Get Mystery Box with random crypto!

AHADU RADIO FM 94.3

የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3 A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3
የሰርጥ አድራሻ: @ahaduradio
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.23K
የሰርጥ መግለጫ

አሐዱ ራድዮ 94.3
Your source for top local and international news and analysis.
"Voice of Ethiopian"
የአሐዱ የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ በመሆን ወቅታዊና እውነተኛ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-06-14 14:50:58
በኢትዮ ጅቡቲ ባቡር መስመር በተደጋጋሚ የሚደርሱትን ችግሮች ለመቀነስ የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚንስቴር አስታወቀ፡፡
የኢትዮ ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት መስመር ከዚህ በፊት የባቡር መሠረተ ልማት ስርቆት፣ የእንስሳት መጋጨት የባቡር እገታ እና መሠል ችሮች ሲስተዋሉ መቆየታቸዉ ይታወቃል፡፡
አሀዱም ችግሩን ለመፍታት ምን አይነት ስራዎች ተሰሩ ሲል የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚንስቴርን ጠይቋል፡፡
ችግሮችን ለመፍታት የፌደራል ፖሊስ ፤የክልል የፀጥታ አካላት፣እንዲሁም የትራንስፖርት ቢሮዎች ከህብረተሰቡ ጋር በመሆን ስራዎችን ሲሰሩ መቆታቸዉን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚንስትር ዲኤታ አቶ በርኦ ሀሰን ለአሀዱ ተናግረዋል፡፡
ከፍተኛ የደህንነት ስጋት በነበረባቸው የባቡር መስመሮች አካባቢ በተሰራዉ ስራ አሁን ላይ ስጋቱን መቀነስ መቻሉን አስታዉቀዋል፡፡
የባቡር መስመሩ የሚሰጠውን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ጥቅም ከፍ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ ገልፀዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
680 views11:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-14 11:00:27
በሱሉልታ ከተማ በታጣቂዎች ቁጥራቸው በውል ያልታውቁ ሰዎች ታፍነው ተወስደዋል በሚል እየተዘዋወረ ያለው መረጃ ሀሰተኛ እንደሆነ ተገለጸ፡፡
በቅርቡ በተዋቀረው የሸገር ከተማ አስተዳደር ሥር በሚገኘው የሱሉልታ ክፍለ ከተማ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሰዎች መንግስት ሸኔ ብሎ በሚጠራው ቡድን ታጣቂዎች ታፍነው መወሰዳቸውን የሚገልጹ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ድህረ ገጾች ላይ ሲዘዋወሩ እንደነበር ይታወሳል፡፡
የተወሰዱት ሰዎችም ያሉበት እንደማይታወቅ እና አጋቾችም ይህን ያህል ብር አምጡና እንለቃቸዋለን በማለት እየተደራደሩ እንደሚገኙ መዘገቡም ይታወቃል፡፡
ይህንኑ ጉዳይ በተመለከተ ያለውን ነባራዊ እውነታ እንዲያብራሩ አሃዱ ያነጋገራቸው የሸገር ከተማ አስተዳደር ኮሚኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ናስር ሁሴን ከተማ አስተዳድሩ መረጃው ከወጣ በኋላ የማጣራት ስራዎችን እንደሰራ አንስተው ሆኖም በከተማ መስተዳድሩ ውስጥ በሚገኙ ክፍለ ከተሞች ውስጥ ታፍነው የተወሰዱ ዜጎች አለመኖራቸውን ተናግረዋል፡፡
ሃላፊው አክለውም በማህበራዊ ሚዲያዎች እየወጡ ያሉት ዘገባዎች ከእውነት የራቁ እና ተአማኒነት የሌላቸው መሆናቸውን በመግለጽ ህብረተሰቡን በተሳሳቱ ዘገባዎች ማደናገር ተገቢ አለመሆኑን ተናግረዋል፡፡አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
1.8K views08:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-13 14:33:15
በአገር አቋራጭ መንገዶች ላይ የሚስተዋሉ የደህንነት ስጋቶችን ለመፍታት ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ የቅንጅት ስራ መጀመሩ ተገለፀ፡፡
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተለያዩ አገር አቋራጭ መንገዶች ላይ በታጣቂዎች የሚደርሱ እገታዎች እንዲሁም ጥቃቶችን ተከትሎ አሽከርካሪዎችም ሆኑ ተሳፋሪዎችን ከፍተኛ ስጋት ውስጥ እንዲወድቁ አድርጓል፡፡ ፡፡
የችግሩን አሳሳቢነት በመረዳት ከሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ምክትል ፕሬዘዳንቶች እንዲሁም የትራንስፖርት ቢሮ እና የፀጥታ ቢሮ ሀላፊዎችን ያሳተፈ ሰፊ ውይይት በማድረግ የቁጥጥር ስራውን በማጠናከር መንገዶቹ ሰላማዊ እንዲሆኑ የማድረግ ስራዎች መጀመራቸውን የትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚንስቴር ሚኒስትር ዴኤታው አቶ በርኦ ሀሰንን አነጋግሯል አስታውቀዋል፡፡
አክለውም በተወሰኑ አካባቢዎች ላይ በወጪ እና ገቢ ንግድ ትራንስፖርት ላይ ብቻ የሚሰሩ አገር አቋራጭ የጭነት ተሸከርካሪዎች ላይ መንገድ በመዝጋት እና ላልተፈለጉ አላማዎች እንዲሁም በግዳጅ የተለያዩ የአገር ውስጥ ጭነት አገልግሎቶች እንዲውሉ ማድረግን የመሰሉ ህገ ወጥ ተግባራት እንደሚስተዋሉ ገልፀዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
3.8K views11:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-13 11:29:02
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ልኡካን ወደ አማራ ክልል መግባታቸው የሁለቱን ክልሎች ግንኙነት ለማጠናከር ጥሩ ጅማሬ መሆኑ ተገለፀ፡፡
በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርእሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ የሚመራ ልዑክ ከአማራ ክልል መስተዳድር እነ የቢሮ ሃላፊዎች ጋር በባሕር ዳር ዉይይት ማድረጉ ይታወቃል፡፡ በሁለቱ ክልሎች መካከል ያለውን ውጥረት ለማርገብ ሆነ ዳግም ግጭት እንዳይፈጠር ምን አይነት አስተዋጾ አለዉ ሲል አሐዱ የፖለቲካ ፓርቲዎችን አነጋግሯል፡፡
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ወደ አማራ ክልል መሄዳቸው በሁለቱ ክልሎች መካከል ያለውን ዉጥረት ሰላም ለማስፈን እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን ለማጠናከር ጥሩ የሚባል ጅማሮ ነው ብለዉ ሰላምን ለማስፈን ከዚህም በላይ ግንኙነቶችን ማጠናከር አስፈላጊ ነው ያሉት የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የፖለቲካ ዘርፍ አባል ኮማንደር ገብረመስቀል ገብረሚካኤል ናቸው፡፡
ሆኖም የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በሚጠበቀው መልኩ አለመተግበሩ አሁንም ለክልሎቹ አንዱ ችግር መሆኑን አንስተዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
3.3K views08:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-13 10:26:50
አደገኛ አውሎ ነፋስ በመጪው ሀሙስ የህንድን ምዐራባዊ ዳርቻ ሊመታ እንደሚችል ተሰግቷል፡፡
በሀገሪቱ ምዕራባዊ የባህር ዳርቻ እያደገ የመጣው ማዕበል ወደ ሀይለኛ አውሎ ነፋስነት ሊቀየርና የጉጅራትን ግዛት እንዲሁም የፓኪስታንን ደቡባዊ አካባቢዎች ሊመታ ይችላል ነው የተባለው፡፡
ቢፓ ርጆሪ ተብሎ የተሰየመው አውሎ ነፋስ የፊታችን ሀሙስ ሊከሰት እንደሚችል እና ከ125 እስከ 135 ኪሎሜትር በሰዓት እንደሚጓዝ የህንድ አየር ትምበያ መስሪያ ቤት በትላንትናው እለት አሳውቋል፡፡
የአየር ንብረት መስሪያ ቤቱ አሳ አጥማጆች ስራቸውን እንዲያቆሙ እና ማህበረሰቡም አካባቢውን ለቆ እንዲወጣ ማሳሰቢያ መስጠቱም ተነግሯል፡፡
እያደገ በመጣው ከባድ የአየረ ጸባይ ምክንያትም በጉጂራት ወደብ ስራዎች እንዲቋረጡ መደረጉን በወደቡ የተሰማራ አንድ ኃላፊነቱ የተወሰነ ኩባንያ ማሳወቁም ተጠቁሟል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
3.1K views07:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 16:35:25
በኢትዮጵያ ዉስጥ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተሻጋሪ የሆነ ስርአት መዘርጋት ላይ ተኩረት አድረገዉ ሊሰሩ እንደሚገባ ተጠቆመ፡፡
ሀገሪቱ በተለያዩ ጊዜያት የሚያጋጥሟት አለመረጋጋቶች እና የጦርነት አዙሪቶች በሙሉ ከፖለቲካዋ ስርአት ጋር መያያዙ እንደ ዋና መንስኤነት ይነሳል፡፡
ለዚህ ደግሞ ግንባር ቀደም ተጠያቂ የሚሆኑት የለቲካዉ ስርአት ላይ ከፊት የተቀመጡ የፓርቲ አመራሮች ናቸዉ ያሉት የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ዶክተር መብራቱ አለሙ ናቸው፡፡
በሀገሪቱ ታሪክ ሁሉም ፓርቲዎች ስልጣንን እና ሃብትን የመካፈል ፍላጎትን ከፊት አድርገዉ መነሳታቸዉ ችግሩን አክብዶታል ሲሉ ይገልፃሉ፡፡
አክለዉም በሀገሪቱ ያለዉን ሰላም እና መረጋጋት በዘላቂነት ለማስፈን የፖለቲካ ጥቅምን ከማስቀደም ይልቅ ዘላቂ የሆነ ፡ ለትዉልድ የሚሻገር የአሰራር ስርአትን መዘርጋት ላይ መስራት ይገባቸዋል ሲሉም አክለዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
3.7K views13:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 10:59:59
በትግራይ ክልል ሰሜን ምእራብ ዞን እና አዲ ዳአሮ ወረዳ አካባቢ ከፍተኛ የሆነ የማእድን ዘረፋ እና የኮንትሮባንድ ንግድ እንዳለ ተገለጸ፡፡
የአዲ ዳአሮ ከተማ ከንቲባ አቶ ተፈሪ ሀይለመለኮት ሰሜን ምእራብ ዞን እና የአዲ ዳአሮ ዞን አካባቢ ከፍተኛ የሆነ የማእድን ዝርፊያ እንዳለ ለአሐዱ ገልጸዋል፡፡
በተለይ ከፍተኛ የሆነ የወርቅ ክምችት በአካባቢዎቹ በመኖሩ ሰፊ የሆነ የኮንትሮባንድ ዝርፊያ እና ንግድ እንዳስቸገራቸው እና ወንጀሉን ለመቆጣጠር ክልሉ ካሉበት የጸጥታ ችግሮች አንፃር ቁጥጥሩን ፈታኝ እንዳደረገባቸው ጨምረው ተናግረዋል፡፡
ከንቲባው እነዚህ የማእድን ሀብቶች በአግባቡ ጥቅም ላይ ቢውሉ ለክልሉም ሆነ ለሀገሪቱ የሚጠቅሙ ናቸው ያሉ ሲሆን ፣ ዘረፋው እና የኮንትሮባንድ ንግዱ እስከ ኤርትራ እና ሱዳን የሚደርሱ ትላልቅ መረቦች አሉት ብለዋል፡፡
ይህ የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ ለማዕድን ዘርፉ ማደግ እንቅፋት እየሆነ መምጣቱን ገልጸው፤ ዘርፉን ለመታደግ እና ሀገር ከዘርፉ ማግኘት የሚገባትን ተገቢውን ጥቅም እንድታገኝ ተገቢው የድንበር ጥበቃ እንዲደረግና አስፈላጊው ትኩረት እንዲሰጠውም አስገንዝበዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
3.8K views07:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 10:00:00
የቤት ግብር ማሻሻያው የተደረገው መንግስት ላይ ከፍተኛ የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች በመኖራቸው ነው ተብሏል፡፡
በቅርቡ ይፋ የተደረገውን የቤት ግብር ማሻሻያ አስመልክቶ በርካታ ሃሳቦች ይደመጣሉ፡፡ ከነዚህም መካከል በአሁኑ ወቅት በዜጎች ላይ ከሚታየው ምጣኔ ሃብታዊ ጫና አንጻር ማሻሻያው ወቅታዊ አይደለም የሚሉ ሃሳቦች ሲነሱ ይደመጣል፡፡
ይህን ጉዳይ አስመልክቶ አሃዱ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ የንብረት ግብር ማስተግበርያ ጊዜያዊ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት አስተባባሪ አቶ አስማማው ሙሉጌታን አነጋግሯል፡፡
የያዝነው ዓመት ብዙ የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች የተነሱበት እንደነበር ጠቅሰው እነዚህን የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች ለመፍታት ደግሞ ግብር መክፈል ዋነኛ መፍትሄ በመሆኑ ከዚህ በፊት ለረጅም ጊዜ ተግባራዊ ሲደረግ የቆየው ነባር አዋጅ ላይ ማሻሻያ ተደርጓል ሲሉ ገልጸዋል፡፡
ለዚህም የንብረት ባለቤቶች አንጻራዊ በሆነ መንገድ የተሻለ የመክፈል አቅም አላቸው ያሉ ሲሆን ባለቤቶቹ እንደንብረታቸው መጠን እንዲከፍሉ እየተደረገ ይገኛል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ የመክፈል አቅምና ገቢ የሌላቸው ከሆኑ በየወረዳው እየተገመገመና እየቀረበ ነጻ የሚሆኑበት ወይም ምህረት የሚደረግበት አሰራር እንዳለም በአዋጁ ተቀምጧል ብለዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
3.6K views07:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 15:00:18
በአማራ ክልል የሚታየውን ችግር ለመቅረፍ በክልሉ ቁርጠኛ ሆኖ የሚታገል አመራር የለም ሲሉ በአማራ ክልል የምክር ቤት የአብን አባላት ገለጹ፡፡
በአማራ ክልል ምክር ቤት የሚሳተፉ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) አባላት ወቅታዊ የክልሉን ሁኔታ አስመልክተው መግለጫ ማውጣታቸው ይታወሳል፡፡
እናንተስ በምክር ቤት አባልነታችሁ በመግለጫችሁ ቀሳችዃቸውን ችግሮች ለመቅረፍ ምን እየሰራችሁ ትገኛላችሁ ሲል አሃዱ አባላቱን አነጋግሯል፡፡
ምክር ቤቱ በመተዳደሪያ ደንቡ ላይ እንደተቀመጠው በዓመት ዝቅተኛ የሚሰበሰበው ለሶስት ጊዜያት በመሆኑ አባላቱን በንቃት በማሳተፍ አስፈጻሚውን ቀርቦ ለመገምገምም ሆነ የህዝቡን ችግር በየጊዜው እየገመገሙ ለመፍታት የሚያስችል ግንኙነት የለንም ያሉት በአማራ ክልል ምክር ቤት የአብን ተወካይ እና የባህር ዳርና አካባቢው አስተባባሪ ዶክተር በቃሉ ታረቀኝ ናቸው፡፡
በክልሉ ባለው መዋቅርም ለአማራ ክልል ህዝብና በክልሉ ላሉት ችግሮችም በቁርጠኝነት የሚታገል አመራር አለ ብሎ ለመናገር የሚያስደፍር አይደለም ሲሉ ተናግረዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
3.2K views12:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 12:00:00
ውይይት አድርጎ ወደ ስራ ለመግባት ለትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ደብዳቤ ተፅፎ ምላሽ እየተጠባበቀ መሆኑን ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ አስታወቀ።
በምክክሩ አስፈላጊነትና አካሄድ ላይ ዉይይት አድርጎ ወደ ስራ ለመግባት ለትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ደብዳቤ ተፅፎ ምላሽ እየተጠባበቀ መሆኑን ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ አስታዉቋል፡፡
የትግራይ ክልልን ጨምሮ በሁሉም ክልሎች በሚገኙ ወረዳዎች የተሳታፊዎች ልየታና አጀንዳ የማሰባሰብና የመረጣ ስራ አስቸጋሪ ሁኔታ ካላጋጠመ በስተቀር የ2015 ዓ.ም ከመጠናቀቁ በፊት እንደሚጠናቀቅ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ አንዱ ኮሚሽነር እና የህዝብ ግንኙነት ሀላፊዉ ዶክተር ዮናስ አዳዬ ለአሀዱ ተናግረዋል።
ከጊዜዊ አስታዳደሩ ለተፃፈዉ ደብዳቤ ምላሽ ሲገኝ ስራዎችን እንደሚኪያከናዉኑ አስታዉቀዋል፡፡
በክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ደረጃ ለሚደረጉ የአጀንዳ ማሰባሰብ ስራዎች ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍሎች ሁለት ሁለት ተወካዮችን ይመርጣሉ ብለዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
3.3K views09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ