ከነበረዉ የኢህ አዲግ ስርአት የፀዳ አሰራር አለመኖሩ ከፍተኛ ችግር ሆኗል ሲሉ አክለዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
4.6K views14:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-26 15:50:35
በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ለማህበረሰቡ እርዳታዎችን ለማድረግ የሚያስችል የአቅም ችግር እንዳለባቸው ተገለጸ፡፡
በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የዓለም የምግብ ፕሮግራም እና ሌሎች የዓለም የእርዳታ ድርጅቶች በክልሉ የሚያደርጉትን ድጋፍ ከማቋራጣቸው ጋር ተያይዞ ለማህበረሰቡ ለመድረስ ምን እየሰሩ ነው ሲል የሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ባለስልጣንን አነጋግሯል፡፡
በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የማህበረሰቡ አካል እንደመሆናቸው ጦርነቱ እነሱንም ጎድቷቸዋል ያሉት የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ጂማ ዲልቦ ናቸው፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ አብዛኞቹ የሲቪል ማህበራት የገቢ ምንጮቸው ከውጪ በሚዘጋጁ ውድድሮች ላይ ቀርበው በማሸነፍ በሚገኙ እርዳታዎች እና ፈንዶች ነው ያሉ ሲሆን ተንቀሳቅሰው ገንዘብ ለማግኘት እና ውድድሮች ላይ ለመሳተፍ አልቻሉም ብለዋል፡፡
የሲቪል ማህበራቱ በተለያዩ አካባቢዎች ላይ በመንቀሳቀስ ለማህበረሰቡ የበጎ ፍቃድ አገልግሎቶችን እየሰጡ እና አቅም ያላቸው ማህበራትም አቀም ለሌላቸው እያካፈሉ እና እየተረዳዱ ነው የሚገኙት ብለዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
4.2K views12:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ