Get Mystery Box with random crypto!

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ) Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ)
የሰርጥ አድራሻ: @zemedkun_zemede
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.26K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-06-22 07:19:27 ሐሙስ ጠዋት! ሰኔ 15/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የካርጎ ሎጅስቲክስ ክፍል "ወደ ሌላ አገር በሽያጭ ሊተላለፍ" ወይም "ለብድር መያዣነት ሊውል" እንደኾነ ተደርጎ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች የሚሰራጨው መረጃ "ከእውነት የራቀ" እና "መሠረተ ቢስ" መኾኑን አስታውቋል። "ይህ ከእውነት የራቀ ወሬ የብሔራዊ አየር መንገዳችን ስም እና ገጽታ" ይጎዳል ያለው አየር መንገዱ፣ ወሬውን የሚያሰራጩ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ጠይቋል።

2፤ ኦብነግ አንድ የመከላከያ ሠራዊት አባል ማክሰኞ'ለት ቀብሪደሃር ከተማ ውስጥ በከፈተው ድንገተኛ ተኩስ ከተገደሉት ግለሰቦች መካከል ሦስቱ አባላቱ እንደኾኑ አስታውቋል። የሠራዊቱ አባል በተኩሱ አንድ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ አመራር አባልን ጨምሮ አራት ሰዎችን ገድሎ ሌሎች ሁለት ሰዎችን ማቁሰሉን ግንባሩ ገልጧል። የሱማሌ ክልልና ፌደራል መንግሥታት ድርጊቱን አጣርተው ርምጃ እንዲወስዱ የጠየቀው ኦብነግ፣ በክልሉ በተደጋጋሚ የሚፈጸሙ የመብት ጥሰቶች "አጠቃላይ አመጽ" ሊቀሰቅሱ ይችላሉ በማለት አስጠንቅቋል።

3፤ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኩባንያ ሥራ አስፈጻሚ አንዋር ሶሳ በቀጣዩ ወር ከሃላፊነት እንደሚለቁ የኬንያው ሳፋሪኮም ኩባንያ አስታውቋል። አንዋር ሶሳ፣ ከሃላፊነታቸው የሚሰናበቱት በኢትዮጵያ የተመደቡበትን ሥራ በማጠናቀቃቸው እንደኾነ ኩባንያው ገልጧል። አንዋር ሶሳ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኩባንያ በኢትዮጵያ የቴሌኮም አገልግሎት መሠረቱን ከጣለ ጀምሮ በዋና ሥራ አስፈጻሚነት በማገልገል ላይ ናቸው።

4፤ የኤርትራ መንግሥት በኤርትራ የተመድ ልዩ ራፖርተር ያወጣውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሪፖርት አጣጥሏል። ኤርትራ፣ የልዩ ራፖርተሩ ሪፖርት መሠረታዊ ችግር ያለበት፣ የኤርትራ ጠላት ከኾኑ አገራት መረጃ የሰበሰበና ብሄራዊ የውትድርና አገልግሎት የግዳጅ ሥራ እንደኾነ አድርጎ በሃሰት የሚያጠለሽ ነው በማለት ከሳለች። የተመድ ሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት "ተቀባይነት የሌለውን" ሪፖርት ውድቅ እንዲያደርግና በሰብዓዊ መብቶች አጠባበቅ ዙሪያ መነጋገርን እንዲመርጥ ኤርትራ ጥሪ አድርጋለች። ልዩ ራፖርተሩ፣ ሰሞኑን ስብሰባ ላይ ላለው የተመድ ሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ሪፖርቱን አቅርቧል።
መረጃ ህይወት ነው፣ ይህንንም መረጃ ለጓደኞቻችሁ#Share በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ


t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
150 views04:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-21 20:41:33 በደብረ ኤልያስ በሚገኙ አራቱ ገዳማት ውስጥ አንድ መነኩሴ ብቻ መገኘታቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ ሥር ባሉ አራት ገዳማት ላይ በደረሰው ከፍተኛ ጉዳት፤ በገዳማቱ አንድ መነኩሴ ብቻ መገኘታቸውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስታውቃለች፡፡

በገዳማቱ ከግንቦት 18 እስከ 23/2015 ለተከታታይ አምስት ቀናት “የታጠቁ ኃይሎች በገዳሙ ውስጥ ይገኛሉ” በሚል በተደረገ ኦፕሬሽን እስካሁን ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ በርካታ መነኮሳት መሞታቸውን፤ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓበርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የገዳማት አሥተዳደር መምሪያ ኃላፊ መጋቤ ካህናት አባ ሀብተጊዎርጊስ አሥራት ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል፡፡

ኃለፊው አክለውም፤ በአራቱም ገዳማት አቢያተ ክርስቲያናት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን ለአዲስ ተናግረዋል፡፡ በዚህም በገዳሙ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች “ሕግ ማስከበር” ያሉትን ዘመቻ ከማካሄዳቸው በፊት በርካታ መነኮሳት እና አገልጋዮች ይኖሩ እንደነበር ገልጸው፣ የገዳማት አስተዳደር መምሪያው ወደ ሥፍራው ባቀናበት ወቅት የተገኙት አንድ መነኩሴ ብቻ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

“መሞታቸው ከታወቀው መነኮሳቱና አገልጋዮች ውጭ ሌሎቹ የት እንደገቡ አይታወቅም፡፡” ያሉት ኃላፊው፤ በገዳሙ ውስጥ ባለው ሰፊ የአትክልት እርሻ በርካታ ያልተቀበሩ አስከሬኖች መኖራቸውንና በአካባቢው ከፍተኛ የአስከሬን ሽታ መኖሩንም ተናግረዋል፡፡

የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች “በገዳሙ የታጠቁ ኃይሎች መሽገዋል” በሚል ኦፕሬሽን ቢያደርጉም፤ በተለያዩ ጊዜያት ሽፍታዎች የገዳሙን ንብረት ለመዝረፍ ወደ ሥፍራው ይመጡ ስለነበር፣ መነኮሳቱ ምሽግ ቆፍረው ንብረቱን ከዝርፊያ ለማዳን እና ሕይወታቸውንም ለመታደግ ጥረት ሲያደርጉ እንደነበር ኃላፊው ተናግረዋል፡፡

በተደረገው ዘመቻ ጉዳት የደረሰባቸው አቢያተ ክርስቲያናት የሥላሴ፣ ኪዳነምሕረት፣ የኤልያስ እና የጊዎርጊስ መሆናቸውን በመጥቀስ፤ አቢያተ ክርስቲያናቱ የውጭ ክፍላቸው ጨምሮ ቅኔ ማሕሌቱ፣ ቅድስቱ እና ቤተመቅደሱ ላይ የደረሰው ድብደባ እጅግ ከፍተኛ መሆኑንም አስረድተዋል።

“በተለይ በኪዳነምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ላይ የደረሰው ጉዳት ከኹሉም የከፋ ነው፡፡” ያሉት ኃላፊው፣ ንዋተ ቅድሳትን ጨምሮ የቤተ መቅደስ መገልገያዎች መውደማቸውን እና ጉልላቱም ተመትቶ መውደቁን ገልጸዋል።

አዲስ ማለዳ “በገዳማቱ ውስጥ ራሳቸውን “የኢትዮጵያ ዓለም ብርሃን” ብለው የሚጠሩ አካላት አሉ”” ተብሎ ስለሚነሳው ገዳይ ላነሳችላቸው ጥያቄም፤ “እነዚህ አካላት በትክክል በገዳሙ ውስጥ አሉ ለማለት ባያስደፍርም በአንዱ ቤተክርስቲያን ላይ የእነሱ አርማ ያለበት ሰንደቅ ዓላማ ታይቷል” ብለዋል።

አሁን ላይ በአራቱም አቢያተ ክርስቲያናት መንፈሳዊ አገልግሎት ሙሉ ለሙሉ መቋረጡንም ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡ የተጎዱትን አቢያተ ክርስቲያናት መልሶ ለመጠገን እና የጉዳት መጠኑን በሚገባ ለማወቅ በመንበረ ፓትርያርክ፣ ጠቅላይ ቤተ ክህነት እና አገረ ስብከቱ የጋራ ውይይት እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
መረጃ ህይወት ነው፣ ይህንንም መረጃ ለጓደኞቻችሁ#Share በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ


t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
173 views17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-21 20:14:13 ረቡዕ ምሽት! ሰኔ 14/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ለሌሎች አገራት አየር መንገዶች ያልከፈለውን 95 ሚሊዮን ዶላር የተከማቸ ዕዳ እንዲከፍል ዓለማቀፉ የአየር ትራንስፖርት ማኅበር በአዲስ አበባ እያካሄደው ባለው ስብሰባ ላይ ማሳሰቡን ሪፖርተር ዘግቧል። በመንግሥት ላይ የተከማቸው ዕዳ፣ ሌሎች አየር መንገዶች አዲስ አበባ ውስጥ በትኬት ሽያጭና ሌሎች አገልግሎቶች ያገኙት ብሄራዊ ባንክ በዓለማቀፍ ሕግ መሠረት ወደ ዶላር ቀይሮ ያልሰጣቸው ገቢያቸው ነው። መንግሥት ዕዳውን ለአየር መንገዶቹ ካልከፈለ፣ የአገሪቱ ዓለማቀፍ የአየር በረራ ግንኙነቶች ላይ ችግር ሊፈጥር እንደሚችል ማኅበሩ ማስጠንቀቁን ዘገባው ጠቅሷል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በበኩሉ፣ ኤርትራና ናይጀሪያን ጨምሮ የተወሰኑ አገራት ከትኬት ሽያጭና ሌሎች አገልግሎት ያገኘውን 180 ሚሊዮን ዶላር እንዳልለቀቁለት ገልጧል ተብሏል።

2፤ መንግሥት ለቀጣዩ በጀት ዓመት በራያና አካካቢው ለሚገኙ ሦስት ወረዳዎችና አንድ የከተማ አስተዳደር የመደበውን የፌደራል ድጎማ በጀት ለትግራይ ክልል እንዳይለቅ የሚጠይቅ የ145 ሺህ ሕዝብ ፊርማ ሰኞ'ለት ለፌደሬሽን ምክር ቤት መቅረቡን "ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ዘግቧል። ከአካባቢው ሕዝብ ፊርማውን አሰባስቦ ያቀረበው፣ የወሎ ራያ አማራ ማንነትና ወሰን አስመላሽ ኮሚቴ እንደኾነ ዘገባው አመልክቷል። ከሰሜኑ ጦርነት በፊት በሦስቱ ወረዳዎችና አንድ የከተማ አስተዳደር የሚኖረው ሕዝብ የማንነት ጥያቄ ሲያነሳ መቆየቱና ከጦርነቱ መቀስቀስ ጀምሮ ግን ሕዝቡ ራሱን በራሱ እያስተዳደረ መኾኑ በአቤቱታው ላይ ተገልጧል ተብሏል። ፌደሬሽን ምክር ቤትም አቤተታውን እመረምራለኹ ማለቱን ዘገባው ጠቅሷል።

3፤ ከፍትህ ሚንስቴር እና ፌደራል ፖሊስ የተውጣጣ ልዑካን ቡድን ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞች በሕገወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች አማካኝነት ወደ ጅቡቲ የሚገቡባቸውን መተላለፊያዎች ተዘዋውሮ መመልከቱን በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ በትዊተር ገጻቸው ገልጸዋል። ልዑካን ቡድኑ፣ የጎበኛቸው የሕገወጥ ፍልሰተኞች መተላለፊያዎች፣ "ኦቦክ" እና በቀይ ባሕር በኩል ወደ መካከለኛው ምሥራቅ በጅልባ መውጫ የኾነው "ፋንታሂሮ" የተባለ ቦታ እንደኾኑ አምባሳደሩ ጠቅሰዋል። ልዑካን ቡድኑ፣ ከአካባቢው የጅቡቲ አስተዳዳሪዎችና ከዓለማቀፉ የፍልሰት ድርጅት ሃላፊዎች ጋር በኢትዮጵያዊያን ሕገወጥ ፍልሰት ዙሪያ መወያየቱም ተገልጧል።

4፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው አየር መንገዱቸው በኪሳራ የተነሳ ለበርካታ ዓመታት በረራ ያቋረጠውን የናይጀሪያ አየር መንገድ በቀጣዩ ዓመት ጥቅምት እንደገና ወደ በረራ ለመመለስ ብርቱ ጥረት እያደረገ መኾኑን ለኢዜአ ተናግረዋል። አየር መንገዱ ባለፈው ወር የናይጀሪያ አየር መንገድን በረራ ለማስጀመር፣ አንድ የራሱን ቦይንግ አውሮፕላን ወደ ናይጀሪያ ልኮ ነበር። ኾኖም የናይጀሪያ ሲቪል አቬሽን በአዲስ መልክ ለተዋቀረው አየር መንገድ የበረራ ፍቃድ ባለመስጠቱና የናይጀሪያ የግል አየር መንገዶች የመሠረቱበት ክስ ባለመቋጨቱ፣ በረራው ሳይጀመር መቅረቱ ይታወሳል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንደገና በተዋቀረው የናይጀሪያ አየር መንገድ ውስጥ 49 በመቶ ድርሻ የያዘ ሲኾን፣ የናይጀሪያ መንግሥት 5 በመቶ እንዲኹም ናይጀሪያዊያን ባለሃብቶች ቀሪውን ድርሻ ይዘዋል።

5፤ የኢትዮጵያ ወታደሮች አልሸባብ ዛሬ በኢትዮጵያና ሱማሊያ የጋራ ወታደራዊ ጦር ሠፈር ላይ ባደረሰው የአጥፍቶ ጠፊ ጥቃት 5 ወታደሮች እንተገደሉና በርካቶች እንደቆሰሉ የሱማሊያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የቡድኑ አጥፍቶ ጠፊዎች በወታደራዊ ጦር ሠፈሩ ላይ ጥቃት የፈጸሙት፣ ከጦር ሠፈሩ 100 ሜትር ርቀት ላይ ፈንጂዎችን በማፈንዳት እንደነበር ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። የፈንጂ ፍንዳታውን ተከትሎ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ የቡድኑ ታጣቂዎች ተገድለዋል ተብሏል። አልሸባብ በድንበር አካባቢ ከሳምንት በፊት በኢትዮጵያ ወታደራዊ ጦር ሠፈር ላይ ተመሳሳይ ጥቃት ለማድረስ ሞክሮ ሳይሳካለት እንደቀረ ይታወሳል።

6፤ ዛሬ ጧት ዋሽንግተን የገቡት የሱማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሐመድ ዛሬ ከአሜሪካ መከላከያ ሚንስትር ኦስቲን ሎይድ ጋር በኹለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚወያዩ ፔንታጎን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ፕሬዝዳንት ሞሐመድ ከዚያም ወደ ኒውዮርክ በማቅናት፣ የተመድ ጸጥታው ምክር ቤት በሱማሊያ ወቅታዊ ጸጥታ ላይ በሚያካሂደው ልዩ ስብሰባ ላይ ንግግር እንደሚያደርጉና ጸጥታው ምክር ቤት በሱማሊያ ላይ የጣለውን የጦር መሳሪያ ማዕቀብ ሙሉ በሙሉ እንዲያነሳ እንድንጠይቁ ይጠበቃል። ጸጥታው ምክር ቤት፣ በሱማሊያ ላይ ልዩ ስብሰባ እንዲቀመጥና ፕሬዝዳንት ሞሐመድ ንግግር እንዲያደርጉ የጋበዘቻቸው የጸጽታው ምክር ቤት የወቅቱ ሊቀመንበር የተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች ናት።

7፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ5114 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ6016 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 66 ብር ከ4317 ሳንቲምና መሸጫው 67 ብር ከ7603 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ59 ከ5592 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ60 ብር ከ7504 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል።
መረጃ ህይወት ነው፣ ይህንንም መረጃ ለጓደኞቻችሁ#Share በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ


t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
174 views17:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-21 13:05:51 የቀድሞዋ አፈጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም መረጃ በማጥፋታቸው የራያ አላማጣ የማንነት ጥያቄ እንዲጓተት ምክንያት ሆኗል ተባለ

የራያ አላማጣ ማህበረሰብ የማንነት ጥያቄ እልባት እንዲሰጠው በሚል ለፌዴሬሽን ምክር ቤት የላከው ደብዳቤ በቀድሞ የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም አማካኝነት እንዲጠፋ ተደርጓል ተብሏል።

የአላማጣ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ሞገስ እያሱ፤ የራያ አላማጣ የማንነት እና የበጀት ጥያቄ ከ2011 ጀምሮ ለፌደሬሽን ምክርቤት ሲቀርብ እንደነበር ገልጸው፤ “የወቅቱ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ኬሪያ ኢብራሂም የማንነት ጥያቄውን ለማዳፈን በማሰብ ለምክር ቤቱ የገባው መረጃ እንዲጠፋ አድርገዋል፡፡” ሲሉ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል።

በዚህም ለምክር ቤቱ የገባው መረጃ እንዲጠፋ መደረጉ፤ የራያ አላማጣ ማህበረሰብ የማንነት ጥያቄ መፍትሄ ሳያገኝ ለአራት ዓመታት እንዲጓተት ምክንያት ሆኗል ነው ያሉት።

“አፈጉባኤዋ ስልጣን ከለቀቁ በኋላ በገባው ደብዳቤ መሰረት የማንነት ጥያቄው መልስ እንዲያገኝ የፌዴሬሽን ምክር ቤቱን ስንጠይቅ፤ መረጃው መጥፋቱ ስለተነገረን ቅጂውን በድጋሜ ለማስገባት ተገደናል፡፡” ሲሉ ጠቁመዋል።

ባሳለፍነው ሰኞ ሰኔ 12/2015 የራያ አላማጣ እና ባላ አካባቢዎች በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ ከ150 ሺሕ በላይ የሕዝብ ፊርማ ተሰብስቦ ለፌደሬሽን ምክር ቤት መግባቱን የጠቀሱት ኃላፊው፤ “ዋና ዓላማውም የማንነት ጥያቄያችን ተፈቶ ወደ አማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን እንድንካተትና በጀቱ በትግራይ ክልል ሳይሆን በአማራ ክልል በኩል እንዲለቀቅልን ነው፡፡” ብለዋል።

አክለውም፤ በተለይ የፌደራል ተቋማት በአካባቢው የተሟላ አገልግሎት እየሰጡ ባለመሆኑ፣ ከባንክ፣ ከኤሌክትሪክና ከኢንተርኔት ጋር ያለው አገልግሎት በቶሎ ምላሽ ሊስጠው እንደሚገባ ጠቁመዋል።

ለዚህም አራት ዓመታትን ያስቆጠረው የራያ አላማጣ የማንነት እና የበጀት ጥያቄ መልስ እንዲያገኝ ኮሚቴ ተቋቁሞ፤ ሰኞ ሰኔ 12/2015 ለፌድሬሽን ምክር ቤት መግባቱ ነው የተገለጸው።

ሕወሓት ለራያ እና አላማጣ አካባቢዎች አመራር መድቧል በሚል የሚነሳውን ጉዳይ በተመለከተም መድቧል ከተባለበት ጊዜ ጀምሮ አምስት አመራሮችን የቀያየረ መሆኑን ጠቁመው፤ “ወደ ራያ እና አላማጣ ግን ሊመጡ አይችሉም፡፡” ሲሉ ተናግረዋል።

ራያ አላማጣ ለኹለት ዓመታት ያለ በጀት መቆየቱን የገለጹት ኃላፊው፤ የማንነት ጥያቄው እና ለኹለት ዓመት የተቋረጠው በጀት በአስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጠው ህዝቡ በተደጋጋሚ በመጠየቅ ላይ መሆኑን ጠቁመዋል።

አዲስ ማለዳ በጉዳዩ ላይ ከፌደሬሽን ምክር ቤት ፅሕፈት ቤት ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት ጥረት ብታደርግም ሳይሳካ ቀርቷል።

በተያያዘም፤ በዛሬው ዕለት የአላማጣ ከተማ ነዋሪዎች ''መንግሥት የማንነት ጥያቄቸውን ሕጋዊ እንዲያደርግላቸው'' በሰላማዊ ሰልፍ የጠየቁ ሲሆን፤ ነዋሪዎቹ በሰላማዊ ሰልፉ “አማራ ነን እንጂ አማራ እንሁን አላልንም”፣ “የፌደራል መንግሥት ተቋማት ዲስትሪክት ወደ ሰሜን ወሎ ዞን ይዛወሩልን”ና ሌሎች የተለያዩ መፈክሮችን ማሰማታቸውን የሰሜን ወሎ ዞን ኮሙኒኬሽን አስታውቀል።
መረጃ ህይወት ነው፣ ይህንንም መረጃ ለጓደኞቻችሁ#Share በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ


t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
190 views10:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-21 12:58:46
የቀድሞ አስረኛ ክፍል ተማሪዎች ከመጭው ዓመት ጀምሮ የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል ትምህርታቸውን መከታተል የሚችሉበት እድል መመቻቸቱ ተገለጸ

በቀድሞው ስርዓተ ትምህርት አስረኛ ክፍል ያጠናቀቁ ተማሪዎች፤ በ2016 የትምህርት ዘመን በማንኛውም ትምህርት ቤት በመግባት የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ትምህርታቸውን በመደበኛ ትምህርት መቀጠል እንደሚችሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አስታውቋል።

የሥራና ክህሎት ሚኒስተር የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ዘርፍ ሚኒስተር ዴኤታ አማካሪ አዝመራ ከበደ፤ “በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት የቀድሞው የአስረኛ ክፍል ተማሪዎች የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል ትምህርታቸውን መቀጠል ይችላሉ፡፡” ብለዋል።

የተግባረ ዕድ ትምህርት ቤት ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዲን አንተነህ ሙሉ በበኩላቸው፤ የቀድሞው አስረኛ ክፍል ተማሪዎች በዲፕሎማ የሚሰጡ ማንኛውንም አይነት ትምህርቶችን መከታተል ይችሉ እንደነበር ጠቁመው፤ ከዚህ በኋላ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የአስረኛ ክፍል የምስክር ወረቀት ያላቸውን ተማሪዎች እንደማይቀበሉ ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል።

ከመጭው ዓመት ጀምሮ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛዎች 12ኛ ክፍልን ያጠናቀቁ ተማሪዎችን ብቻ፣ ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በሚያወጣው መቁረጫ ነጥብ መሰረት እንደሚቀበሉም ጠቁመዋል።

ተማሪዎቹ በመደበኛው 11 እና 12ኛ ክፍልን ከመማር በተጨማሪም፤ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መምሪያ መሰረት አጫጭር ስልጠናዎችን መውሰድ እንደሚቸሉም ገልጸዋል፡፡

በቀድሞው ስርዓተ ትምህርት አስረኛ ክፍል አጠናቀው የብሔራዊ ፈተና ማለፊያ ውጤት ያላመጡ ተማሪዎች፤ ወደ ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት በመግባት በዲፕሎማ የሚሰጡ ትምህርቶችን መከታተል ይችሉ እንደነበር ይታወሳል።ሼር አድርጉ

t.me/emsmereja
186 views09:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-21 07:33:51
ባሳለፍነው ቅዳሜ ጠዋት ከደብረጉራች ከፍ ብሎ በአሊዶሮ በታጣቂዎች ከታፈኑ ከ40 በላይ ሾፌሮች መካከል

ከደ/ማርቆስ:-
1ኛ) ጌታቸው
2ኛ) እሙየ አጥናፉ
3ኛ ) አካሉ መራ

ከ#አማኑኤል :-
4ኛ) ተመስገን አስሬ
5ኛ) አብርሀም አንለይ
6ኛ) ሞላ አማኑኤል /ወርቅማ /

ከአዲስ ቅዳም:-
7ኛ) አቢዎት አዳሙ (ጎባው)
8ኛ) አዲሱ የሻለም
9ኛ) ፋሲካው አማረ
10ኛ) ደዊት ልመንህ(አብዲሌ)
11ኛ) ሰለሞን ማሩ
12ኛ) ምናየ

ከደጀን ከተማ
13ኛ) ውዱ

ከሉማሜ :-
14ኛ) ይሁኔ በላቸው
ከወጀል
15ኛ) ኢብራሂም
ረዳት ከደጀን ዙሪያ/ጉብያ/ ነዋሪ የሆኑት(ወንድማማቾች)
16ኛ) ፀገየ አስናቀ እና
17ኛ) ምንይለዋል አስናቀ ከታገቱት ውስጥ ይገኙበታል።
አጋቾቹ ለቤተሰቦቻቸው እየደወሉ አንድ ሚሊየን ካላመጣችሁ እንገድላቸዋለን እያላቸው ነው።
የሚመለከተው የመንግሥት አካል እና የፀጥታ አካላት ዝምታን መምረጣቸው ያሳዝናል። ሼር አድርጉላቸው
መረጃ ህይወት ነው፣ ይህንንም መረጃ ለጓደኞቻችሁ#Share በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ


t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
203 views04:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-20 22:35:06
ስሜ ሜላት ይባላል፡፡ 27 አመቴ ነው አ.አ cmc ነው የምኖረው፣
በዚህ
ሳምንት የገጠመኝን
እውነተኛ የወሲብ ታሪኬን ላካፈላቹ፣
በዚህ ሊንክ ያንብቡ
t.me/yesextarikoch
t.me/yesextarikoch
t.me/yesextarikoch
262 views19:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-20 12:54:38
እስከ ሰኔ 30 ድረስ የቤት ኪራይ መጨመርም ሆነ ተከራይ ማስወጣት አይቻልም ተብሏል
በመዲናዋ አዲስ አበባ “ከጣሪያ እና ግድግዳ ግብር ጋር በተያያዘ አንዳንድ አከራዮች በተከራዮች ላይ የዋጋ ጭማሪ እያደረጉ መሆኑን” ደርሼበታለሁ ሲል የከተማዋ አስተዳደር አስታውቋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ የካቲት 30/2015 ባደረገው ውይይት ማንኛውም አከራይ የቤት ኪራይ እስከ ሰኔ 30 /2015 ድረስ መጨመር የማይቻል መሆኑን መወሰኑ ይታወሳል።

በመሆኑም በውሳኔው መሰረት ማንኛውም አከራይ የቤት ኪራይ እስከ ሰኔ 30 /2015 ድረስ መጨመርም ሆነ ተከራይ ማስወጣት የማይቻል መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አሳስቧል።
መረጃ ህይወት ነው፣ ይህንንም መረጃ ለጓደኞቻችሁ#Share በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ


t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
250 views09:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-20 12:22:07 በሰሜን ሸዋ በርካታ ቁጥር ያላቸው አሽከርካሪዎችና ተሳፋሪዎች በኦነግ ‹‹ሸኔ›› ታፈነው መወሰዳቸው ተሰማ

ማክሰኞ ሰኔ 13 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ኩዩ ወረዳ ገርበ ጉራቻ ከተማ፤ ቅዳሜ ዕለት ሰኔ 10/2015 ከጠዋቱ 12 ሰዓት አካባቢ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ከባድ መኪና እና የሕዝብ ትራንሰፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎችን በማገት በርካታ አሸከርካሪዎችንና ተሳፋሪዎች አፍነው መወሰዳቸውን አዲስ ማለዳ ከአካባቢው ነዋሪዎች ሰምታለች።

ለእገታ የተዳረጉት የኹሉም ተሽከርካሪዎች አሽከርካሪዎችና ተሳፋሪዎች ከክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች እና ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ ጉዞ በማድረግ ላይ የነበሩ ናቸው ተብሏል።

በዕለቱም ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው እና በመንግሥት ኦነግ ሸኔ ተብሎ በአሸባሪነት የተፈረጀው ታጣቂ ቡድን ከገርበ ጉራቻ ከተማ ወጣ ብሎ ልዩ ሥሙ ኡላ በተባለ ቦታ መንገድ በመዝጋት መኪኖቹን ካስቆመ በኋላ፤ ለጊዜው ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ በርካታ ሰዎችን ወስዶ ከስፍራው መሰወሩን ነው ነዋሪዎች የተናገሩት፡፡  

ነዋሪዎቹ አክለውም፤ ታጣቂ ቡድኑ በአካባቢው በተደጋጋሚ መሰል ተግባራትን ማድረጉ የተለመደ ቢሆንም፣ የአሁኑ ለየት የሚያደርገው በቁጥር ብዙ የሆኑ ሰዎችን አፍኖ መውሰዱ እና ሌላ ጊዜ ሌሊት ላይ የሚያደርገውን ተግባር በቀን መፈጸሙ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡

እንዲሁም ድርጊቱ በተፈጸመበት አካባቢ የአገር መከላከያ ሰራዊት ካምፕ በኩዩ ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኝ ቢሆንም፤ “ከበላይ አካል ትዕዛዝ አልተቀበልንም” በማለት ሰዎቹን ሊታደጓቸው አለመቻላቸው ነው የተገለጸው፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታ ከአንድ ሳምንት በፊት በፊቼ ከተማ መውጫ ላይ በተለምዶ ገንደ ጉዳ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ከሚገኘው የመከላከያ ሰራዊት ካምፕ በቅርብ ርቀት ላይ ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች በታጣቂ ቡድኑ ታፍነው መውሰዳቸው ተነግሯል።

የአካባቢው ማህበረሰብ በታጣቂ ቡድኑ በተደጋጋሚ በሚደርስበት ጥቃት የስነልቦና ድቀት እንዲሁም በሰው ሕይወትና በንብረት ከፍተኛ ጉዳት እያስተናገደ ነውም ብለዋል።

በታገቱ ሹፌሮች ቁጣ፣ በትናንትናው ዕለት በአማራ ክልል ከደብረ ማርቆስ ወደ ደንበጫ የሚወስደው መንገድ ከረፋድ ጀምሮ ዝግ መሆኑ አዲስ ማለዳ መዘገቧ ይታወሳል።

የታገቱ አሽከርካሪዎችን ለመልቀቅ አጋቾች ለአንድ ሰው ከ500 ሺሕ እስከ አንድ ሚሊዮን ብር እየጠየቁ መሆኑም ተነግሯል።

አዲስ ማለዳ ከአሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሠላምና ጸጥታ መምሪያ የሥራ ኃላፊዎች ምላሽ ለማግኘት ጥረት ብታደርግም ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሳይሳካ ቀርቷል።
መረጃ ህይወት ነው፣ ይህንንም መረጃ ለጓደኞቻችሁ#Share በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ


t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
225 views09:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-20 12:22:07 የኤርትራ ሰራዊት ለሽረ ዕደስላሴ አዋሳኝ በሆኑት በሽራሮ እና ማይፀብሪ አካባቢዎች ተደጋጋሚ ትንኮሳ እያደረሰ እንደሚገኝ ተገለጸ

ለሽረ ዕደስላሴ አዋሳኝ በሆኑት በሽራሮ እና ማይፀብሪ አካባቢዎች በኤርትራ ሰራዊት ተደጋጋሚ ትንኮሳ እየደረሰ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡

ሰራዊቱ ከሽራሮ 17 ኪሎ ሜትር ድረስ ተቆጣጥሮ በመያዝ በርካታ ግፎችን በትግራይ ሕዝብ ላይ እየፈጸመ እንደሚገኝ ተነግሯል፡፡ የሽረ እዳስላሴ ከተማ ምክትል ከንቲባ ተፈሪ ሀይለመለኮት ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት፤ የኤርትራ ሰራዊት ከፍተኛ ትንኮሳ በየቀኑ እንደደሚፈፅማባቸው አስታውቀዋል፡፡

የኤርትራ ሰራዊት በባድመ፣ ገምሀሎ እና በሽራሮ በኩል 17 ኪሎ ሜትር ድረስ በመዝለቅ ከብቶች የመዝረፍ፣ የመግደል እና ለእርሻ የተሰማሩ ሰዎች የመግድል እንቅስቃሴ አሁንም ተባብሶ እንደቀጠለም የተናገሩ ሲሆን፤ በማይፀበሪም በተለያዩ አከባቢዎች ከፍተኛ የሆነ ትንኮሳ እየደረሰበት እንደሚገኝ ምክትል ከንቲባው አስረድተዋል።

ህብረተሰቡ በዚህ ድርጊት በከፍተኛ ሁኔታ የተማረረ መሆኑንም በመግለጽ፤ አሁንም ድረስ በሚድርስበት ጥቃት ክፉኛ እንደተጎዳ ተናግረዋል።

የክልሉ መንግሥት በሰላም ስምምነቱ ላይ ባለው አመኔታ ነገሮችን በትዕግስት እያለፈ እንደሚገኝም ምክትል ከንቲባው ጨምረው ገልጸዋል፡፡
መረጃ ህይወት ነው፣ ይህንንም መረጃ ለጓደኞቻችሁ#Share በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ


t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
211 views09:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ