Get Mystery Box with random crypto!

AHADU RADIO FM 94.3

የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3 A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3
የሰርጥ አድራሻ: @ahaduradio
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.23K
የሰርጥ መግለጫ

አሐዱ ራድዮ 94.3
Your source for top local and international news and analysis.
"Voice of Ethiopian"
የአሐዱ የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ በመሆን ወቅታዊና እውነተኛ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-03-17 16:50:05
የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ከፓርቲዎች መሰረታዊ ችግር ጋር ተያይዞ በመግለጫዉ ያነሳዉ ሀሳብ ሀላፊነት እንደወሰደ የሚያሳይ ነዉ ሲሉ ፓርቲዎች ገለጹ፡፡
የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ከፓርቲዎች ጋር ተያይዞ እያጋጠሙ ያሉ ተፅእኖችን እንዴት መፈታት እንደሚገባ በሰጡት መግለጫ አብራርተዋል፡፡

አሀዱም በተለይ የተፅእኖዉ ሰለባ የሆኑ ፓርቲዎችን ያነጋገረ ሲሆን የእናት ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ያየህ አስማረም ዋና ሰብሳቢዋ በተለይ ድርጊቱን የፈፀሙት ተጠያቂ እንዲሆኑና ፍትህ ሚኒስቴር ክስ እንዲመሰርት ማለታቸዉ ፤ድርጊቱ በመንግስት ሀይሎች የሚፈፀም ነዉ ብለዉ መሬት ላይ ያለዉን ነባራዊ እዉነት ማንሳታቸዉ ጥሩ ጅማሮ ነዉ ሲሉ ገልጸዋል፡፡

የባልደራስ ለእዉነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ዶክተር በቃሉ አጥናፉ በበኩላቸዉ በተለይ ከመሰብሰቢያ አዳራሽ አንፃር የከዚህ ቀደም ጥያቄያችን በምርጫ ቦርድ መሰብሰቢያ አዳራሽ በአማራጭነት መቅረቡና ቦርዱ ይህን ማመቻቸቱ ለዚህም ምላሽ መሰጠቱ ተገቢነት ያለዉ በመሆኑ ፓርቲያችን የሚቀበለዉ ነዉ ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አንዱ ሀላፊነቱ በፓርቲዎች መካከል የሚፈጠሩ ችግር መፍታት በመሆኑ የጀመረዉን ሂደት እንዲሁም በመግለጫዉ የተቀመጡት ዉሳኔዎች እንዲፈጸሙ በተለይም ተጠያቂነትን ማረጋገጥ እንዲችልም ፓርቲዎቹ ጠይቀዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
1.6K viewsedited  13:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-15 16:54:40

1.5K views13:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-15 16:36:11

1.6K views13:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 15:32:24
የስነ-ህዝብ ትሩፋትን የተመለከተ አዲስ ጥናት በቀጣዮቹ ሳምንታት እንደሚጀመር ተገለጸ፡፡
በአንዲት ሃገር ውስጥ ያለውን የህዝብ ብዛት መጠን ከግምት ባስገባ መልኩ ምጣኔ ሃብታዊ ጥቅምን ለማረጋገጥ የሚነደፉ ስትራቴጂዎችን ያካተተው የስነ-ህዝብ ትሩፋት ጽንሰ-ሃሳብ ተግባራዊ ለማድረግ ሃገር አቀፍ የህዝብ ቆጠራ መካሄድ እንዳለበት መገለጹ ይታወሳል፡፡ በቀጣዮቹ ሳምንታት የሚጀመረው ጥናትም ኢትዮጲያ በምን መልኩ የስነ-ህዝብ ትሩፋትን በአግባቡ ማግኘትና ተጠቃሚ መሆን ትችላለች የሚለውን ለመመለስ ያለመ እንደሆነ ለአሃዱ የገለጹት በፕላንና ልማት ሚኒስቴር የስነ-ህዝብ ዘርፍ የቴክኒክ አማካሪው አቶ ተፈሪ ደገፋ ናቸው፡፡
ጥናቱ እያንዳንዱ የመንግስት ሴክተር ያለበትን ስራና ሃላፊነት ከመለየት ባለፈ አዳዲስ ፖሊሲና ስትራቴጂዎችን በውጤትነት ይዞ ይወጣል የሚል እምነት እንዳላቸው የገለጹት አማካሪው ጥናቱ በዋነኝነት በፕላንና ልማት ሚኒስቴር እንደሚከናወንም ተናግረዋል፡፡
ይህንን ጽንሰ-ሃሳብ ተግባራዊ ከሚያደርጉ የእስያ ሃገራት መካከል ደቡብ ኮርያ በዋነኝነት እንደምትጠቀስ ገልጸው ኢትዮጵያም ተሞክሮውን በመውሰድ ጥናቱን አጠናቅቃ ጽንሰ-ሃሳቡን ተግባራዊ ማድረግና ያላትን የህዝብ ምጣኔ ለልማት ማዋል ይኖርባታል ሲሉም ገልጸዋል፡፡
የጥናቱ ዋነኛ ባለቤት የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ቢሆንም የተባበሩት መንግስታት የስነ-ህዝብ ፈንድ ከፍተኛ ድጋፍ እንደሚያደርግም አመላክተዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
683 views12:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 15:27:57
አሜሪካ ከኢትዮጲያ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማደስ ቅድመ-ሁኔታዎች መሟላት እንደሚኖርባቸው የአሜሪካ መንግስት አስታወቀ፡፡
ይህንን ያሉት የአሜሪካ መንግስት ቃል-አቀባይ ቢሮ የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ጸሃፊ ሞሊ ፊ ሲሆኑ የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን በተያዘው ሳምንት በኢትዮጲያና በኒጀር የሚያደርጉትን ጉብኝት በተመለከተ በሰጡት መግለጫ ላይ መሆኑን ቢሮው ለአሃዱ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡
የቢሮው ረዳት ጸሃፊ ሞሊ ፊ የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን የሰሜኑ ጦርነት እልባት እንዲያገኝ በማድረግ ረገድ ሰፊ ስራ አሜሪካ መስራቷን በውቅቱ ገልጸው በነገዉ እለት ወደ ኢትዮጲያ የሚያደርጉት ጉዞም ከሰላም ስምምነቱ በኋላ የተከናወኑ ዘርፈ-ብዙ ስራዎችን ለመመልከት ያለመ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡
ከሰላም ስምምነቱ በኋላ አሜሪካ ከኢትዮጲያ ጋር የሚኖራት ግንኙነት የአፍሪካ ነጻ የንግድ ተጠቃሚነት ወይንም ‹‹አጎዋ››ን ጨምሮ ወደ ቀድሞው መደበኛ ግንኙነት የመመለስ እድል አለው ወይ በሚል ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄም ረዳት ጸሃፊው ‹‹ፊ››አሜሪካ ከኢትዮጲያ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማደስ ቅድመ-ሁኔታዎች መሟላት እንዳለባቸው ነዉ ምላሽ የሰጡት፡፡
አሜሪካና ኢትዮጲያ ዘመናትን ያስቆጠረ ግንኙነት ያላቸው ሃገራት ቢሆኑም ግንኙነት ለማደስ ግን ኢትዮጵያን ለአስርት አመታት ወደ ኋላ እየጎተታት ያለዉን በተለያዩ አካባቢዎች የሚስተዋሉትን የብሄር ማንነትን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች ሊቆሙና መረጋጋትም ሙሉ በሙሉ ሊሰፍን ይገባል ነው ያሉት፡፡
የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ነገ ረቡ በኢትዮጵያ የሚያደርጉት ጉብኝትም በዋነኝነት የሰላም ስምምነቱ ተግባራዊነት ላይ የሚያተኩር ነው ያሉት ረዳት ጸሃፊው የሁለቱን ሃገራት ግንኙነትም ያድሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ አክለዋል፡፡
722 views12:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 15:25:22
የተፈጠረውን የጸጥታ ችግር ተከትሎ የባጃጅ ተሸከርካሪዎቻቸዉ በጸጥታ አካላት እንደተወሰዱና እስካሁን እንዳልተመለሱላቸዉ አሽከርካሪዎች ለአሃዱ ቅሬታ አቅርበዋል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊሰ ኮምሽን በበኩሉ በህገ ወጥ ድርጊት ላይ የተሳተፉ ግለሰቦችን እና 194 የባጃጅ ተሽከርካሪዎችን በህግ ቁጥጥር ስር ማዋሉን ገልጻል፡፡
ለአሃዱ ቅሬታቸውን ያቀረቡት የባጃጅ አሽከርካሪዎች እንደተናገሩት ስራ ከማቆማቸው ባሻገር ባጃጆቻቸው ተጭኖ በመወሰዱ የት እናዳለ እንደማያውቁ እና በርካታ የስራ ባልደረቦቻቸው በአሁኑ ሰአት በእስር ላይ እንደሚገኙ ገልጸው የሚመለከተው አካል አፋጣኝ መፍትሄ ይስጠን ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮምሽን የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ በበኩላቸው በከተማው ላይ የጸጥታ ችግር እንዲፈጠር ከማድረግ ባሻገር በአካባቢው የትራፊክ መጨናነቅ እንዲኖር ያደረጉ እና የጸጥታ አካላት ላይ ጥቃት የፈጸሙ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸዉን ጠቅሰዉ ከጸጥታ ችግሩ ጋር በቀጥታ ግንኙነት የነበራቸውን 194 ገደማ የባጃጅ ተሽከርካሪዎች በቁጥጥር ስር እንደዋሉና አስፈላጊው የህግ ሂደት እየተደረገባቸው እንደሚገኝም ለአሃዱ ተናግረዋል፡፡
ምክትል ኮማንደር ማርቆስ አክለውም በተለይ ከጸጥታ አካላት ጋር ግጭት የፈጠሩ በርካታ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልጸው ጉዳያቸው በህግ አግባብ እየተጣራ እንደሚገኝም አስታዉቀዋል፡፡
ማንኛውም የመብት ጥያቄ በህግ አግባብ መሰረት መጠየቅ አለበት ያሉት ምክትል ኮማንደሩ ከዛ ውጪ የሆነ ነገር በህግ እንደሚያስጠይቅ ማህበረሰቡ ሊገነዘብ ይገባል ነዉ ያሉት፡፡ በአዲስ አበአባ ከተማ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት ካሳለፍነዉ ሳምንት ጀምሮ እንዲቋረጥ መደረጉ የሚታወቅ ነዉ፡፡
654 views12:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 14:50:47
ባለፉት 6 ወራት ከ200 ሺህ በላይ ነዋሪዎች የዲጅታል መታወቂያ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸዉ ተገለፀ፡
በአዲስ አበባ ከተማ 118 ወረዳዎች የሚገኙ ሲሆን 104 ወረዳዎች ዲጂታል አገልግሎት ሙሉ ለሙሉ እየሰጡ መሆናቸዉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና መረጃ ኤጀንሲ አስታዉቋል፡፡
ቀሪዎቹ 14 ወረዳዎች ንፋስ ስልክ ላፍቶ፤ አቃቂ እና በለሚኩራ ክፍለ ከተማ የሚገኙ ወረዳዎች ሲሆን የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነላቸዉ መሆኑን በምክትል ዋና ዳይሬክተር ማዕረግ የኤጀንሲዉ አማካሪ አቶ መላክ መኮንን ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
በቅርቡ እነዚህ 14 ወረዳዎች እየተከናወነ ያለዉ የመሰረተ ልማት ግንባታ ሲጠናቀቅ ዲጅታል አገልግሎቱን ይስጣሉ ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል፡፡
የዲጅታል አገልግሎቱ ብልሹ አሰራርን ለመከላከል እንደሚያስችል ገልፀዉ ባለፉት 6 ወራት ከ200ሺህ በላይ ነዋሪዎች የዲጅታል መታወቂያ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸዉን አስታዉቀዋል፡፡
በህመም ላይ ላሉ ዜጎች በልዩ ሁኔታ የማኑዋል አገልግሎት ተፈቅዶ የቤት ለቤት አገልግሎት እየተሰጣቸዉ መሆኑን አቶ መላክ አክለዉ ተናግረዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
931 views11:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 14:47:25
ከዚህ ቀደም ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ በአንድ አመት የጊዜ ሂደት ይሰበሰብ የነበረውን ገንዘብ በሰባት ወር ውስጥ መሰብሰብ እንደተቻለ ተገለጸ፡፡
ምንም እንኳን በሀገራችን ያለው ነባራዊ እውነታ በብዙ መልኩ አመቺነት ባይኖረውም ከመቼውም ጊዜ በላይ ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውል ገንዘብ ከህብረተሰቡ መሰብሰብ መቻሉን በማስታወስ በዘንድሮው አመት ባለፉት ሰባት ወራቶች ብቻ ከ948 ሚሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን የገለጹት የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤ የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሀይሉ አብርሃም የህዳሴው ዋንጫ ባለፉት ስድስት ወራት በመላ ሀገሪቱ ባይዞርም ህብረተሰቡ ግን በሌሎች መንገዶች ድጋፉን በመቀጠሉ ገቢው ከፍ እንዲል ማድረግ ማስቻሉን ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
የገቢ መጠኑን ከዚህም በላይ ለማሳደግ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ አክልው የገለጹት አቶ ሀይሉ የህዳሴው ግድብ 12ተኛ አመት ክብረ በአልን አስመልክቶም የተለያዩ ሁነቶችን በማዘጋጀት እና ህብረተሰቡን ተሳታፊ በማድረግ ገቢውን ለመጨመር ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ተግባር ለመግባት በሂደት ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከተጀመረ የፊታችን መጋቢት 24 ቀን 2015 ዓ/ም ድፍን አስራ ሁለት አመታት እንደሚሆነው ይታወቃል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
914 views11:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 13:43:31
በደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን የሚገኙ ስድስት አባላቱ ያለአግባብ እንደታሰሩበት ኢዜማ አስታወቀ፡፡

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ ኢዜማ አምስት የደቡብ ክልል ምክር ቤት አባላቱን ጨምሮ ስድስት የፓርቲዉ አባላት ያለአግባብ በመታሰራቸዉ መንግሥት በአስቸኳይ እንዲፈታቸዉ ሲል ጠይቁዋል፡፡
የኢዜማ የህግና የአባላት ደህንነት ጉዳይ መምሪያ ሃላፊ አቶ ስዩም መንገሻ ለአሀዱ እንደተናገሩት አባላቶቹ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ተይዘዉ መታሰራቸዉን አስታዉቀዋል፡፡

የታሳሩት የፓርቲዉ አባላት ከየካቲት 22 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በእሥር ላይ እንደቆዩና በሕጉ መሠረት 48 ሰዓት ፍርድ ቤት መቅረብ ሲገባቸው እስካሁን ድረስ ፍርድ ቤት እንዳልቀረቡ ገልፀዋል፡፡
አባላቱ የተከሰሱበት ጉዳይ እንዳልታወቀ ገልጸዉ በዚህም ምክንያት በአባላቱ ላይ የህገ መንግሥት ጥሰት እየተፈጸመባቸው ይገኛል ነዉ ያሉት፡፡

ለደቡብ ክልል ፍትህ ቢሮ ፣ ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እና ለፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤትን ጨምሮ ለተለያዩ አካላት ጥያቂያቸዉን በደብዳቤ ማቅረባቸዉን አቶ ስዩም አክለዉ ተናግረዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
1.9K views10:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 13:39:53
የስነ ምግባር ጉድለት ባሳዩ እና በብልሹ አሰራር ላይ በተሳተፉ 109 ሰራተኞች ላይ እርምጃ እንደተወሰደባቸዉ ተገለጸ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አሌክትሪክ አገልግሎት ባለፉት 6 ወራት የስነ ምግባር ጉድለት ባለባቸዉ በሙስና እና በብልሹ አሰራር ላይ በተሰማሩ 109 ሰራተኞች ላይ እርምጃ መወሰዱን አስታዉቋል፡፡
ከነዚህ ሰራተኞች መካከል 15 የሚሆኑ ሰራተኞች ከስራ እንዲሰናበቱ መደረጉን የአዲስ አበባ ከተማ አሌክትሪክ አገልግሎት የእቅድ ዝግጅት ክፍል ስራ አስፈፃሚ አቶ አወል ካሳ ተናግረዋል፡፡

16 የሚሆኑ አመራሮች ከሀላፊነት እንዲነሱ መደረጉን ገልፀዉ በሌሎቹ ላይ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱን አስታዉቀዋል፡፡
የክፍያ ጊዜን ለደንበኛዉ በወቅቱ ከማሳወቅ አንፃር ያሉ የአሰራር ክፍተቶችን በማሻሻል የተጠያቂነትን ለማስፈን በትኩረት እየሰሩ መሆናቸዉን ተናግረዋል፡፡
ህግና ስርዓትን በመጣስ ተገልጋይን የሚያጉላሉ ሰራተኞች ላይ አስፈላጊዉን እርምጃ ለመዉሰድ ቁርጠኛ መሆናቸዉን አቶ አወል አክለዉ ተናግረዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
1.7K views10:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ