Get Mystery Box with random crypto!

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ) Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ)
የሰርጥ አድራሻ: @zemedkun_zemede
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.26K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2023-04-12 08:33:12 በጦርነቱ የተሳተፉ ቤተሰቦቻቸው የት እንዳሉ ማወቅ እንፈልጋለን ሲሉ የመቀሌ ነዋሪዎች ጠየቁ:: አዲስ ዘይቤ

አቶ ገብረመስቀል አበበ የተባሉት ሌላኛው ነዋሪም የአንድ ወንድ ልጅ አባት ሲሆኑ “ከአንድ ቤት አንድ ሰው ወደ ጦርነት መግባት አለበት፣ ካልሆነ እርዳታ አይሰጠውሙ” በተባለ ጊዜ አንዱ ልጃቸው በግዳጅ ወደ ውጊያ ማምራቱን በሀዘን ድባብ ውስጥ ሆነው ነግረውናል።

አሁን በተደረሰው ስምምነት መሰረት “ልጄ ከዛሬ ነገ ይመጣል እያልኩ በሀዘንና በተስፋ እገኛለሁ” የሚሉት አቶ ገብረመስቀል ልብ በሚሰብር ሁኔታ እያለቀሱ ልጄ ካለ መንግስት ምላሽ ይስጠኝ ሲሉ ይማፀናሉ። 

ወ/ሮ ለምለም ኃይሉ የመቀሌ ከተማ ነዋሪ ናቸው። ለሁለት ዓመታት በቆየው ጦርነት ሁለት ልጆቻቸው ወደበረሃ ወርደው ጦርነቱን እንደተቀላቀሉ ይገልፃሉ። ጦርነቱ በሰላም ስምምነት ተቋጭቶ ግልፅነት ይጎድለዋል የሚሉ አካላት ቢኖሩም አንፃራዊ ሰላም ሰፍኖ ክልሉም ጊዜያዊ አስተዳደር ተሹሞለታል።

ይሁን እንጂ ወ/ሮ ለምለም ሁለት ልጆቻቸው እስካሁን ድረስ የት እንዳሉ እንደማያውቁ ገልፀው የልጆጃቸውን መገኛ በጉጉት እንደሚጠብቁ ነግረውናል። ከቤት በወጡበት ሰሞን ልጆቻቸው ደብዳቤ ይሉኩላቸው እንደነበር ለአዲስ ዘይቤ የተናገሩት አዛውንቷ፣ ለመጨረሻ ጊዜ የልጆቻቸውን ወሬ ከሰሙ 1 ዓመት ከ8 ወር ማለፉንም ገልፀዋል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
282 views05:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 08:27:53 ረቡዕ ማለዳ! ሚያዝያ 4/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ ትናንት በአማራ ክልል የኮምቦልቻ ከተማ የጸጥታ ዕዝ ከምሽቱ 3:00 ሰዓት በኋላ ማንኛውም ሰው መንቀሳቀስ እንደማይችል ገደብ መጣሉን አስታውቋል። የጸጥታ ዕዙ፣ በከተማዋ አድማ መጥራት ወይም ማስተባበር፣ ያልተፈቀዱ ስብሰባዎችን ማድረግና ጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ የከለከለ ሲሆን፣ ከጸጥታ አካላት ተሽከርካሪዎች ውጭ ባጃጅና ሌሎች ተሽከርካሪዎች ከምሽት 1:00 ሰዓት በኋላ እንዳይንቀሳቀሱ ገደብ ጥሏል። መጠጥና ምግብ ቤቶችም ከምሽቱ 1:00 ሰዓት በኋላ አገልግሎት እንዳይሰጡ ተከልክለዋል።

2፤ በአማራ ክልል የወልድያ ከተማ የጸጥታ ዕዝ ከጸጥታ ሰዎች ውጭ ከምሽቱ 3:00 እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት በከተማዋ የማንኛውንም ሰው እንቅስቃሴ ማገዱን አስታውቋል። በከተማዋ በማንኛውም ጊዜና ቦታ ጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ፣ ጥይት መተኮስ፣ አድማ መቀስቀስ፣ የጸጥታ አካላትን አልባሳት መልበስ፣ ያልተፈቀዱ ስብሰባዎችን ማድረግ፣ ወታደራዊ ሥልጠና መስጠትን ከልክሏል። ቡና ቤቶች፣ ካፍቴሪያዎችና ምግብ ቤቶች ከምሽቱ 2:00 ሰዓት በኋላ አገልግሎት እንዳይሰጡ፣ ባጃጆችም ከምሽቱ 1:00 ሰዓት እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት ድረስ እንዳይንቀሳቀሱ ጭምር ዕዙ አግዷል።

3፤ እናት ፓርቲ፣ መኢአድና ኢሕአፓ መንግሥት የአማራ ክልል ልዩ ኃይልን ማፍረስ በሚመስል መልኩ በክልሉ ከጀመረው "ግብታዊ እንቅስቃሴ" እንዲቆጠብና የሰሞኑ "የጥፋት ጉዞ እንዲገታ" አዲስ ባወጡት የጋራ መግለጫ ጠይቀዋል። መንግሥት አገራዊ ምክክር ተደርጎ የሕገመንግሥት ማሻሻያ እስኪደረግ ድረስ፣ አገሪቱን "ወደ ሁለንተናዊ ቀውስ እየከተታት ያለውን አካሄድ እንዲያቆም" ፓርቲዎቹ ጥሪ አድርገዋል። የክልሉ ልዩ ኃይል መሳሪያዎቹን ወደ ግምጃ ቤት እንዲያስገባ በጽሁፍ ትዕዛዝ ተላልፎለታል ያሉት ፓርቲዎቹ፣ የመንግሥት ርምጃ "ግልጽነት በጎደለው" ኹኔታ እየተካሄደ መኾኑንና አካሄዱ "አገሪቱን ወደ ሁለንተናዊ ቀውስ የሚያስገባ" መኾኑን ገልጸዋል።

4፤ የታንዛኒያ ፖሊስ 63 ኢትዮጵያዊያን ሕገወጥ ፍልሰተኞች በኬንያ በኩል ባንድ የከባድ ጭነት ተሽከርካሪ ወደ ታንዛኒያ ገብተው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን መናገሩን ዘ ኢስት አፍሪካን ዘግቧል። ፍልሰተኞቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት፣ ሲያጓጉዛቸው የነበረው ተሽከርካሪ የግጭት አደጋ አጋጥሞት በቆመበት ወቅት መኾኑንና ሌሎች 40 ኢትዮጵያዊን ፍልሰተኞች ግን ከአካባቢው ተሰውረው እየተፈለጉ መኾኑን ፖሊስ መግለጡን ዘገባው ጠቅሷል። ፍልሰተኞች በሕገወጥ የሰው አዘዋዋሪዎች አማካኝነት ወደ ደቡብ አፍሪካ ሊሻገሩ እንደነበር ተገልጧል።

5፤ ትናንት ናይሮቢ የገቡት የኤርትራው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ኦስማን ሳለህና የፕሬዝዳንት ኢሳያስ አማካሪ የማነ ገ/አብ ከፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ጋር መወያየታቸውን የኤርትራው ቃል አቀባይ የማነ ገ/መስቀል በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል። ልዑካን ቡድኑ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ በሁለትዮሽና ቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለኬንያው አቻቸው ፕሬዝዳንት ሩቶ የላኩትን መልክት ማድረሳቸውን ኢምባሲው ገልጧል። ፕሬዝዳንት ሩቶም፣ የሁለቱ አገራት የጋራ የትብብር ማዕቀፍ በቶሎ እንዲሰበሰብ መጠየቃቸው ተጠቅሷል።

6፤ የደበብ አፍሪካ መንግሥት በሩሲያና ዩክሬን ጦርነት ላይ የያዘውን አቋም ለአሜሪካ ባለሥልጣናት ለማስረዳትና ለማሳመን ወደ ዋሽንግተን ልዑካን ቡድን ሊልክ መኾኑን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የልዑካኑ አባላት ማንነት ግን እንዳልተገለጠ ዘገባዎቹ አመልክተዋል። ደቡብ አፍሪካ በሩሲያና ዩክሬን ጦርነት ለሩሲያ ድጋፏን አሳይታለች በማለት አሜሪካ ቅር እንደተሰኘችባት ስትገልጽ ቆይታለች። በቀጣዩ ሐምሌ በደቡብ አፍሪካ በሚካሄደው የ"ብሪክስ" የመሪዎች ጉባኤ ላይ የዓለማቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት የእስር ማዘዣ ያወጣባቸው ፕሬዝዳንት ፑቲን የሚገኙ መኾኑ ደሞ፣ ደቡብ አፍሪካን አጣብቂኝ ውስጥ አስገብቷታል። ደቡብ አፍሪካ የፍርድ ቤቱ መመስረቻ ስምምነት ፈራሚ ናት። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
265 views05:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 21:55:15 ማክሰኞ ምሽት! ሚያዝያ 3/2015 ዓ.ም የEMS ዕለታዊ ዜናዎች
1፤ በትግራይ ክልል ሽራሮ ከተማ ከሚገኝ የዓለም ምግብ ድርጅት የዕርዳታ መጋዘን ውስጥ ለ100 ሺህ ተረጅዎች የሚበቃ ሰብዓዊ ዕርዳታ መዘረፉን ድርጅቱ በቅርቡ እንደደረሰበት ከሁለት የረድዔት ድርጅት ሠራተኞች ሰምቻለሁ ሲል አሶሴትድ ፕሬስ ዘግቧል። ዕርዳታውን የለገሰው የአሜሪካው ዓለማቀፍ የተራድዖ ድርጅት መኾኑንና ዕርዳታውን ማን እንደዘረፈው ግን እስካሁን እንዳልታወቀ ምንጮቹ መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል።
ድርጅቱ በትክክል ከየትኛው መጋዘኑ ዕርዳታ እንደተዘረፈ ባይጠቅስም፣ በኢትዮጵያ የድርጅቱ ኃላፊ ክላውድ ጂቢዳር ግን ለድርጅቱ አጋሮች በጻፉት ደብዳቤ በአገር ውስጥ ገበያዎች ከፍተኛ መጠን ያለው ምግብ ለሽያጭ መቅረቡ ድርጅቱን እንዳሳሰበው መግለጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ኹኔታው በድርጅቱ ስምና ወደፊት የምግብ ዕርዳታ ልገሳ ለማግኘት በሚያደርገው ጥረት ላይ ስጋት እንደሚደቅን ኃላፊው መግለጣቸውንና፣ "ዕርዳታ እንዳይዘረፍና ላልታለመለት ዓላማ እንዳይውል አስቸኳይ ርምጃዎችን መውሰድ መውሰድ እንደሚያስፈልግ" በደብዳቤያቸው መጠቆማቸው በዘገባው ተጠቅሷል። ድርጅቱ በጉዳዩ ላይ ምርመራ እያደረገ ስለመኾኑም በደብዳቤው ላይ ጠቅሷል ተብሏል።

2፤ አብን የአማራ ክልልን ጨምሮ የየትኛውም ክልል ካቢኔ ወይም ምክር ቤት የክልል ልዩ ኃይሎችን መልሶ በማደራጀት ዙሪያ ያደረገው "ውይይትም ኾነ ያሳለፈው ሕጋዊ ውሳኔ" የለም ሲል ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። የፌደራል መንግሥት ባለሥልጣናት የክልል ልዩ ኃይሎች የመልሶ ማደራጀት ማስፈጸሚያ በተባለው ዕቅድ ላይ የተወያዩት መጋቢት 30 ላይ መኾኑን ፓርቲው በአስረጅነት ጠቅሷል። ገዥው ፓርቲ የክልል ልዩ ኃይሎችን መልሶ የማደራጀቱ ውሳኔው በሁሉም ክልሎች በተመሳሳይ ጊዜ የሚተገበር ስለመኾኑ ትናንት ያወጣው መግለጫ "እወነታን የካደ" መኾኑን የገለጠው አብን፣ ከአማራ ክልል ውጪ "በየትኛውም ክልል የልዩ ኃይል አባላትን ትጥቅ የማስፈታት ወይም መልሶ የማደራጀት እንቅስቃሴ አልተደረገም" ብሏል። የአማራ ክልል ልዩ ኃይል አዛዦችን በድንገት ከሥራ ውጭ በማድረግ፣ የልዩ ኃይሉ "የዕዝ ሰንሰለት እንዲፈርስ" ተደርጓል በማለትም አብን ከሷል። አብን አያይዞም፣ የክልሉና የፌደራል መንግሥታት "የክልሉ ሕዝብ አደባባይ ወጥቶ ያቀረበውን ጥያቄ እንዲያከብሩ" ጠይቋል።

3፤ በአማራ ክልል በባሕርዳር እና ደብረብርሃን ከተሞች በተለያዩ የጸጥታ ኃይሎች መካከል ዛሬ የተኩስ ልውውጥ መደረጉን ከነዋሪዎችና የረድዔት ድርጅት ሠራተኞች መስማቱን ጠቅሶ አሶሴትድ ፕሬስ ዘግቧል። ትናንት ሌሊት ደሞ፣ በደሴ እና ሰቆጣ ከተሞች የጥይት ተኩስ ሲሰማ ማደሩን ከምንጮች መስማቱን ዘገባው አመልክቷል። በክልሉ በርካታ በአካባቢዎች መንገዶች፣ የንግድ መደብሮችና ባንኮችም መዘጋታቸውን ዜና ምንጩ ጨምሮ አመልክቷል።

4፤ ኢሰመጉ መንግሥት የክልል ልዩ ኃይሎችን መልሶ ለማደራጀት ጀመርኩት ያለው እንቅስቃሴ የክልሎችን ነባራዊና ተጨባጭ ኹኔታ ግምት ውስጥ ያስገባና የዜጎችን ደኅንነት አደጋ ላይ የማይጥል መኾኑን እንዲያረጋግጥ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። መንግሥት የክልሎች ልዩ ኃይሎችን መልሶ የማደራጀት ውሳኔውንና የውሳኔውን አፈጻጸም ለተለያዩ ባለድርሻ አካላትና ባጠቃላይ ለሕዝቡ ግልጽ እንዲያደርግ የጠየቀው ኢሰመጉ፣ የፌደራሉና ክልል መንግሥታት ውሳኔውን በሰላማዊ፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰት በማያስከትልና ዘለቄታዊ መፍትሄ ሊያመጣ በሚችል መንገድ እንዲፈጽሙት ጥሪ አድርጓል። ኢሰመጉ፣ ክልሎች በአንዳንድ አጋጣሚዎች ልዩ ኃይሎቻቸውን በማንቀሳቀስ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ሲፈጽሙ እንደተስተዋሉ ኢሰመጉ በመግለጫው አስታውሷል። ኢሰመጉ፣ ሰሞኑን ከመንግሥት ውሳኔ ጋር በተያያዘ በአማራ ክልል በተቀሰቀሱ ተቃውሞዎች መንገዶች እንደተዘጉና የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችም እንደተፈጸሙ ጨምሮ አመልክቷል።

5፤ የዓለማቀፉ ቀይ መስቀል ማኅበር የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ቢሮ በአማራ ክልል ለሕይወት አስጊ በኾነ ሕመም ላይ የሚገኙ ታማሚዎችን ከቦታ ቦታ በሚያጓጉዙ አምቡላንሶች እና የጤና ባለሙያዎች ላይ በቅርብ ጊዜያት የተፈጸሙ ጥቃቶች አሳስበውኛል ሲል ዛሬ ከቀትር በኋላ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። የጤና ሠራተኞች፣ አምቡላንሶችና ሆስፒታሎች ዒላማ መኾን እንደሌለባቸው የገለጠው ማኅበሩ፣ የጤና ሠራተኞች፣ አምቡላንሶችና ሆስፒታሎች በማናቸውም ጊዜ ሊከበሩ እና ጥበቃ ሊደረግላቸው የሚገባቸው ናቸው ብሏል።

6፤ በትግራይ ክልል ሽራሮ ከተማ ከሚገኝ የዓለም ምግብ ድርጅት የዕርዳታ መጋዘን ውስጥ ለ100 ሺህ ተረጅዎች የሚበቃ ሰብዓዊ ዕርዳታ መዘረፉን ድርጅቱ በቅርቡ እንደደረሰበት ከሁለት የረድዔት ድርጅት ሠራተኞች ሰምቻለሁ ሲል አሶሴትድ ፕሬስ ዘግቧል። ዕርዳታውን የለገሰው የአሜሪካው ዓለማቀፍ የተራድዖ ድርጅት መኾኑንና ዕርዳታውን ማን እንደዘረፈው ግን እስካሁን እንዳልታወቀ ምንጮቹ መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል።
ድርጅቱ በትክክል ከየትኛው መጋዘኑ ዕርዳታ እንደተዘረፈ ባይጠቅስም፣ በኢትዮጵያ የድርጅቱ ኃላፊ ክላውድ ጂቢዳር ግን ለድርጅቱ አጋሮች በጻፉት ደብዳቤ በአገር ውስጥ ገበያዎች ከፍተኛ መጠን ያለው ምግብ ለሽያጭ መቅረቡ ድርጅቱን እንዳሳሰበው መግለጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ኹኔታው በድርጅቱ ስምና ወደፊት የምግብ ዕርዳታ ልገሳ ለማግኘት በሚያደርገው ጥረት ላይ ስጋት እንደሚደቅን ኃላፊው መግለጣቸውንና፣ "ዕርዳታ እንዳይዘረፍና ላልታለመለት ዓላማ እንዳይውል አስቸኳይ ርምጃዎችን መውሰድ መውሰድ እንደሚያስፈልግ" በደብዳቤያቸው መጠቆማቸው በዘገባው ተጠቅሷል።

7፤ የጤና ሚንስትር ዶ/ር ሊያ ታደሠ የመሩት የሚንስቴሩ ከፍተኛ ልዐካን ቡድን ዛሬ በመቀሌ ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ባለሥልጣናት ጋር ውይይት ማድረጉን የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል። ልዑካን ቡድኑ በትግራዩ ጦርነት በጤና ተቋማት ላይ የደረሰውን ውድመት በማዕከላዊ እና ምሥራቃዊ የክልሉ አካባቢዎች ተዘዋውሮ እንደሚጎበኝ ዘገባው አመልክቷል።

8፤ የተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ዛሬ በጎረቤት ሱማሊያ ጉብኝት በማድረግ ላይ ናቸው። ጉተሬዝ ሞቃዲሾ ውስጥ ከሱማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሐመድ ጋር የተወያዩ ሲሆን፣ በውይይቱ ላይም ፕሬዝዳንት ሞሐመድ የተመድ ጸጥታው ምክር ቤት በሱማሊያ ላይ የጣለውን የጦር መሳሪያ ማዕቀብ እንዲያነሳ መጠየቃቸውን የፕሬዝዳንቱ ቤተመንግሥት አስታውቋል። ጉተሬዝ፣ ወደ ደቡባዊ ምዕራብ ፌደራል ግዛት ዋና ከተማ ባይድዋ አቅንተው በአገሪቱ ለ5 ተከታታይ የዝናብ ወቅቶች የተከሰተው ከባድ ድርቅ ያስከተለውን ሰብዓዊ ቀውስና በምግብ እጥረት የተጎዱ ሰዎች የተጠለሉበትን ጣቢያ መመልከታቸውን የሱማሊያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል።

9፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ0019 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ0819 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 64 ብር ከ0471 ሳንቲም እና መሸጫው 65 ብር ከ3280 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ58 ብር ከ8459 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ60 ብር ከ0228 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
285 views18:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 08:08:57 ተለቀቀ! ቁጥር_3
የሳጥናኤል ጎል ኢትዮጵያ ትረካ መፅሐፍ- ክፍል 1- ቁጥር 3  ሙሉ ክፍል ተለቀቀ!! ሊንኩን በመንካት ትረካውን ያድምጡ


312 views05:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 07:26:04 ማክሰኞ ማለዳ! ሚያዝያ 3/2015 ዓ.ም የEMS Mereja ዕለታዊ ዜናዎች

1፤ በአማራ ክልል የደብረብርሃንና ደሴ ከተሞች የጸጥታ ዕዞች የተለያዩ ጸጥታ-ነክ ገደቦችንና ክልከላዎችን ተጥለዋል። በከተሞቹ ከተጣሉት ክልከላዎችና ገደቦች መካከል፣ ከመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች ውጪ ጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስለ፣ እውቅና የሌላቸው ስብሰባዎችን ማድረግ፣ አድማዎችን ማድረግ፣ ማስተባበር መቀስቀስ እና መታወቂያ ሳይዙ መንቀሳቀስ ይገኙበታል። በደብረብርሃን ከተማ የሚገኙ ተፈናቃዮችም ላልተወሰነ ጊዜ ከመጠለያ ጣቢያዎች ውጭ እንዳይንቀሳቀሱ ገደብ ተጥሏል።

2፤ ትናንት ምሽት በባሕርዳር ከተማ አባይ ማዶ ቀበሌ ባንድ የሆቴልና መጠጥ መሸጫ በደረሰ የቦምብ አደጋ ሦስት ሰዎች ሞተው 10 ሰዎች መቁሰላቸውን ቪኦኤ ዘግቧል። በአካባቢው የሚገኘው አዲስ ዓለም ሆስፒታል ከ10 በላይ በአደጋው የቆሰሉ ሰዎች ለሕክምና ገብተው እንደነበር መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል። የአማራ ክልል ልዩ ኃይልን መልሶ ከማደራጅት ውሳኔ ጋር በተያያዘ፣ በከተማዋ ከዕሁድ'ለት ጀምሮ አገልግሎት ሰጪና የንግድ ተቋማት ዝግ እንደኾኑ ዘገባው ጨምሮ አመልክቷል።

3፤ በአማራ ክልል የካቶሊክ ተራድዖ ድርጅት ዕሁድ'ለት በቆቦ ከተማ በነበረ የከባድ መሳሪያ ተኩስ የተገደሉበት ሠራተኞቹ ቾል ቶንጊክ የተባሉ የጸጥታ ሃላፊው እና አማረ ክንደያ የተባሉ ሹፌሩ እንደኾኑ መናገሩን የውጭ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ሁለቱ የድርጅቱ ሠራተኞች የተገደሉት፣ ከአካባቢው ወደ አዲስ አበባ በመንቀሳቀስ ላይ ሳሉ መኾኑን ገልጧል። ኾኖም ሁለቱ ግለሰቦች በምን አኳኋን ሊገደሉ እንደቻሉ ገና እንዳላወቀ ድርጅቱ አስታውቋል።

4፤ የፌደራሉ ጤና ሚንስቴር ከፍተኛ ልዑካን ቡድን ዛሬ በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ በተለያዩ አካባቢዎች ጉብኝት እንደሚያደርግ የትግራይ ክልል ቴሌቪዥን ዘግቧል። የልዑካን ቡድኑን የሚመሩት የጤና ሚንስትር ደኤታው እንደኾኑ ዘገባው ጠቅሷል። ባለፉት ጥቂት ቀናት የትምህርት ሚንስቴር ከፍተኛ ልዑካን ቡድን በመቀሌ ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ባለሥልጣናት ጋር መምከሩ ይታወሳል።

5፤ የተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ዛሬ ሞቃዲሾ ይገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የቻይናው ሲጂቲኤን ዘግቧል። ጉተሬዝ በሱማሊያ ጉብኝት ያደርጋሉ የተባለው፣ በአገሪቱ በተከሰተው ድርቅ ሳቢያ ከ8 ነጥብ ሁለት ሚሊዮን በላይ ሱማሊያዊያን የድርቅ ተጎጅዎች አስቸኳይ ሰብዓዊ ዕርዳታ ፈላጊ በኾኑበት ወቅት ላይ ነው።

6፤ የኬንያው ፕሬዝዳንት ሩቶ እና ተቃዋሚያቸው ራይላ ኦዲንጋ ለአገሪቱ መረጋጋት ሲሉ የብሄራዊ አንድነት መንግሥት ለመመስረቱ እንዲደራደሩ ግፊት እየተደረገባቸው መኾኑን ደይሊ ኔሽን አስነብቧል። ከብሄራዊ አንድነት መንግሥት ሌላ፣ ሁለተኛው አማራጭ በመንግሥት ውስጥ ለተቃዋሚ ፓርቲው ሊቀመንበር ራሱን የቻለ ቢሮ ማቋቋም መኾኑን ዘገባው አመልክቷል። ፕሬዝዳንቱ ሁለተኛውን አማራጭ ቢደግፉትም፣ ኦዱንጋ ግን ውድቅ አድርገውታል። ሁለቱ አማራጮቹ የቀረቡት፣ በቅርቡ ወደ ኬንያ አቅንተው የነበሩት የፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ልዑክ ሴናተር ክሪስ ኩንስ እና የኬንያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን መሪዎች አማካኝነት ነው። ኦዱንጋ፣ አሸናፊው ሁሉንም ጠቅልሎ የሚወስድበትን የምርጫ ሥርዓት የሚቀይር ሕገመንግሥታዊ ማሻሻያ እንዲደረግ ሃሳብም አቅርበዋል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
335 views04:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 20:11:54 ሰኞ ምሽት! ሚያዝያ 2/2015 ዓ.ም የEMS Mereja ዐበይት ዜናዎች

1፤ በአማራ ክልል ቆቦ ከተማ በአካባቢው ፋኖ ሚሊሻዎችና በመከላከያ ሠራዊት መካከል ትናንት በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ሁለት የካቶሊክ ተራድዖ ድርጅት የረድኤት ሠራተኞችን ጨምሮ በትንሹ አራት ሰዎች እንደተገደሉ ዋሽንግተን ፖስት ከናይሮቢ ዘግቧል። የካቶሊክ ተራድዖ ድርጅት፣ በግጭቱ አንድ የጸጥታ ኃላፊዬና አንድ ሹፌሬ ተገድለውብኛል በማለት ማረጋገጡን ዘገባው ጨምሮ ጠቅሷል። ዜና ምንጩ፣ በዚሁ ግጭት የክልሉ ልዩ ኃይል አባላት እንዳልተሳተፉና ኾኖም ትጥቃቸውን ተገደው ላለመፍታት ሲሉ ከበተማዋ ለቀው መውጣታቸውን ከከተማዋ ነዋሪዎች ሰምቻለሁ ብሏል። በተመሳሳይ ቅዳሜ'ለት በከተማዋ የመከላከያ ሠራዊት እና የፋኖ ሚሊሽያ አባላት ባካሄዱት ተኩስ ልውውጥ፣ ሁለት የፋኖ ሚሊሽያ አባላት መገደላቸውን ነዋሪዎች መናገራቸውን ዜና ምንጩ ገልጧል። የክልሉ መንግሥትም ኾነ ፌደራል መንግሥቱ በቆቦ ከተማ ግጭት ሰዎች ሞተዋል ስለመባሉ፣ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ የሰጡት ማስተባበያም ኾነ ማረጋገጫ የለም።

2፤ በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን የጎንደር ከተማ አስተዳደር የጸጥታ ዕዝ የከተማዋን ሰላምና ጸጥታ ለማስጠበቅ አስፈላጊ ናቸው ያላቸውን ክልከላዎች መጣሉን አስታውቋል። የጸጥታ ዕዙ፣ በከተማዋ መጠጥ ቤቴችና ጭፈራ ቤቶች ከምሽቱ ሦስት ሰዓት በኋላ አገልግሎት እንዳይሰጡ እንዲኹም ባለ ሦስት እግር ባጃጆች ከንጋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ድረስ ብቻ አገልግሎት እንዲሰጡ ደንግጓል። ዕዙ፣ በከተማዋ ከመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች ውጭ ጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ፣ በማናቸውም ጊዜ ጥይት ወይም ሮኬት መተኮስ፣ የመከላከያ፣ ፖሊስና የልዩ ኃይሉን የመለዮ አልባሳት መልበስ፣ ወታደራዊ ሥልጠና መስጠት፣ ያልተፈቀዱ ስብሰባዎችን እና አድማ ማድረግን ጭምር እንደከለከለ አስታውቋል። ከተለያዩ ካምች ወጥተው ወደ ከተማዋ የገቡ የልዩ ኃይል አባላትም በከተማዋ ወደተዘጋጀው ጊዜያዊ ማረፊያ እንዲገቡ ዕዙ ጥሪ አድርጓል። በተያያዘ፣ በክልሉ የተለያዩ ከተሞች የክልሉ ልዩ ኃይል መፍረስ የለበትም የሚሉ የተቃውሞ ሰልፎች ዛሬም ተደርገዋል።

3፤ የሱማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፋ ኡመር ፌደራል መንግሥቱ የክልሎች ልዩ ኃይሎችን መልሶ ለማደራጀት ያወጣውን የጸጥታ መዋቅር ማሻሻያ ዕቅድ የክልሉ መንግሥት ካቢኔ ዛሬ ባደረገው ስብሰባ ላይ ማጽደቁን በትዊተር ገጻቸው ባሠፈሩት መረጃ አስታውቀዋል። የክልሉ ካቢኔ ዕቅዱን ያጸደቀው፣ የክልሎች ልዩ ኃይሎች ከአገሪቱ መከላከያ ሠራዊት ጋር እንዲቀላቀሉ በወጣው ዕቅድ ዙሪያ ገለጻ ከተደረገለት በኋላ መኾኑን ሙስጠፋ ገልጸዋል። የክልሉ ካቢኔ በዕቅዱ ላይ ተወያይቶ ዕቅዱን ያጸደቀው ዛሬ መኾኑን ሙስጠፋ ይግለጡ እንጂ፣ ፌደራል መንግሥቱ ግን የክልሎችን ልዩ ኃይሎች መልሶ የማደራጀቱ ጉዳይ ከሁሉም የክልል መንግሥታትና የክልል ጸጥታ ተቋማት ጋር ቀደም ሲል በተደረጉ ውይይቶች የጋራ ውሳኔ ላይ የተደረሰበት መኾኑን ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በመግለጽ ላይ ይገኛል።

4፤ በትግራይ ክልል ጉብኝት ላይ የሚገኘው የገንዘብ ሚንስቴር ልዐካን ቡድን ዛሬ ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ባለሥልጣናት ጋር ዛሬ መቀሌ ውስጥ መወያየቱን የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል።
የሁለቱ ወገኖች ውይይት የያተኮረው፣ በክልሉ በጦርነቱ በወደሙ መሠረተ ልማቶች መልሶ ግንባታ፣ የጦርነት ተፈናቃዮችን ወደቀያቸው በመመለስ እና የሕክምና መስጫና የትምህርት ተቋማትን እንደገና አገልግሎት በማስጀመር ዙሪያ እንደኾነ የገንዘብ ሚንስትር ደኤታ ሠመሬታ ሰዋሰው መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል። የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ተወካዮችም፣ ፌደራል መንግሥቱ የክልሉን የድጎማ በጀት በቶሎ እንዲለቅ የሚንስቴሩ ልዑካን ቡድን ጥረት እንዲያደርግ መጠየቁን ዘገባው አመልክቷል። የክልሉ የጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አማኑኤል ኃይሌ በበኩላቸው፣ ፌደራል መንግሥቱ ዓለማቀፍ ለጋሾች ለትግራይ ክልል የሕክምና ተቋማት የሚልኳቸው የሕክምና ቁሳቁሶች ወደ ክልሉ እንዳይገቡ የሚያደርጉ መሰናክሎችን እንዲያስወግድ ጠይቀዋል ተብሏል።

5፤ ፍትህ ሚንስቴር በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ወህኒ ቤት በሚገኙ 120 የወንጀል ተከሳሾች ላይ የመሠረታቸውን ክሶች ማቋረጡን የመተከል ዞን ኮምንኬሽን ጽሕፈት ቤት የክልሉን ፍትህ ቢሮ ጠቅሶ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሰራጨው መረጃ ገልጧል። የክሶቹን መቋረጥ ተከትሎ ተከሳሾቹ በሙሉ ከእስር እንደተፈቱ ያመለከተው መረጃው፣ ክሶቹ የተቋረጡት መንግሥት ለተከሳሾቹ በሰጠው ምኅረትና ይቅርታ መሠረት እንደኾነ ጠቅሷል። ተከሳሾቹ በመተከል ዞን ላለፉት ጥቂት ዓመታት ከነበረው ግጭት ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር ውለው ፍትህ ሚንስቴር ጉዳያቸውን ሲከታተለው የቆዩ ናቸው። በዞኑ ከግጭቱ ጋር በተያያዘ የተከሳሾች ክስ ሲቋረጥ የአሁኑ ለሦስተኛ ጊዜ እንደኾነ ተገልጧል።

6፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 53 ብር ከ9847 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ0644 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 64 ብር ከ1401 ሳንቲም እና መሸጫው 65 ብር ከ4229 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ58 ብር ከ9297 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ60 ብር ከ1083 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
344 views17:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 07:58:41 ሰኞ ማለዳ! ሚያዝያ 2/2015 ዓ.ም የEMS Mereja ዕለታዊ ዜናዎች

1፤ በአማራ ክልል ፌደራል መንግሥቱ የክልል ልዩ ኃይሎችን መልሶ የማደራጀት ርምጃ መጀመሩን ተከትሎ ትናንት በተለያዩ የክልሉ ከተሞች የተቃውሞ ሰልፎች እንደተካሄዱ EMS ሰምታለች። በቆቦ ከተማ አቅራቢያ ደሞ፣ በጸጥታ ኃይሎች መካከል የተኩስ ልውውጥ እንደተደረገ ከአካባቢው ነዋሪዎች መረዳት ተችሏል። ባንዳንድ አካባቢዎች የክልሉ ልዩ ኃይሎች ከካምፕ እንደወጡና፣ የክልሉ መንግሥትም የልዩ ኃይሉ አባላት በካምፓቸው እንዲቆዩ ከልዩ ኃይሉ አመራሮች ጋር መወያየቱ ታውቋል። በተያያዘ፣ በክልሉ ምክር ቤት የአብን ተወካዮች የክልሉ ምክር ቤት በጉዳዩ ላይ አስቸኳይ ጉባኤ እንዲቀመጥ በደብዳቤ ጠይቀዋል።

2፤ በአማራ ክልል ጎንደር እና ቆቦ ከተሞች ፌደራል መንግሥት የክልሉን ልዩ ኃይል መልሶ ለማደራጀት የሚያደርገውን እንቅስቃሴ በመቃወም የጥይት ተኩሶችና ተቃውሞዎች እንደነበሩ መስማቱን ጠቅሶ ሮይተርስ ዘግቧል። በጎንደር ከተማ የመንግሥትን ውሳኔ በመቃወም የልዩ ኃይል አባላት ጥይት ወደ ሰማይ ይተኩሱ እንደነበር ምንጮች መናገራቸውን የጠቀሰው ዘገባው፣ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ቢያንስ በስድስት ከተሞች ተቃውሞ እንደተቀሰቀሰ መስማቱን ገልጧል። ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ትናንት ባወጡት መግለጫ፣ የክልል ልዩ ኃይሎችን መልሶ የማደራጀቱን ተልዕኮ "የሚከፍለውን ዋጋ ከፍለንም ቢኾን" እናሳካዋለን ያሉ ሲሆን፣ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለም የፌደራል መንግሥቱ ያሳለፈው ውሳኔ በተዛባ መንገድ ተተርጉሟል ሲሉ የውሳኔውን አስፈላጊነት ለክልሉ ብዙኀን መገናኛ ተናግረዋል።

3፤ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ውሃ ሙሌት በቀጣዩ ክረምት የሚይዘው የውሃ መጠን ከ22 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ወደ 42 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ከፍ እንደሚል ከምንጮች ሰምቻለሁ ሲል ሪፖርተር አስነብቧል። የግድቡ መካከለኛ ክፍል ከፍታ ባለፈው ዓመት ከነበረበት 600 ሜትር ዘንድሮ ወደ 620 ሜትር እንዲኹም የግራ እና ቀኙ ክፍል ከፍታ 633 ሜትር ይደርሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ ምንጮች መናገራቸውንም ዘገባው ጠቅሷል። የግድቡን ግንባታ ቀሪ ሥራዎች ለማጠናቀቅ፣ 60 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ ገንዘብ ያስፈልጋል ተብሏል።

4፤ እናት ፓርቲ ቅዳሜ የምርጫ ቦርድ ታዛቢዎች በተገኙበት ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ከፍተኛ አመራሮቹን መምረጡን በማኀበራዊ ትስስር ገጹ ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል። የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ፣ ዶ/ር ሰይፈሥላሴ አያሌውን የፓርቲው ሊቀመንበር እንዲኹም ጥሩማር አባተን ምክትል ሊቀመንበር አድርጎ መምረጡን ፓርቲው ገልጧል። ፓርቲው፣ የላዕላይ ምክር ቤትና የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትንም መርጫለሁ ብሏል።

5፤ የማኅበረሰብ አንቂና የ"ኢትዮ ንቃት" ዩትዩብ ጣቢያ ባለቤት መስከረም አበራ
ትናንት በፌደራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሏን "ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ዘግቧል። ፌደራል ፖሊሶች መስከረምን ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ሦስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ከመሄዳቸው በፊት፣ በመኖሪያ ቤቷ ብርበራ ማካሄዳቸውን ከቤተሰቧ ማረጋገጡን ዘገባው ጠቅሷል። መስከረም ባለፈው ታኅሳስ ለሁለተኛ ጊዜ ታስራ ሁከት በመቀስቀስ ወንጀል ክስ ከተመሠረተባት በኋላ፣ በ50 ሺህ ብር ዋስትና መፈታቷ ይታወሳል። መስከረም በዩትዩብ ጣቢያዋ ካደረገችው ንግግር ጋር በተያያዘ ስትታሠር የትናንቱ ለሦስተኛ ጊዜ ነው። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
364 views04:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 08:57:55 የኢትዮጵያ ሠራዊት በብሔራዊ ደረጃ የተደራጀበትን ታሪክ ከተመለከትን የተለያዩ ወታደራዊ አደረጃጀቶችን ወደ ብሔራዊ የመከላከያ ሠራዊት በማዋሐድ የተከናወነ መሆኑን እናያለን። የሌሎች ሀገሮች ታሪክም ተመሳሳይ ነው። ከብሔራዊ የመከላከያ ሠራዊት ውጭ የሆኑ አደረጃጀቶች በተለያየ የታሪክ አጋጣሚ ሊፈጠሩ ይችላሉ። በዐማጽያን ትግል ምክንያት የሚፈጠርበት ጊዜ አለ። እነዚህ ዐማጽያን ወደ ሰላማዊ መንገድ ሲመለሱ ከሚከናወኑ ተግባራት አንዱ የታጠቁ አካላትን መርምሮና መልምሎ ወደ መከላከያ ሠራዊትነት መቀላቀል ነው። በ1983 ዓ.ም. መከናወን ነበረበት ብለን ለብዙ ዓመታት በተደጋጋሚ የኮነንነው አንዱ ጉዳይ ይሄ ነበር።
በሌላ በኩል ደግሞ ሀገር ፈተና ላይ ስትወድቅ የሚፈጠሩ ወታደራዊ አደረጃጀቶችም ይኖራሉ። ኢትዮጵያ በፋሺስት ጣልያን በተወረረችበት ጊዜ በታዋቂ ዐርበኞች ሥር የተፈጠሩ ወታደራዊ አደረጃጀቶች ለዚህ ምሳሌ ናቸው። ኢትዮጵያ ሀገራችን በፋሺስት ጣልያን በተወረረች ጊዜ የተለያዩ የዐርበኛ መሪዎች ጦር አደራጅተው በዱር በገደሉ ዘምተው ነበር። ጣልያን ድል ሆኖ ነጻነት ሲመለስ ከፊሎቹ ወደ መከላከያ ሠራዊት ሲገቡ፣ ሌሎች ወደ ሲቪል ሕይወት ተመልሰዋል።
ዛሬም የየክልሉ ልዩ ኃይሎችን እስከ ዛሬ ለሰጡት አገልግሎት አመስግነን፣ ወደ ሌሎች የጸጥታ መዋቅሮች የምናካትትበት ወቅት ላይ እንገኛለን። ይህ ውሳኔ በሁሉም ክልል አመራሮች በጋራ የተወሰነና በጋራ የሚተገበር ነው። አብዛኞቹ ክልሎችም ሠራዊት ለማስተዳደር የሚያስችል የኢኮኖሚ ዐቅም የላቸውም። ሁሉም ለማለት በሚያስደፍር ሁኔታ በፌዴራል መንግሥት ከሚሰጣቸው በጀት ለልዩ ኃይላቸው የሚጠቀሙ ናቸው። የዚህ ወይም የዚያ ክልል ልዩ ኃይል ብቻውን ትጥቅ ሊፈታ ነው፤ የዚህኛው ክልል ይቆይ ተብሏል፤ ይሄን ወይም ያንን ሕዝብ ለመጉዳት የተደረገ ነው የሚሉ ውዥንብሮችን የሚነዙ አካላት ገሚሶቹ ባለማወቅ ሲሆን፤ የተቀሩት ዓላማቸው ሕዝብ ከማበጣበጥ የዘለለ አይደለም። ጥቂት የማይባሉትም የክልል ልዩ ኃይል መፍረስ አለበት ብለው ሲጽፉና ሲሞግቱ የከረሙ ናቸው፤ ጠለቅ ብለን ብንፈትሻቸው፥ ይሁን ሲሏቸው አይሁን፣ አይሁን ሲሏቸው ይሁን የማለት ልማድ የተጠናወታቸው ሆነው እናገኛቸዋለን።
ከዚህ በኋላ ክልሎች የፖሊስ ኃይላቸውን አጠናክረው ወንጀልን በመከላከልና አካባቢያዊ ጸጥታን በማስከበር ላይ ብቻ ያተኩራሉ። ከየትኛውም ኃይል የሚሰነዘር፣ የሀገርን ድንበር፣ ህልውናና ሉዓላዊነት የሚዳፈር ኃይል ሲነሣ ደግሞ የመከላከያ ሠራዊቱ እርምጃ ይወስዳል። ለዚህ የሚሆን አደረጃጀትም በተግባር ላይ ውሏል። የክልሎች ፉክክርና ትብብር በልዩ ኃይል ግንባታ ሳይሆን በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊ ልማትና በዴሞክራሲያዊ ባህል ላይ ይሆናል። ይህ ውሳኔም ለኢትዮጵያ ኅብረ ብሔራዊ አንድነትና ለሕዝቡ ሰላም ሲባል ዋጋ ተከፍሎም ቢሆን ተግባራዊ ይደረጋል። ሳይገባቸው የሚቃወሙትን ለማስረዳትና ለማሳመን ጥረት እናደርጋለን። ሆን ብለው የአፍራሽነት ሚና በሚጫወቱት ላይ ደግሞ ተገቢው የሕግ ማስከበር እርምጃ ይወሰዳል። ለዚህም በቂ ዝግጅት ተደርጓል። በመሆኑም የሚመለከታቸው ተቋማትና ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በአጠቃላይ፣ የውሳኔውን ሃገራዊ ፋይዳና የሚያስገኘውን ዘላቂ ጥቅም ከግምት በማስገባት ለተግባራዊነቱ ርብርብ እንድታደርጉ በዚሁ አጋጣሚ ጥሪዬን አቀርባለሁ።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
መጋቢት፣ 2015 ዓ.ም
ጠ/ሚንስተር ዶ/ር ዐብይ አህመድ አሊ
#ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
394 views05:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-05 07:31:44 ረቡዕ ማለዳ! መጋቢት 27/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ አብን የገዥው ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የአማራ ክልል ልዩ ኃይልን ለማፍረስ ያሳለፈው ውሳኔ "ወቅቱን ያልጠበቀ፣ ነባራዊ ሁኔታዎችን ከግምት ያላስገባና ለጥቃት ተጋላጭ የኾኑ አካባቢዎችን ተገማችና ቀጥተኛ ለኾነ ጥቃት የሚዳርግ" መኾኑን በመግለጽ ውሳኔውን ውድቅ እንዳደረገው አስታውቋል። ውሳኔው ክልሉን "ለሥርዓት አልበኝነትና ለሽብርተኛ ኃይሎች መፈንጫነት የሚያመቻች" መኾኑን የገለጠው አብን፣ የክልል ልዩ ኃይሎችን የማፍረስና ያለማፍረስ ጉዳይ በአገራዊ ምክክሩ ሂደት መታየት እንዳለበት አውስቷል። አብን፣ የአማራ ክልል መንግሥት "ትጥቅ አስፈቺው ውሳኔ" እንዳይተገበር የማድረግ ሃላፊነት አለበት ብሏል።

2፤ በኤርትራ ደኅንነት ሚንስትር የተመራ የኤርትራ ወታደራዊ ልዑካን ቡድን ትናንት ቢሾፍቱ የሚገኘውን የኢትዮጵያ አየር ኃይልን መጎብኘቱን የኤርትራ መንግሥት ቃል አቀባይ የማነ ገ/መስቀል በትዊተር ገጻቸው ገልጸዋል። ልዑካን ቡድኑ በተመሳሳይ፣ በኦሮሚያ ክልል የስንዴ ማሳዎችን፣ የግብርና ማቀነባበሪያ፣ የምግብ ዋስትና ፕሮጀክቶችንና የኢንዱስትሪ ተቋማትን መጎብኘቱን የማነ ገልጸዋል። በሌላ ዜና የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ኦስማን ሳለህ ሰኞለ'ት ወደ ጁባ አቅንተው፣ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ የላኩትን መልዕክት ለፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር እንደሰጡና ከፕሬዝዳንቱ ጋር በሁለትዮሽና ቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ እንደተወያዩ ተገልጧል።

3፤ የተመድ ሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት በአገራት ላይ የሚጣሉ የተናጥል ማዕቀቦች በሰብዓዊ መብቶች ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንዳላቸው የሚገልጽ የውሳኔ ሃሳብ ትናንት በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል። የውሳኔ ሃሳቡን ሁሉንም አባል የአፍሪካ አገራት ጨምሮ 33 አገራት የደገፉት ሲሆን፣ ሌሎች 13 አባል አገራት ደሞ ተቃውመውታል። ምክር ቤቱ የውሳኔ ሃሳቡን ያጸደቀው፣ ለበርካታ ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን ዓመታዊ ጉባዔውን ማጠናቀቂያ ላይ ነው። ከምክር ቤቱ 47 አባል አገራት ሜክሲኮ ብቻ ድምጸ ተዓቅቦ አድርጋለች።

4፤ የሩሲያው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ አሜሪካ በመጭው ሐምሌ የሚካሄደውን የሩሲያና አፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ለማስተጓጎል ጥረት እያደረገች ነው በማለት መክሰሳቸውን ሮይተርስ ዘግቧል። አሜሪካ እያደረገችው ያለችው ዋናው ጥረት፣ የአፍሪካ አገራት በፒተርስበርግ ከተማ በሚካሄደው የመሪዎች ጉባኤ ላይ እንዳይገኙ የማሳመን ጥረት መኾኑን ላቭሮቭ መጠቆማቸውንና፣ የዚሁ ጥረት ዋና ዓላማ ሩሲያን ከዓለማቀፉ ኅብረተሰብ መነጠል መኾኑን ባንድ ቃለ ምልልሳቸው መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል። #ሼር በማድረግ ተባበሩኝ


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
11 views04:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-04 20:50:37 ማክሰኞ ምሽት! መጋቢት 26/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ የጸጥታና ደኅንነት ግብረ ኃይል " በመንግሥት ባለስልጣናትና በከተሞች ላይ በጦር መሳሪያ የታገዘ ጥቃት ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ ደርሼባቸዋለሁ" ያላቸውን ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር አውያለሁ ማለቱን ፋና ብሮድካስት ዘግቧል። ምሁራን፣ የመገናኛ ብዙኀን ባለቤቶችና የማኅበረሰብ አንቂዎች የታቀፉባቸው ናቸው የተባሉት ኅቡዕ ቡድኖች፣ ጥቃቱን ሊፈጽሙ ያቀዱት በአዲስ አበባ፣ ባሕርዳር፣ አዳማ እና ድሬዳዋ እንደነበር ግብረ ኃይሉ መግለጡን ዘገባው ጠቅሷል። በቁጥጥር ስር ከዋሉት መካከል፣ ዶ/ር ወንደወሰን አሠፋ፣ ረዳት ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቸው፣ ፕሮፌሰር ማዕረጉ ቢያበይን እና ዶ/ር መሠረት ወርቁ የተባሉ ተጠርጣሪዎች እንደሚገኙበትና በአንዳንዶቸ ተጠርጣሪዎች እጅ ጦር መሳሪያዎች እንደተያዙ ዘገባው አመልክቷል። ተጠርጣሪዎቹ " የአማራ ሕዝብ በከፍተኛ ጭቆና ውስጥ ይገኛል" በማለት፣ "ሕዝብን በሐይማኖት፣ በብሄርና በጽንፈኛ የፖለቲካ ዓላማ ዙሪያ ደጋፊ ለማሰባሰብ ሲሞክሩ ነበር" ተብሏል።

2፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ ከኦሮሚያ ክልል የተመረጡትን አባሉን ዶ/ር ጫላ ዋታን ያለመከሰስ መብት በአንድ ድምጸ ተዓቅቦ አንስቷል። ጫላ ያለመከሰስ መብታቸው የተነሳው፣ የሁሌ ቦራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት በነበሩበት ወቅት ከመንግሥት የግዥ ሥርዓት ውጭ ፈጽመውታል ተብለው በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል መኾኑን ለምክር ቤቱ የውሳኔ ሃሳቡን ያቀረበው የሕግና ፍትህ ቋሚ ኮሚቴ አስረድቷል። ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ የወንጀል ተጠርጣሪው ጫላ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ስለመዋላቸው አልታወቀም።

3፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሌሊሴ ደሳለኝን የከፍተኛው ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት እና ዘሃራ ኡመርን የፍርድ ቤቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ኾነው እንዲሾሙ የቀረበለትን የውሳኔ ሃሳብ በሁለት ድምጸ ተዓቅቦ አጽድቋል። ሌሊሴ የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤትን ጨምሮ በተለያዩ የክልሉና ፌደራል ፍርድ ቤቶች በዳኝነት እንዲሁም ባንድ ወቅት በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በምክትል ፕሬዝዳንትነት ማገልገላቸው የተገለጠ ሲሆን፣ ዘሃራ ደሞ በሱማሌ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በተለያዩ ኃላፊነቶች ማገልገላቸው ተጠቅሷል። ሌሊሴና ዘሃራ የተሾሙት፣ የፍርድ ቤቱ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ብርሃን መስቀል ዋጋሪና ምክትል ፕሬዝዳንት ተናኘ ጥላሁን በፍቃዳቸው ከሃላፊነት በመልቀቃቸው እንደኾነ ተዘግቧል።

4፤ የአውሮፓ ኅብረት የውጭ ግንኙነት ኃላፊ ጆሴፕ ቦሬል ኅብረቱ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ግንኙነት "በሂደትና ደረጃ በደረጃ" ከሰሜኑ ጦርነት በፊት ወደነበረበት እንደሚመልስ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል። ቦሬል፣ አውሮፓ ኅብረት ከኢትዮጵያ ጋር ስለሚኖረው ግንኙነት ዛሬ መግለጫ የሰጡት፣ ብራስልስ ውስጥ ከአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን ጋር ከተወያዩ በኋላ ነው። የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት በመንግሥትና ሕወሃት መካከል በተፈረመ ሰላም ስምምነት መቋጨቱ አዎንታዊ ክስተት መኾኑን የጠቀሱት ቦሬል፣ የሰላም ስምምነቱ ዘላቂ እንዲኾን ኅብረቱ ከአሜሪካ መንግሥት ጋር በትብብር መስራት እንደሚቀጥል ተናግረዋል። ቦሬል፣ አውሮፓ ኅብረት የሰላም ስምምነቱን አፈጻጸም በቅርበት በመከታተል ላይ እንደኾነ የኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥትና የትግራይ ክልል አመራሮች እንዲረዱትም አሳስበዋል።

5፤ ኢትዮ ቴሌኮም የኢንተርኔት ግንኙነት ያለ "ቪፒኤን" ለማድረግ እንደተቸገረ ተደርጎ በማኅበራዊ ትስስር ገጾች የተሠራጨው መረጃ "የተሳሳተ ነው" ሲል ዛሬ በትዊተር ገጹ ባስተላለፈው መልዕክት አስታውቋል። ኢትዮ ቴሌኮም ያለ "ቪፒኤን" የኢንተርኔት ግንኙነት ለማድረግ "ተጨማሪ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እንዳስፈለገው" ተደርጎ የተሠራጨው መረጃም ሐሰት መኾኑን ጨምሮ ገልጧል። ኢትዮጵያ ውስጥ ምክንያቱ ባልተገለጠ ሁኔታ የፌስቡክ፣ ቴሌግራምና ዩትዩብ ማኅበራዊ መገናኛ አገልግሎቶች ከተገደቡ ሁለት ወር የተቆጠረ ሲሆን፣ ደንበኞች የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎቹን የሚጠቀሙት "በቪፒኤን" በመግባት ብቻ ነው። የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎቹ ለምን እንደተገደቡ፣ ኩባንያው ያለው ነገር የለም።

6፤ በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኢምባሲ ከጅቡቲ የቀይ ባሕር ዳርቻ 142 ፍልሰተኞችን መታደግ እንደተቻለ ዛሬ በትዊተር ገጹ ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል። ፍልሰተኞችን መታደግ የተቻለው፣ ፍልሰተኞቹ በሕገወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች አማካኝነት በጀልባዎች ቀይ ባሕርን አቋርጠው ወደ የመን ለመሻገር ሲሞክሩ መኾኑን ኢምባሲው ገልጧል። ኢምባሲው፣ ፍልሰተኞቹን ሊያሻግሩ የነበሩ ሕገወጥ የሰው አዘዋዋሪዎችም በቁጥጥር ስር እንደዋሉ የገለጠ ሲሆን፣ በቁጥጥር ስር የዋሉትን ሕገወጥ የሰው አዘዋዋሪዎች ብዛትና ዜግነታቸውን ግን አልጠቀሰም።

7፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 53 ብር ከ9302 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ0088 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 63 ብር ከ6169 ሳንቲም እና መሸጫው 64 ብር ከ8892 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ58 ብር ከ5844 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ59 ብር ከ7561 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። ሼር በማድረግ ተባበሩኝ


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
101 views17:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ