Get Mystery Box with random crypto!

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ) Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ)
የሰርጥ አድራሻ: @zemedkun_zemede
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.26K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-04-19 19:51:17 ረቡዕ ምሽት! ሚያዝያ 11/2015 ዓ.ም የEMS Mereja ዐበይት ዜናዎች

1፤ የተመድ ዋና ጸሃፊ አንቴኒዮ ጉተሬዝ ባለፈው የካቲት ወደ ኢትዮጵያ በሄዱ ጊዜ ትግራይን እንዳይጎበኙ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ደመቀ ቀደም ብለው በጻፉላቸው ደብዳቤ እንደተከለከሉ ዋሽንግተን ፖስት ከአሜሪካ መንግሥት ካፈተለኩት ሚስጢራዊ የስለላ መረጃዎች ተመልክቻለሁ ሲል አስነብቧል። መንግሥት ጉተሬዝ ትግራይን እንዲጎበኙ ባለመፍቀዱ፣ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ይቅርታ እንደጠየቋቸው ጉተሬዝ ለተመድ ባለሥልጣናት ስለመናገራቸው ዘገባው ጠቅሷል። ጉተሬዝ የጉብኝት እቅዳቸውን መከልከላቸውን እንዳወቁ፣ ቅሬታቸውን በተመድ ለኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ለመግለጽ ፈልገው እንደነበር ተገልጧል።

2፤ የብሄራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምኅረቱ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሃ ግብር ከዓለም ገንዘብ ድርጅትና ዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ ውጭም ቢኾን ይቀጥላል ሲሉ በአሜሪካው ሀርቫርድ ዪኒቨርሰቲ ባደረጉት ንግግር ላይ መግለጣቸውን ሪፖርተር አስነብቧል።
አሜሪካ የሚገኘው የመንግሥት ልዑካን ቡድን በከፍተኛ የዕዳ ጫና፣ የኑሮ ውድነት፣ ያልተመጣጠነ የውጭ ምንዛሬና የውጭ ብድር ዙሪያ ከሁለቱ ተቋማት ጋር እየተነጋገረ ስለመኾኑ ማሞ መጥቀሳቸውን ዘገባው አመልክቷል። ማሻሻያዎቹ በመንግሥት አገር በቀል የኢኮኖሚ መርሃ ግብር ማዕቀፍ እንደሚከናወኑ ማሞ እንደገለጡ ያመለከተው ዘገባው፣ ኾኖም ማሻሻያዎቹን በተሟላ አኳኋን ለመተግበር የውጭ ድጋፍ ያስፈልገናል ማለታቸውን ጠቅሷል። ማሞ ይህን የተናገሩት፣ እሳቸውና ገንዘብ ሚንስትር አሕመድ ሽዴ የመሩት ልዐካን ቡድን በዓለም ባንክና የዓለም ገንዘብ ድርጅት ስብሰባ ላይ ባለፈው ሳምንት ከተካፈለ በኋላ ነው።

3፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ዛሬ የግጭት ቀጠና ኾኖ በከረመው ምሥራቅ ወለጋ ዞን በነቀምት ከተማ ጉብኝት ማድረጋቸውን የጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤት በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል። ዐቢይ በነቀምት ቆይታቸው፣ ከከተማዋ ነዋሪዎች ጋር መወያየታቸው የተገለጠ ቢኾንም፣ ስለ ጉብኝቱ ዓላማና ስለ ውይይቱ ጽሕፈት ቤቱ ዝርዝር መረጃ አልሰጠም። ከዐቢይ ጋር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሠ ጫፎ እና የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ በጉብኝቱ ላይ ተሳትፈዋል ተብሏል።

4፤ በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የክልሉ ትምህርት ቢሮ በመጭው ሚያዝያ 23 የመማር ማስተማር ሥራ ይጀምራሉ ማለቱን የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል። በዕለቱ ትምህርት የሚጀምሩት፣ በክልሉ የሚገኙ ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍሎች የሚያስተምሩ ትምህርት ቤቶች በሙሉ እንደኾኑ ዘገባው አመልክቷል።

5፤ ጀኔራል ሞሐመድ ደጋሎ የሚመሩት የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት ዛሬ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ የሚጸና የ24 ሰዓት ተኩስ አቁም ለማድረግ ዝግጁ መኾኑን ከቀትር በኋላ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ጀኔራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን የሚመሩት የሱዳን ጦር ሠራዊት ግን፣ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ ስለ ተኩስ አቁም ጥሪው ምላሽ እንዳልሰጠ ታውቋል። ሁለቱ ተፋላሚ ወገኖች የ24 ሰዓት ተኩስ አቁም ለማድረግ ትናንት በተናጥል የደረሱበት ውሳኔ ተግባራዊ ሳይኾን ቀርቷል። ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊቱ ሙሉ ተኩስ አቁም ለማድረግ ዝግጁ መኾኑንም በትዊተር ገጹ ገልጧል።

6፤ ኢጋድ ለሱዳኑ ግጭት ሰላማዊ መፍትሄ ለማፈላለግ የሰየማቸው የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ፣ የጅቡቲው ፕሬዝዳንት እስማዔል ጌሌ እና የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ዛሬ ካርቱም ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል። ዛሬ አምስተኛ ቀኑን በያዘው የሱዳን ጦር ሠራዊትና ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት ግጭት 270 ሰዎች እንደተገደሉና ከ2 ሺህ 500 በላይ ሰዎች እንደቆሰሉ የውጭ ዜና ምንጮች የዓለም ጤና ፕሮግራምን ጠቅሰው ዘግበዋል። በርካታ የካርቱም ነዋሪዎች ግጭቱን በመሸሽ፣ ከተማዋን ለቀው እየወጡ መኾኑን ዘገባዎች አመልክተዋል። ዛሬ በካርቱም የከባድ መሳሪያ ውጊያ እየተካሄደ ያለው፣ በዋናነት በጦር ሠራዊቱ ጠቅላይ መምሪያና አውሮፕላን ማረፊያው ውስጥ እንደኾነ ተገልጧል።

7፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ0679 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ1493 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 64 ብር ከ2123 ሳንቲም እና መሸጫው 65 ብር ከ4974 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ59 ብር ከ3449 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ60 ብር ከ5318 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
ለማስታወቂያ ስራና ለመረጃ ጥቆማዎች @infoetrobot ይህን ይጠቀሙ
120 views16:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 06:33:19 ረቡዕ ማለዳ! ሚያዝያ 11/2015 ዓ.ም የEMS Mereja ዐበይት ዜናዎች

1፤ በሱዳን የኢትዮጵያ ኢምባሲ በሱዳን ጦር ሠራዊትና በፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት ውጊያ ከተገደሉት ሰላማዊ ሰዎች መካከል ኢትዮጵያዊያን እንደሚገኙበት መረጃዎች ደርሰውኛል ሲል በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል። ኾኖም ኢምባሲው እስከ ትናንት ባገኘው መረጃ ስንት ኢትዮጵያዊያን በግጭቱ ሕይወታቸውን እንዳጡ አልገለጠም። ዶይቸቨለ ግን፣ ካርቱም ውስጥ አራት ወይም አምስት ኢትዮጵያዊያን በከባድ መሳሪያ ፍንጣሪ እንደተገደሉ ከዓይን ምስክሮች መስማቱን ጠቅሶ ዘግቧል።

2፤ የሩሲያው የግል ወታደራዊ ኩባንያ ዋግነር ግሩፕ ሱዳን ውስጥ ቅጥረኛ ተዋጊዎቼን እንዳላሠማራ መናገሩን የውጭ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ኩባንያው ካለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህ በሱዳን ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ የለኝም ማለቱን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ከሩሲያ መንግሥት ጋር ግንኙነት እንዳለው የሚነገርለት ወታደራዊ ኩባንያው፣ በተለይ ከሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት አዛዥ ጀኔራል ሞሐመድ ደጋሎ ጋር በቅርብ እንደሚሠራ ሲነገር ቆይቷል።

3፤ የሱዳን ጦር ሠራዊት እና ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት የ24 ሰዓት ተኩስ አቁም ለማድረግ ትናንት ምሽት የደረሱበት የ24 ሰዓት ተኩስ አቁም ስምምነት ሙሉ በሙሉ እንዳልተከበረ የተለያዩ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ተኩስ አቁሙ ትናንት ምሽት ከ12:00 ሰዓት ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚኾን ተጠብቆ ነበር። የተመድ የዕርዳታ ማስተባበሪያ ቢሮ ሃላፊ ማርቲን ግሪፊትስ፣ በግጭቱ በረድዔት ሠራተኞች ላይ የጾታ ጥቃት እየተፈጸመ ስለመኾኑ መናገራቸውን ዘገባዎች አመልክተዋል። ከሁለቱ ተፋላሚ ወገኖች ማን ወታደራዊ የበላይነት እንደያዘ እስከ ትናንት ድረስ አልታወቀም።

4፤ ቦይንግ ኩባንያ ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖቹን በከፍተኛ መጠን ለማምረት የያዘውን ዕቅድ እንደሚገፋበት መግለጡን ብሉምበርግ ዘግቧል። ኩባንያው ይህን አቋሙን የገለጠው፣ የታዘዛቸውን 737 ማክስ አውሮፕላኖች የኋለኛው ክፍል ተገጣጣሚዎች ላይ እክል እንዳጋጠመውና አዲስ አውሮፕላኖችን በታቀደው ጊዜ ለደንበኞቹ ለማስረከብ ከፍተኛ የጊዜ መዘግየት እንደሚያጋጥመው በተናገረ ማግስት ነው። ኩባንያው፣ የመገጣጠሚያ እክል ባለባቸው ባለፉት አራት ዓመታት በተመረቱ ከ550 እስከ 800 የሚገመቱ አውሮፕላኖች ላይ እንደገና ፍተሻ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ገልጧል።

5፤ ጃፓን በሒሮሺማ ከተማ ከቀጣዩ ግንቦት 11 እስከ 13 በምታስተናግደው የቡድን-7 የበለጸጉ አገሮች ጉባኤ ላይ ደቡብ አፍሪካን ሳትጋብዝ ቀርታለች። ጃፓን በደቡብ አፍሪካ ፋንታ አፍሪካ ኅብረትን እንደጋበዘችና የኅብረቱ የወቅቱ ሊቀመንበር የኮሞሮሱ ፕሬዝዳንት አዛሊ አሱማኒ ኅብረቱን ወክለው እንደሚገኙ "ኒውስ 24" ዘግቧል። ደቡብ አፍሪካ በቡድን-7 ስብሰባ ላይ ለበርካታ ዓመታት ስትጋበዝ ነበር። ደቡብ አፍሪካ በዩክሬኑ ጦርነት ድጋፏን ለሩሲያ ሰጥታለች የሚል ውግዘት ከምዕራባዊያን አገራት ሲቀርብባት መቆየቱ ይታወሳል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
ለማስታወቂያ ስራና ለመረጃ ጥቆማዎች @infoetrobot ይህን ይጠቀሙ
223 views03:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 20:47:30
በሬ በነፃ
40 ሺ ብር የወጣበት ሰንጋ 53ሺ ብር ሚያወጣ ወርቅ ሆዱ ውስጥ ተገኘ።
በአርሲ ዞን ጢዮ ወረዳ ዶንሾ ቀበሌ  ለበዓል  ከታረደ ሰንጋ ሆድ ውስጥ   18.5  ግራም ወርቅ  ተገኝቷል።   ለባለቤቶቹ  53 ሺ ብር  ገቢ  አስገኝቶ ከወጣበት በላይ አስገቷል ተብሏል።

ይህ ነገር በሳይንስ እንዴት ይታያል ለሚለው ጥያቄ በኦሮሚያ ግብርና ቢሮ አሰላ የሚገኘው የእንስሳት ጤና ጥበቃ ማዕከላዊ የእንስሳት ጤና ጥበቃ የእንስሳት ሐኪም ዘሰጡት አስተያየት።

"በረሃማ አካባቢ የሚኖሩ ከብቶች ትንንሽ ማዕድናት ያላቸውን ተክሎች ስለሚመገቡ ከቆይታ ብዛት ወደ  ወርቅ ይለወጣል. ብለዋል ። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
ለማስታወቂያ ስራና ለመረጃ ጥቆማዎች @infoetrobot ይህን ይጠቀሙ
268 views17:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 20:02:47 ማክሰኞ ምሽት! ሚያዝያ 10/2015 ዓ.ም የEMS Mereja ዐበይት ዜናዎች

1፤ የተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ትጥቅ የሚፈቱ የቀድሞ ተዋጊዎችንና ታጣቂዎችን የመመዝገብና ወደ ማዕከሎች የማስገባት ሥራ በቀጣዩ ሰኔ እንደሚጀምር ማስታወቃቸውን ፋና ብሮድካስት ዘግቧል። ኮሚሽኑ የቀድሞ ተዋጊዎች ትጥቅ ፈትተው እንደጨረሱ ዋናውን ሥራውን እንደሚጀምር የገለጡት ኮሚሽነሩ፣ ኮሚሽኑ ተልዕኮውን ለመወጣት የኹለት ዓመት ዕቅድ አዘጋጅቷል ማለታቸውን ዘገባው አመልክቷል። ከ250 ሺህ እስከ 300 ሺህ የሚገመቱ የቀድሞ ተዋጊዎችንና ታጣቂዎችን መልሶ ለማቋቋም 550 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግም ኮሚሽነር ተሾመ ተናግረዋል ተብሏል።

2፤ አምነስቲ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት በአማራ ክልል በቅርቡ ከተቀሰቀሰው ሁከት ጋር በተያያዘ የታሠሩ ሰባት የመገናኛ ብዙኀን ሠራተኞችን ባስቸኳይ ከእስር እንዲለቁ አዲስ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። አምነስቲ፣ ባለሥልጣናቱ ባንዲት አንስት ጋዜጠኛ ላይ ተፈጸመ የተባለውን አካላዊ ጥቃትም እንዲያጣሩ ጠይቋል። መንግሥት "የኹሉንም ዜጎች ሃሳብን የመግለጽና ሰላማዊ ተቃውሞ የማድረግ መብት" እንዲያከብርም አምነስቲ ጥሪ አድርጓል። ድርጅቱ፣ በአማራ ክልል በቅርቡ የተደረጉ የተኩስ ልውውጦችና ሁለት ረድኤት ሠራተኞች በክልሉ ውስጥ መገደላቸውም እንዳሳሰበው ገልጧል።

3፤ የሱዳን ጦር ሠራዊትና ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን ያቀረቡትን ጥሪ በመቀበል የ24 ሰዓት ተኩስ አቁም ለማድረግ በተናጥል ፍቃደኛነታቸውን መግለጣቸውን የዓረብ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ሁለቱ ተፋላሚ ወገኖች የ24 ሰዓት ተኩስ አቁም እንዲያውጁ ጥሪ የቀረበላቸው፣ ቁስለኞችን ለማሸሽና ችግር ላይ ላሉ ወገኖች ሰብዓዊ ዕርዳታ ለማቅረብ እንዲቻል ነው። የ24 ተኩስ አቁም ለማድረግ ዝግጁ መኾኑን ቀድሞ ያሳወቀው፣ የጀኔራል ሞሐመድ ደጋሎ ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት ነበር። ኾኖም ተኩስ አቁሙ ከመቼ ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚኾን ዘገባዎቹ አልገለጡም። የሱዳን ሐኪሞች ማኅበር፣ በግጭቱ እስከዛሬው ዕለት ድረስ 144 ሰላማዊ ሰዎች ተገድለዋል ማለቱን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።

4፤ የተለያዩ አገራት ሱዳን የሚገኙ ዜጎቻቸው ደኅንነት እንዳሳሰባቸው በመግለጽ ላይ ናቸው። ኬንያ ግጭቱ ያስከተለው ሰብዓዊ ቀውስ ከተባባሰ 30 ሺህ ዜጎቿን ከአገሪቱ የሚያስወጣ ግብረ ኃይል ማቋቋሟን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ግብረ ኃይሉ እስከዚያው ለኬንያዊያኑ የአስቸኳይ ዕርዳታ አቅርቦትን እንደሚያስተባብር የገለጡት ዘገባዎቹ፣ እስካሁን ባለው መረጃ በግጭቱ የተገደለ ኬንያዊ እንደሌለ ጠቅሰዋል። ባሁኑ ወቅት የሱዳን የአየር ክልል ዝግ ሲሆን፣ የካርቱም አውሮፕላን ማረፊያም የግጭት ቀጠና ኾኗል። በተመሳሳይ፣ የኢትዮጵያው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ደዔታ ምስጋኑ አረጋ በኢትዮጵያ ከሱዳን አምባሳደር ጋር ትናንት ባደረጉት ውይይት፣ በአገሪቱ ስለሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ደኅንነት እንዳነሱላቸው ሚንስቴሩ ገልጧል። አራተኛ ቀኑን በያዘው ግጭት የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ200 እንዳለፈ መረጃዎች ያመለክታሉ።

5፤ የተመድ ረዳት ዋና ጸሃፊ አሚና ሞሐመድ የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ "ጨካኝ" እና "እምነት የማልጥልባቸው ናቸው" በማለት ለተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ መናገራቸው ኬንያን እንዳስከፋ ሮይተርስ አንድ የኬንያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ባለሥልጣንን ጠቅሶ ዘግቧል። አሚና ይህን መናገራቸው ይፋ የኾነው፣ ሰሞኑን ከአሜሪካ ባለሥልጣናት ካፈተለኩት ሚስጢራዊ የስለላ መረጃዎች ነው። ባለሥልጣኑ፣ አፈትልኮ የወጣው መረጃ ሩቶን ከቀጠናዊና ዓለማቀፋዊ ሥራቸው አያደናቅፋቸውም ማለታቸውን ዘገባው ጠቅሷል። የተመድ ዋና ጸሃፊ ቃል አቀባይ ስቲፋኒ ዱጃሪች፣ የአሚናን አስተያየት "ከአውዱ ውጭ የተወሰደና ተዛብቶ የቀረበ" በማለት ተችተውታል ተብሏል። በተመድ የኬንያ ቋሚ መልዕክተኛ፣ በጉዳዩ ዙሪያ ማብራሪያ ለማግኘት ጉተሬዝንና አሚናን አነጋግሬያለሁ ማለታቸውን ዘገባው ጨምሮ አመልክቷል።

6፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ0576 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ1388 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 64 ብር ከ0924 ሳንቲም እና መሸጫው 65 ብር ከ3742 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ59 ብር ከ3174 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ60 ብር ከ5037 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
ለማስታወቂያ ስራና ለመረጃ ጥቆማዎች @infoetrobot ይህን ይጠቀሙ
255 views17:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 13:15:15 በሱዳን ጉዳይ የሃያላን ሀገራት ፍላጎትና አሰላልፍ ምን ይመስላል?
የሃያላኑ የፍላጎት ተቃርኖ ካርቱምን የእጅ አዙር ጦርነት መፋለሚያ ሜዳ ያደርጋት ይሆን ?
የሱዳን ጦርና የፈጥኖ ደራሽ ሃይሉ (አርኤስኤፍ) ውጊያ ዛሬ አራተኛ ቀኑን ይዟል።
አሜሪካና ሩሲያን ጨምሮ በርካታ ሀገራትም ተፋላሚዎቹ ተኩስ አቁመው ወደ ድርድር እንዲመጡ ጥሪ ማቅረባቸውን ቀጥለዋል።
የሱዳኑ አርኤስኤፍ ሀይል ማን ነው?
ካርቱም ለ3ኛ ቀን በድብደባ እየተናወጠች ነው 
ለግጭቱ የፈጥኖ ደራሽ ሃይሉ ወደ ብሄራዊ ጦሩ መቀላቀል አለመፈለጉ እንደምክንያት ቢነሳም ከጀርባ በርካታ ገፊ ምክንያቶች እንዳሉ ተንታኞች ያምናሉ።
ከ2019ኙ መፈንቅለ መንግስት ወዲህ የሲቪል አስተዳደር ለመትከል ሞክራ ወዲያው የከሸፈባት ሀገር አደባባዮቿ ሰርክ በተቃውሞ ሰልፎች ቢሞሉም መረጋጋት አልቻለችም።
ምርጫ እስኪደረግ ድረስ የሽግግር መንግስት ለመመስረት ፖለቲከኞቿ ሲያደርጉት የከረሙት ውይይትም ወደ ፍጻሜው ሲቃረብ ኦማር ሀሰን አልበሽርን በጋራ ያስወገዱት ጀነራሎች በጠላትነት ተፈራርጀው ጦር ተማዘዋል።
በሁለቱም ወገን ያሉ “አይዞህ ባዮች” የምስራቅ አፍሪካዊቷን ሀገር መከራ ስለማብዛታቸው ነው የሚነገረው።
 የሱዳን ጦር አዛዡ አብዱልፈታህ አልቡርሃን እና የአርኤስኤፍ መሪው ጀነራል ሃምዳን ዳጋኦ (ሄሜቲ) ልዩነት እንዲሰፋም የተለያየ ፍላጎት ያላቸው ሀገራት ድርሻ በቀላሉ የሚታይ እንዳልሆነ ተንታኞች ይሞግታሉ።
ሩሲያ  
ሩሲያ ኦማር ሃሰን አልበሽር በመፈንቅለ መንግስት ከስልጣናቸው ከመነሳታቸው በፊት ከሱዳን ጋር አንድ ስምምነት ፈጽማለች፤ በፖርት ሱዳን ወታደራዊ ማዘዣ መገንባት የሚያስችል ስምምነት።
ስምምነቱ ሞስኮ 300 ወታደሮች እና አራት የጦር መርከቦቿን የምታሰፍርበትና በቀይ ባህር ቅኝት የምታደርግበትን እድል የሚፈጥር ነው።
ለ25 አመት ይቆያል የተባለው ስምምነት ካርቱምን ከሩሲያ የጦር መሳሪያ እንድታገኝ የሚያደርግ እንደነበርም አሶሼትድ ፕረስ በዘገባው ያወሳል።
ይህ ስምምነት በፓርላማ ሳይጸድቅ ግን አልበሽር በመፈንቅለ መንግስት ከስልጣናቸው ተነስተዋል።
ሞስኮ ባለፉት አመታት ከሱዳን ወታደራዊ መሪዎች ጋር በስምምነቱ ዙሪያ ስትመክር ቆይታለች።
የፈጥኖ ደራሽ ሃይሉ መሪ ጀነራል ሃምዳን ዳጋሎም ለአንድ ሳምንት በሞስኮ ቆይታ አድርገው ሲመለሱ አዎንታዊ ምላሽ መስጠታቸው ይታወሳል።
ሄሜቲ በዚህ ጉብኝታቸው ከቭላድሚር ፑቲን ሀገር የተገባላቸው ቃል ባይገለጽም የኦማር ሃሰን አልበሽር አስተዳደር ቀደም ብሎ የጠየቀው የጦር መሳሪያ ድጋፍ በአጻፋው እንደሚሰጣቸው የሚገምቱ ተንታኞች አሉ።
የሩሲያው የወጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ በሱዳን ባደረጓቸው ጉብኝቶችም የወታደራዊ ጣቢያው ጉዳይ ዋነኛ መነጋገሪያ ርዕስ እንደነበር የሮይተርስ ዘገባ ያመላክታል።
ባለፈው ቅዳሜ ጀነራል ሃምዳን ዳጋሎ የሚመሩት ፈጥኖ ደራሽ ሃይል ከሱዳን ጦር ጋር መፋለም ሲጀምር የሩሲያ ስም አብሮ እየተነሳ ነው።
የሩሲያው ቅጥረኛ ወታደሮች አቅራቢ ዋግነር ለሄሜቲ ከለላ እየሰጠ ነው የሚሉ ሪፖርቶችም ወጥተዋል።
በሱዳን የሚገኘው የሩሲያ ኤምባሲ ግን ሁለቱም ወገኖች ግጭት አቁመው ወደ ጠረጼዛ ዙሪያ ንግግር እንዲመለሱ ከመጠየቅ ውጪ ለሚቀርቡ ወቀሳዎች ምላሽ አልሰጠም።
አሜሪካ
አሜሪካ የሱዳን ወቅታዊ ሁኔታን በቅርበት እየተከታተልኩ ነው ብላለች።
 የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ አንቶኒዮ ብሊንከንም ከጀነራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን እና ጀነራል ሃምዳን ዳጋሎ ጋር በስልክ መምከራቸው ተገልጿል።
በውይይቱ በግጭቱ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች ለማንቀሳቀስና ንጹሃንን ለመጠበቅ ለ24 ስአት ተኩስ ለማቆም ተስማምተናል ያሉት ሄሜቲ፥ የአልቡርሃን ጦር ድብደባውን ገፍቶበታል ሲሉ ከሰዋል።
ይህንን አለማቀፍ ህግ የመጣስና ሌሎች ጉዳዮች በተመለከተ ከአሜሪካ ጋር በቀጣይ እንመክርበታለን የሚል መልዕክታቸውንም በትዊተር ገጻቸው ላይ አስፍረዋል።
ይህም ከዋሽንግተን የተለየ ድጋፍ ያላቸው መስሎ መታየትን መፈለጋቸውን አልያም ከብሊንከን ጋር ባደረጉት ውይይት የተገባላቸው ቃል ስለመኖሩ የሚያመላክተው ነገር እንደሚኖር ይታመናል።
የዋሽንግተን ግልጽ አሰላለፍ እስካሁን በይፋ ባይገለጽም ፍላጎቷ ግን ግልጽ ነው፤ ሩሲያ በፖርት ሱዳን ልትገነባው ያሰበችውን ወታደራዊ ጣቢያ ከንቱ ማድረግ። ለዚህም አሸናፊ ይሆናል ብላ ላመነችበት ሃይል ድጋፍ ልታደርግ እንደምትችል ነው ወታደራዊ ተንታኞች የሚያነሱት።
ሄሜቲ ከሁለቱ ባላንጣ ሃያላን ሀገራት ድጋፍ እንዳላቸው ቢነገርም ወይም መስለው ቢታዩም፥ የሱዳንን ጦር የሚመሩት ጀነራል አብዱልፈታህ አልቡርሃንም በፊናቸው አጋር አላቸው።
ከአሜሪካ እና ሩሲያ ባሻገር የጎረቤት እና የቀጠናው ሀገራት ፍላጎትና የሃይል አሰላለፍ ሱዳንን እንደ ዩክሬን የሃያላኑ የእጅ አዙር መፋለሚያ ምድር እንዳያደርጋት ያሰጋል።
የሱዳናውያን የለውጥ አቢዮት በውጭ ሃይላት ጣልቃገብነት እንዳይጠለፍም ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል እየተባለ ነው።#ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
ለማስታወቂያ ስራና ለመረጃ ጥቆማዎች @infoetrobot ይህን ይጠቀሙ
266 views10:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 07:46:48 ማክሰኞ ማለዳ! ሚያዝያ 10/2015 ዓ.ም የEMS Mereja ዐበይት ዜናዎች

1፤ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ከጠላት ጋር መተባበርን ጨምሮ ሕወሃት በጦርነቱ ወቅት ባወጣቸው 30 ክልከላዎች የታሠሩ ግለሰቦችን ለመፍታት መወሰኑን ቪኦኤ ዘግቧል። ውሳኔው ምርመራ ላይ የሚገኙ፣ በክስ ሂደት ያሉና በፍርድ ቤት ውሳኔ የታሠሩ ግለሰቦችን እንደሚመለከት ቢሮው መናገሩን የገለጠው ዘገባው፣ ሰው የገደሉ፣ ጾታዊ ጥቃት ያደረሱ ወይም ከኤርትራ ጋር የተባበሩ ግን ውሳኔው አይመለከታቸውም መባሉን ዘገባው ጠቅሷል። በውሳኔው መሠረት የሚፈተት እስረኞች ብዛት ስንት እንደኾነ ግን ቢሮው አልተገለጠም ተብሏል። የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር እስረኞችን ለመፍታት የወሰነው የሰላም ስምምነት ከተፈረመ በኋላ በእስር ላይ መቆየታቸው አስፈላጊ ስላልኾነ መኾኑን ቢሮው መግለጡን ዘገባው ጨምሮ አመልክቷል።

2፤ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በሱማሌ ክልል በኩል በኮንትሮባንድ ወደ ውጭ የሚወጣውን የጫት ምርት ለማስቆም ክልሉ ሊተባበረኝ አልፈቀደም ማለቱን ሪፖርተር አስነብቧል። በክልሉ በኩል ጫት ወደ ውጭ የሚወጣው፣ "ለአገር ውፍጆታ ነው" በሚል ሽፋን መኾኑን ኮሚሽኑ መግለጡንና፣ ጫት በሕጋዊ መንገድ ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ለሚደረገው ጥረት ጭምር የክልሉ ጸጥታ ኃይሎች ተባባሪ እንዳልኾኑ መናገሩን ዘገባው አመልክቷል። በክልሉ ሲቲ ዞን ውስጥ የጫት ኮንትሮባንድ ነጋዴዎች ከታጠቁ ሚሊሻዎች ድጋፍ እንደሚያገኙ ኮሚሽኑ መግለጡንም ዘገባው አስነብቧል።

3፤ ተመድ በሱዳን ጦር ሠራዊትና በፈጥኖ ደራሽ ሠራዊቱ መካከል በቀጠለው ግጭት ከ180 በላይ ሰዎች መገደላቸውንና ከ1800 በላይ ሰዎች መቁሰላቸውን አስታውቋል። አሜሪካ የሱዳኑ ግጭት ባስቸኳይ እንዲቆም ከጀኔራል ቡርሃንና ከጀኔራል ሞሐመድ ደጋሎ ጋር ግንኙነት እያደረገች መኾኗን አስታውቃለች። የሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በበኩሉ፣ ግጭቱ ሱዳናዊያን ብቻ የሚፈቱት የውስጥ ጉዳይ ነው ሲል ትናንት ማምሻውን አስታውቋል። ሚንስቴሩ፣ የሱዳን ጦር ሠራዊት ወታደራዊ ጠቅላይ መምሪያውን፣ ቤተ መንግሥቱን፣ የካርቱም አውሮፕላን ማረፊያንና ብሄራዊ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ጣቢያውን "አማጺ" ሲል ከፈረጀው ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት ማስለቀቁን የገለጠ ሲሆን፣ የጀኔራል ደጋሎ ኃይሎች ግን ያስተባብላሉ።

4፤ የሱዳን ጦር ሠራዊት ዋና አዛዥ ጀኔራል ቡርሃን ጀኔሬል ሞሐመድ ደጋሎ የሚመሩት ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት የከፈተው ጥቃት "የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ" እና "በአገሪቱ ላይ የተቃጣ ጥቃት" ነው ሲሉ መናገራቸውን ለሲ ኤን ኤን ዘግቧል። ጀኔራል ቡርሃን፣ ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊቱ በጦር ሠራዊቱ ጠቅላይ መምሪያ ላይ ጥቃት የፈጰመው፣ እሳቸውን ለመግደል መኾኑን መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል። የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት በበኩሉ፣ ባሁኑ ወቅት ተኩስ አቁም ለማድረግ ዝግጁ አለመኾኑን መናገሩን ብሉምበርግ ዘግቧል።

5፤ ብሪታኒያ "ሕገወጥ" ያለቻቸውን ጥገኝነት ጠያቂዎች ሩዋንዳ ውስጥ ለማስፈር ሁለቱ አገሮች የደረሱበትን ስምምነት ማሻሻላቸውን ዘ ኢስት አፍሪካን ጋዜጣ ዘግቧል። በስምምነቱ ላይ አዲስ በተጨመረው አንቀጽ መሠረት፣ ብሪታኒያ ጥገኝነት ያልጠየቁ ስደተኞችንና ፍልሰተኞችን ጭምር ወደ ሩዋንዳ እንደምትልክ ዘገባው ጠቅሷል። ማሻሻያው፣ ሩዋንዳ ጥገኝነት ያልጠየቁ ስደተኞችን ከተቀበለች በኋላ ወደ አገራቸው እንድትልካቸው መብት እንደሚሰጣት ዘገባው ጠቅሷል። የብሪታኒያ ፍርድ ቤት ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ ሩዋንዳ የመላኩ ውሳኔ ሕጋዊ ነው በማለት መወሰኑ ይታወሳል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
ለማስታወቂያ ስራና ለመረጃ ጥቆማዎች @infoetrobot ይህን ይጠቀሙ
279 views04:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 22:04:28 ሰኞ ምሽት! ሚያዝያ 9/2015 ዓ.ም የEMS Mereja ዐበይት ዜናዎች

1፤ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ምክር ቤት በጋዜጠኞች ላይ የሚመሠረቱ ክሶች "በመገናኛ ብዙኀን አዋጅ ብቻ" እንዲታዩ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። ምክር ቤቱ በታሠሩ ጋዜጠኞች ላይ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እየተፈቀደባቸው መታሠራቸው "ተቀባይነት የሌለው ነው" በማለት ድርጊቱን አውግዟል። ጋዜጠኞች በመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች "ከሕግ አግባብ ውጭ መያዛቸው፣ መታፈናቸውን" የጠቀሰው ምክር ቤቱ፣ የመገናኛ ብዙኀን ተቋማት "ያለ ፍርድ ቤት ማዘዣ ብርበራ" እንደሚፈጸምባቸው አመልክቷል።

2፤ የኢትዮጵያ መንግሥት በሳዑዲ ዓረቢያ በቤት ሠራተኛነት ቀጥረው የሚሠሩ ዕድሜያቸው ከ18 እስከ 40 የሚኾኑ 500 ሺህ ሠራተኞችን እየመለመለ መኾኑን አልጀዚራ ዘግቧል። አማራ ክልል ብቻ 150 ሺህ አመልካቾችን እንዲመዘግብ በመንግሥት መታዘዙን መናገሩን ዘገባው አመልክቷል። ተቀጣሪ ሠራተኞች ወደ ሳዑዲ ዓረቢያ በመንግሥት ወጪ እንደሚጓዙና ወርሃዊ ደመወዛቸው 1 ሺህ የሳዑዲ ሪያል ወይም 266 የአሜሪካ ዶላር እንደሚኾን ዘገባው አመልክቷል። መንግሥት አመልካቾች እንዲመዘገቡ በተለያዩ ከተሞች ጥሪ ሲያደርግ ሰንብቷል ተብሏል።

3፤ በሱዳን ጦር ሠራዊትና በፈጥኖ ደራሹ ሠራዊት መካከል ከቅዳሜ ጀምሮ በቀጠለው ግጭት በትንሹ 97 ሰላማዊ ሰዎችና 45 ወታደሮች መገደላቸውንና ከ940 በላይ ሰዎች መቁሰላቸውን የሱዳን ሐኪሞች ቡድን ማስታወቁን ሮይተርስ ዘግቧል። ዛሬ ካርቱም ውስጥ በጦር ሠራዊቱ ዋና ወታደራዊ ማዘዣ ጣቢያ አካባቢ ውጊያ ሲካሄድ መዋሉን የጠቀሰው ዘገባው፣ የሱዳን ጦር ሠራዊት ብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያውን መልሶ መቆጣጠሩ አመልክቷል። የፈጥኖ ደራሹ ሠራዊት ዋና አዛዥ ጀኔራል ሞሐመድ ሐሚቲ፣ ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ "እስላማዊ አክራሪ" እና "ወንጀለኛ" ባሏቸው በባላንጣቸው የጦር ሠራዊቱ ዋና አዛዥ ጀኔራል ቡርሃን ላይ ርምጃ እንዲወስድ በትዊተር መልዕክታቸው ጠይቀዋል።

4፤ ኢጋድ በሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም ለተቀሰቀሰው ከባድ ግጭት ሰላማዊ መፍትሄ ለማፈላለግ ከፍተኛ የመሪዎች ልዑካን ቡድን ሊልክ እንደኾነ አስታውቋል። ኢጋድ ወደ ካርቱም የሚልከው፣ የደቡብ ሱዳኑን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪርን፣ የጅቡቲውን ኡመር ጌሌንና የኬንያውን ዊሊያም ሩቶን እንደኾነ ገልጧል። የኬንያ፣ ኡጋንዳ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱማሊያና ጅቡቲ መሪዎች ትናንት ባደረጉት የበይነ መረብ ውይይት፣ የአገሪቱ ጦር ሠራዊት እና ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት ግጭቱን ባስቸኳይ አቁመሙ ንግግር እንዲጀምሩና የሰብዓዊ ዕርዳታ ኮሪደሮችን እንዲከፍቱ ጥሪ አድርገዋል።
አፍሪካ ኅብረትም፣ የኮሚሽኑን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማኅተማን ወደ ካርቱም እንደሚልክ አስታውቋል።

5፤ 15 የሱማሊያ ዓለማቀፍ አጋሮች የሱማሌላንድ ራስ ገዝ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ በላስ አኖድ ከተማ ለቀጠለው ግጭት "ያለምንም ቅድመ ሁኔታ አስቸኳይ ተኩስ አቁም እንዲያውጁ በጋራ ባወጡት መግለጫ ጠይቀዋል። ዓለማቀፍ አጋሮች፣ የራስ ገዟ ወታደሮችና ተቃዋሚ የጎሳ ሚሊሻዎች በጋራ ስምምነት ወደሚደረስባቸው ቦታዎች ተዋጊዎቻቸውን እንዲያሸሹ ጥሪ አድርገዋል። ፕሬዝዳንት ቢሂ ግን፣ ወታደሮቻቸውን ከላስ አኖድ ከተማ እንዲያስወጡ የቀረበላቸውን ጥሪ እንዳልተቀበሉት የሱማሊያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል።

6፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ0403 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ1211 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 64 ብር ከ5364 ሳንቲም እና መሸጫው 65 ብር ከ8271 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ59 ብር ከ5308 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ60 ብር ከ7214 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
ለማስታወቂያ ስራና ለመረጃ ጥቆማዎች @infoetrobot ይህን ይጠቀሙ
288 views19:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 21:21:53 ሰበር ሰበር ሰበር ሰበር
ዶ/ር ዐብይ አህመድ የኖቤል ሽልማቱን ለምን ሊነጠቅ ቻለ?!
ጌታቸው ረዳ ሁለት ክፍለ ጦሩን ወደ አማራ ክልል ለምን አስጠጋ?
ህወሓት ለቆቦና አላማጣ ከተሞች የሾማቸው አስተዳዳሪዎች እነማናቸው?!
ዶ/ር ዐብይ አህመድ የተበላው ቁማር ምንድነው? ሁሉንም ከስር ባለው ሊንክ ይመልከቱ


ይህንን ተጫኑ
278 views18:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 18:59:28 ዓርብ ምሽት! ሚያዝያ 6/2015 ዓ.ም የEMS Mereja ዐበይት ዜናዎች

1፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ከዓለማቀፉ ገንዘብ ድርጅት ቢያንስ 2 ቢሊዮን ዶላር ለመበደር ከድርጅቱ ጋር ንግግር ላይ እንደኾነ ከምንጮች ሰምቻለሁ ሲል ሮይተርስ ዘግቧል። ኢትዮጵያ በድርጅቱ ውስጥ ካላት ድርሻ ቢያንስ 500 ፐርሰንት ያህሉን ለመበደር መጠየቋን የጠቀሰው ዘገባው፣ ድርጅቱም የአገሪቱን ብድር የመበደር አቅም ገና እያጠናና ከመንግሥት ልዑካን ቡድን ጋር ዋሽንግተን ውስጥ ድርድር ላይ መኾኑን አመልክቷል። ድርጅቱ በደረሰበት ግምገማ፣ ኢትዮጵያ እስከ ቀጣዮቹ አራት ዓመታት በአማካይ የ6 ቢሊዮን ዶላር ክፍተት ይገጥማታል የሚል ስጋት መኖሩን ዜና ምንጩ ጨምሮ ጠቅሷል።

2፤ የጣሊያን ጠቅላይ ሚንስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በኢትዮጵያ ለሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ማምሻውን አዲስ አበባ መግባታቸውን ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል። ሜሎኒ ቦሌ ዓለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ፣ ዐቢይ አቀባበል አድርገውላቸዋል። ጠቅላይ ሚንስትር ሜሎኒ፣ ጣሊያን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን ሰብዓዊና የልማት ድጋፍ ማጠናከር በምትችልባቸው ኹኔታዎችና በቀጠናዊ፣ አሕጉራዊና ዓለማቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር እንደሚመክሩ ይጠበቃል።

3፤ የሱማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሐመድ በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ መግባታቸውን ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በትዊተር ገጹ አስታውቋል። ፕሬዝዳንት ሞሐመድ በኢትዮጵያ የኹለት ቀናት የሥራ ቆይታ እንደሚኖራቸው ሚንስቴሩ የገለጠ ሲሆን፣ የጉብኝታቸው ዓላማ ምን እንደኾነ ግን አላብራራም። ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ፕሬዝዳንቱን በጽሕፈት ቤታቸው መቀበላቸውን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል። ለፕሬዝዳንት ሞሐመድ በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ አቀባበል ያደረጉላቸው የገዥው ብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ እንደኾኑ ተገልጧል።

4፤ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ባለሙያዎች ማኅበር "ያለምንም የሕግ አግባብ የታሠሩ ጋዜጠኞች" ባስቸኳይ እንዲፈቱ ትናንት ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። የመንግሥት ጸጥታ አካላት ጋዜጠኞች ሥራቸውን በነጻነት እንዳይሠሩ እያሸማቀቋቸውና እንግልት እያደረሱባቸው መኾኑን ማኅበሩ ገልጧል። ማኅበሩ፣ የሥራ አሥፈጻሚ አባሉና የ"አራት ኪሎ ሜዲያ" ዩትዩብ ጣቢያ ባለቤትና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻውን ጨምሮ ስድስት ጋዜጠኞች በአሁኑ ወቅት በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንደሚገኙ በመግለጫው አውስቷል።

5፤ ቦይንግ ኩባንያ ደንበኞች ያዘዟቸውን ቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላኖች ባቀደው ጊዜ ለማስረከብ እንዳልቻለ አስታውቋል። ትዕዛዞቹ የዘገዩት፣ በአውሮፕላኑ የኋላኛው ክፍል ላይ እንዲገጠሙ ሌሎች አምራች ኩባንያዎች ያመረቷቸው መገጣጠሚያዎች ተፈላጊውን ደረጃ ባለመሟላታቸው እንደኾነ ኩባንያው ገልጧል። ችግሩ አጣዳፊ የበረራ ደኅንነት ስጋት እንደማይደቅን የገለጠው ኩባንያው፣ በረራ ላይ ያሉ ማክስ አውሮፕላኖች በረራቸውን መቀጠል ይችላሉ ብሏል። የችግሩ ሰለባ የኾኑት፣ በመገጣጠም ሂደት ላይ ያሉና ተጠናቀው የተቀመጡ "ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው" አውሮፕላኖች መኾናቸውንም ኩባንያው ጠቅሷል።ባንያው ተጨማሪ ቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላኖችን እንዲያመርትላቸው ትዕዛዝ ሰጥተው ከሚጠባበቁት አየር መንገዶች መካከል፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይገኝበታል።

6፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ0117 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ0919 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 64 ብር ከ1360 ሳንቲም እና መሸጫው 65 ብር ከ4187 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ58 ብር ከ9106 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ60 ብር ከ0888 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። አንድ የቻይና ዩዋን ደሞ በ7 ብር ከ0980 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ7 ብር ከ2400 ሳንቲም እንደተሸጠ ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
196 views15:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 18:46:08
ዜና
በኬንያ ክርስቶስን ቶሎ ለማግኘት በረሃብ አድማ ላይ የነበሩ አራት ሰዎች ህይወታቸው አለፈ

በኬንያ የባህር ጠረፍ ኪሊፊ አውራጃ አራት ሰዎች ህይወታቸው አልፈው የተገኙ ሲሆን በርካቶች ደግሞ ክፉኛ መጎዳታቸው የተሰማ ሲሆን የምግብ አድማ በማድረግ የዓለምን ፍጻሜ ሲጠባበቁ እንደነበረ ተጠቁመሟማ። ፖሊስ እንዳስታወቀው ለተከታታይ ቀናት ባጫካ ውስጥ ግለሰቦቹ በፃም "ኢየሱስን ለማግኘት እንዲጠበቁ በኃይማኖት አባት" ከተነገራቸው በኋላ ይህው ድርጊት አጋጥሟል።

ፖሊስ ባደረገው የነፍስ አድን ጥረት 11 ሰዎችን በህይወት ማትረፍ ችሏል። በህይወት ከተረፉት መካከል ስድስቱ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን በከፋ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ተጠቁሟል ። ሌሎች የቀሩ ሰዎች በጫካ ውስጥ እንዳሉ መነገሩን ተከትሎ ፖሊስ ዛሬ ጠዋት ተጨማሪ ኃይል በማሰማራት ፍለጋ እንደሚቀጥል ገልጿል።

ፖሊስ በጫካው ውስጥ በቅርብ ቀናት የተቀብሩ ሰዎች አስክሬን ማግኘቱን አስታውቋል። ግለሰቦቹ ፈጥነው ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመድረስ በረሃብ እንዲሞቱ ያደረገው የጉድ ኒውስ ኢንተርናሽናል ቤተክርስቲያን መሪ መሆኑ ተነግሯል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
207 views15:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ