Get Mystery Box with random crypto!

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ) Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ)
የሰርጥ አድራሻ: @zemedkun_zemede
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.26K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 15

2023-03-28 07:45:08 ማክሰኞ ማለዳ! መጋቢት 19/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ በደቡብ ክልል ጌዲኦ ዞን ከሚገኙ 320 ትምህርት ቤቶች መካከል የትምህርት ሚንስቴርን መመዘኛ የሚያሟሉት 13ቱ ብቻ እንደኾኑ ዋዜማ ከዞኑ ትምህርት ቢሮ ሰምታለች። የትምህርት ቤት ግንባታ ጥራት ጉድለት፣ የሰው ኃይልና የቤተመጽሃፍት እጥረትና የትምህርት አመራርና አስተዳደር ጉድለት ዋነኞቹ የዞኑ ትምህርት ቤቶች ችግሮች ናቸው። በዘንድሮው ዓመት በዞኑ ለመማር ከተመዘገቡት 266 ሺህ 700 ተማሪዎች መካከል፣ ከ18 ሺህ በላይ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቋርጠዋል ተብሏል። ተማሪዎች ትምህርታቸውን ከሚያቋርጡባቸው ምክንያቶች መካከል፣ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች በአካባቢው የሚያደርጉት እንቅስቃሴ አንዱ እንደኾነ መረዳት ተችሏል።

2፤ የአማራ ክልል ልዩ ኃይል የቀድሞ ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጀኔራል ተፈራ ማሞ በውጭ አገር ሕክምና እንዳያገኙ ተከልክለዋል በማለት ቤተሰቦቻቸው ክስ ሊመሠርቱ መሆኑን ቪኦኤ ዘግቧል። ብ/ጀኔራል ተፈራ ወደ ውጭ አገር ሂደው ሕክምና እንዲያገኙ የሐኪሞች ቦርድ ትዕዛዝ የጻፈላቸው፣ ከአራት ወራት በፊት እንደነበር መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ብ/ጀኔራል ተፈራ ለሕክምና ሊጓዙ የነበሩት ወደ እስራኤል እንደነበር የተናገሩት ባለቤታቸው መነን ኃይሌ፣ የውጭ ጉዞ ክልከላ ትዕዛዙ የመጣው "ከበላይ አካል" ስለመሆኑ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ እንደተነገራቸው ገልጸዋል ተብሏል።

3፤ የፌደራል የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን በሰሜኑ ጦርነት በትግራይ፣ አማራና አፋር ክልሎች ለተጎዱ ዕርዳታ ፈላጊዎች 282 ሺህ 934 ሜትሪክ ቶን ዕርዳታ ማሰራጨቱን መናገሩን ፋና ብሮድካስት ዘግቧል። መንግሥት ብቻውን ያቀረበው፣ 15 ሺህ 666 ሜትሪክ ቶን ሰብዓዊ ዕርዳታ እንደኾነ የጠቀሰው ኮሚሽኑ፣ ቀሪውን ዕርዳታ ያቀረቡት ዓለማቀፍ ረድዔት ድርጅቶችና አጋሮች እንደኾኑ ገልጧል ተብሏል። ኮሚሽኑ ባሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል ከ5 ነጥብ 2 በላይ ዕርዳታ ፈላጊዎች፣ በአማራ ክልል ከ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ እንዲሁም በአፋር ክልል ከ715 ሺህ በላይ ዕርዳታ ፈላጊዎች እንደሚገኙ መግለጡን ዘገባው አመልክቷል።

4፤ የሱማሊያ ፌደራል መንግሥት የወከላቸው አሸማጋዮች ግጭት በተቀሰቀሰባት ሱማሌላንድ ራስ የሽምግልና እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ይገኛሉ። ከሱማሊያ የጎሳ ሽማግሌዎች የተውጣጡት አሸማጋዮቹ፣ የግጭት ቀጠና በሆነችው ላስ አኖድ ከተማ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን በማነጋገር ላይ እንደኾኑ የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። በሱማሌላንድ መንግሥት ወታደሮችና በሱማሌላንድ ስር መተዳደር አንፈልግም በሚሉ የላስ አኖድ ከተማ የአካባቢ የጎሳ ሚሊሻዎች መካከል የተፈጠረው ግጭት ሁለተኛ ወሩን የያዘ ሲሆን፣ ለግጭቱ እስካሁን ፖለቲካዊ መፍትሄ አልተገኘለትም።

5፤ የሱዳን ወታደራዊና የፖለቲካ ኃይሎች ሁለተኛውን ሲቪል የሽግግር መንግሥት ለመመስረት ወደ መጨረሻው ምዕራፍ ተቃርበዋል። ቅዳሜ እና ዕሁድ በረቂቅ የስምምነት ሰነድ ላይ የተወያዩት ወታደራዊ መሪዎችና የሲቪል የፖለቲካ ኃይሎች ተወካዮች፣ ረቂቅ የስምምነት ሰነዱን ከድርድር ሂደቱ ውጭ ለሆኑ የፖለቲካ ኃይሎች ለመስጠት መስማማታቸውን ሱዳን ትሪቡን ዘግቧል። የወታደራዊው መንግሥትና ሲቪል የፖለቲካ ኃይሎቹ፣ ሰነዱን መጋቢት 23 ቀን ለመፈረም ቀጠሮ ይዘዋል። ኾኖም ከግብጽ ጋር ግንኙነት ያላቸው የተወሰኑ ታጣቂና የፖለቲካ ቡድኖች የሲቪል ሽግግር መንግሥት ምስረታውን የድርድር ሂደት እስካሁን አለመቀላቀላቸው ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል። #ሼርርር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
170 views04:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 21:05:01 ሰኞ ምሽት መጋቢት 18/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ነገ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሪፖርት እንደሚያቀርቡና ሪፖርቱን ተከትሎ የምክር ቤቱ አባላት ለሚያቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እንደሚሰጡ ምክር ቤቱ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል። ለጠቅላይ ሚንስትሩ ጥያቄና ማብራሪያ የሚቀርብላቸው፣ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሆነ ምክር ቤቱ ገልጧል። ዐቢይ፣ በተያዘው ዓመት ባለፈው ኅዳር ወር በምክር ቤቱ ተገኝተው ለጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ መስጠታቸው ይታወሳል። ዐቢይ፣ ነገ ለምክር ቤቱ አባላት ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡት፣ ምክር ቤት በ61 ተቃውሞ ሕወሃትን ከአሸባሪነት ፍረጃ በሰረዘ ማግስት ነው።

2፤ የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን በብሄራዊ ምክክሩ ለመሳተፍ ፍቃደኛ ያልሆኑ 13 የፖለቲካ ኃይሎችን ለማግባባት ላለፉት 6 ወራት ያደረጋቸው ሙከራዎች እንዳልተሳኩ ዋዜማ ከምንጮቿ ሰምታለች። "ቡድን 13" ተብለው የሚጠሩት እነዚሁ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በአገራዊ ምክክሩ አንሳተፍም ያሉት፣ በምክክር ኮሚሽኑ የፖለቲካ ገለልተኛነት እና በኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች አሿሿም ሂደት ላይ ጥያቄ በማንሳት ነው። ከአገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ጋር ለመስራት ፍቃደኛ ካልሆኑ ፓርቲዎች መካከል፣ ኦፌኮ፣ ኦነግ፣ የአፋር ሕዝብ ፓርቲ፣ የሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ እና ኦብነግ ይገኙበታል። የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤትም፣ ፓርቲዎቹ ወደ አገራዊው የምክክሩ ማዕቀፍ እንዲገቡ ጥረት እያደረገ መኾኑን የምክር ቤቱ ሊቀመንበር መብራቱ ዓለሙ ለዋዜማ ተናግረዋል።

3፤ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚንቀሳቀሱ ስምንት ፓርቲዎች ከግንቦት 30 በፊት በክልሉ ምርጫ እንዲካሄድ ለምርጫ ቦርድ ደብዳቤ ማስገባታቸውን የዋዜማ ሪፖርተር ዘግቧል። ጥያቄውን ለቦርዱ ካስገቡት ፓርቲዎች መካከል፣ ገዥው ብልጽግና ፓርቲ ይገኝበታል። ፓርቲዎቹ በክልሉ በ2013ቱ አገር ዓቀፍ ምርጫ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ለክልል ምክር ቤቶች ከተያዙ አብዛኞቹ ምርጫ ክልሎች ሳይካሄድ የቀረው ምርጫ ከዘንድሮው ክረምት መግባት በፊት እንዲካሄድ የጠየቁት፣ የክልሉ የጸጥታ ሁኔታ ተሻሽሏል በማለት ነው። ምርጫ ቦርድ ምርጫ ማድረግ የሚጠበቅበት፣ በ71 የክልል ምክር ቤትና በ6 የየሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ክልሎች ነው።

4፤ የከፍተኛ ትምህርት ምዘናና የፈተናዎች አገልግሎት የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል አገር ዓቀፍ መልቀቂያ ፈተና ልክ እንደ ባለፈው ዓመት ሁሉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቅጥር ግቢ ውስጥ እንደሚሰጥ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ማስታወቁን የአገር ውስጥ ዜና አውታሮች ዘግበዋል። ተቋሙ ለዘንድሮው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ምዝገባ ከቀጣዩ ረቡዕ ጀምሮ እስከ ሚያዝያ 15 ድረስ እንደሚካሄድና፣ በጠቅላላው 1 ሚሊዮን ተፈታኞች ይመዘገባሉ የሚል ቅድመ ግምት እንደተያዘ መግለጡን ዘገባዎቹ አመልክተዋል። የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል አገር ዓቀፍ ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ ግን፣ የተፈታኞች ትክክለኛ ብዛት ከታወቀ በኋላ እንደሚወሰን ተቋሙ ገልጧል ተብሏል።

5፤ ጎረቤት ኬንያ ዛሬ በከፍተኛ ሁከት የታጀቡ ጸረ-መንግሥት የተቃውሞ ሰልፎችን አስተናግዳለች። የተቃውሞ ሰልፉ በተለይ በዋና ከተማዋ ናይሮቢ እና የኦዲንጋ የድጋፍ መሠረት በሆነችው ኪሱሙ ከተሞች በርትቷል። የተወሰኑ ሰልፈኞች ናይሮቢ ውስጥ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪው ራይላ ኦዲንጋ ቤተሰብ ንብረት በሆነ አንድ ኩባንያ ላይ ጥቃት የፈጸሙ ሲሆን፣ ሌሎች የተደራጁ ቡድኖች ደሞ በቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ቤተሰብ ንብረት በሆነ ኩባንያ ላይ ዝርፊያ እንደፈጸሙ የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ፖሊስ የሰልፉ መሪ ኦዲንጋ የተሳፈሩባቸውን መኪኖች ጨምሮ፣ በሰልፈኞቹ ላይ አስለቃሽ ጭስ እንደተኮሰ ተገልጧል። ኦዲንጋ በሳምንት ሁለት ጊዜ አገር ዓቀፍ የተቃውሞ ሰልፍ የጠሩት፣ ለአገሪቱ የኑሮ ውድነት መንግሥትን ተጠያቂ በማድረግና የባለፈው ነሐሴ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ተጭበርብሯል በማለት ነው።

6፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 53 ብር ከ8752 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 54 ብር ከ9527 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 62 ብር ከ7288 ሳንቲም እና መሸጫው 63 ብር ከ9834 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ57 ብር ከ7542 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ58 ብር ከ9093 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼርርር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
194 views18:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 07:24:32 ሰኞ ማለዳ! መጋቢት 18/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1. የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከናይጀሪያ አየር መንገድ ጋር በፈጠረው ስምምነት መሠረት ከበረራ ውጭ የሆነውን የናይጀሪያ አየር መንገድ መልሶ በማቋቋም በመጭው ግንቦት በረራ ሊያስጀምር መሆኑን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። አዲስ በሚቋቋመው የናይጀሪያ አየር መንገድ ውስጥ፣ የኢትዮጵያ አዩር መንገድ 49 በመቶ፣ ናይጀሪያዊያን ባለሃብቶች 46 በመቶ እንዲሁም የናይጀሪያ መንግሥት ቀሪውን 5 በመቶ የባለቤትነት ድርሻ እንዲይዙ ስምምነት ላይ እንደተደረሰ ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። አየር መንገዱን እንደገና በረራ ለማስጀመር የታቀደው፣ በ23 አውሮፕላኖች እንደሆነ ተገልጧል። የናይጀሪያ አየር መንገድ ከባድ ሙስና ባደረሰበት ኪሳራ ሳቦያ፣ ከበረራ ውጭ የሆነው ከ20 ዓመት በፊት ነበር።

2፤ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የአዲስ አበባ አገረ ስብከት የካቲት 23 ቀን በፒያሳው ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ላይ አስለቃሽ ጭስ የተኮሱ አካላት አጣርቶ ለሕዝብ ይፋ የሚያደርግ የሕግ ባለሙያዎች ቡድን ማቋቋሙን አስታውቋል። አገረ ስብከቱ፣ በአዲሱ ሸገር ከተማ ስር ከተካለሉ ቤተክርስቲያናት መካከል መንግሥት በግብረ ኃይሉ ያስፈረሰውን አንድ የጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን በራሱ ወጭ መልሶ እንዲያስገነባም አሳስቧል። አገረ ስብከቱ ጨምሮም፣ በቤተክርስቲያናት ላይ የሚፈጸመው "አድሏዊ" እና "ኢ-ሕገመንግሥታዊ" ድርጊት እንዲቆም ጠይቋል።

3፤ ብሄራዊ ባንክ ሦስት አዳዲስ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን መንደፉን ሪፖርተር አስነብቧል። ማሻሻያዎቹ የባንኩን ተቋማዊ ነጻነትና የቁጥጥር ሥልጣን በማጠናከር፣ የሰው ኃይልና ዲጂታል አቅሙን በማሳደግና የገንዘብ ፖሊሲውን በማሻሻል ላይ ያተኮሩ እንደሆኑ ዘገባው ጠቅሷል። የባንኩ ገዥ ማሞ ምኅረቱ፣ በሦስት ዓመታት ውስጥ 70 በመቶ ኢትዮጵያዊያን ለባንኩ የፋይናንስ አገልግሎት ተደራሽ እንዲኾኑ ግብ እንደተያዘ መጋቢት 14 ቀን በተካሄደ አንድ መድረክ ላይ መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ብሄራዊ ባንክ ለሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኩባንያ የሞባይል ገንዘብ ዝውውር ፍቃድ በቅርቡ እንደሚሰጥም ማሞ ተናግረዋል ተብሏል።

4፤ በሜጀር ጀኔራል ተስፋዬ አያሌው የተመራ የኢትዮጵያ ጦር ሠራዊት የከፍተኛ መኮንኖች ልዑክ ቅዳሜ'ለት በማዕከላዊ ሱማሊያ የሒራን ግዛት ከተማ በለደወይን መግባቱን የሱማሊያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የኢትዮጵያ ጦር ሠራዊት ልዑክ ወደ ሱማሊያ ያቀናው፣ የሱማሊያ መንግሥት በአልሸባብ ላይ ሁለተኛውን ዙር የማጥቃት ዘመቻ በሚያውጅበት ዋዜማ ላይ ነው። ልዑኩ ከሱማሊያ ጦር ሠራዊት አቻዎቹ ጋር እንደሚወያይና፣ ኢትዮጵያ በቅርቡ ወደ ሱማሊያ ያዘመተቻቸው ቁጥራቸው ያልተገለጹ ወታደሮች ከአልሸባብ ጋር ለመዋጋት ያላቸውን ዝግጁነት እንደሚገመግም ዘገባዎቹ አመልክተዋል። ከልዑካን ቡድኑ ጋር የተወሰኑ የሱማሌ ክልል ባለሥልጣናት አብረው ተጉዘዋል ተብሏል።

5፤ የሱዳን ወታደራዊ መሪዎችና ሲቪል ተቃዋሚ የፖለቲካ ኃይሎች ትናንት ምሽት በዓለማቀፍ አደራዳሪዎች አማካኝነት ባደረጉት ስብሰባ ላይ የመጨረሻው የሲቪል ሽግግር መንግሥት ማቋቋሚያ ረቂቅ ሰነድ ተጠናቆ መቅረቡን የሱዳን ዜና ወኪል ዘግቧል። በስምምነት ረቂቅ ሰነዱ ላይ ገና በድርድር ላይ ያለው የጸጥታ መዋቅር ማሻሻያ ከታከለበት በኋላ፣ መጋቢት 23 እንደሚፈረም ዘገባው ጠቅሷል። ተሰብሳቢዎቹ፣ የመጀመሪያውን የፖለቲካ ማዕቀፍ ስምምነት ያልፈረሙ ኃይሎች የፖለቲካ ንግግር ሂደቱን ተቀላቅለው የመጨረሻውን ስምምነት እንዲፈርሙ ጥሪ ማድረጋቸው ተገልጧል። የስምምነት ማዕቀፉ አካል ያልሆኑት ቡድኖች ግን፣ ለፊርማ የተቃረበውን የሲቪል መንግሥት ማቋቋሚያ ሰነድ እንደማይቀበሉት በመግለጽ ላይ ናቸው። #ሼርርር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
229 views04:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 21:25:57 """"""""""ሁሉም ሰው ገነት መግባት ይፈልጋል፣ ነገር ግን መሞት አይፈልግም።
የእነዚህ ትግራይ የሚገኙ የኃይማኖት አባቶች ጉዳይ ደግሞ ከመጠን በላይ ግራ የሚያጋባ ነው። በጣም!

1) ብዙ ነገሩ ፖለቲካ ነው። ስለ እምነት ሳይሆን ስለጦርነቱ በስፋት ያነሳሉ። ጦርነቱን ይመሩ የነበሩት ፖለቲከኞች ግን ታርቀዋል። ጌታቸው ረዳ አራት ኪሎ ነው። ፖለቲከኞቹ ሲታረቁ፣ የቤተ ክርስቲያን ሰዎች ለምን ተገንጣይነትን ይሰብካሉ? ምዕመኑ ወደ መሃል አገር እየጎረፈ እነሱ የጦርነቱ ወቅት ላይ ናቸው።

2) ከሲኖዶሱ ጋር የማይነጣጠሉበት፣ መነጣጠልም የማይፈልጉበት ጉዳይ አለ። በጀት ይፈልጋሉ። ትዕዛዝ አንቀበልም ይላሉ። በጦርነቱ ወቅት ጨምሮ ደሞዝ አልተቋረጠም። ሲኖዶሱ ደሞዝ እየላከ ነው። ግን በራሳቸው ይወስናሉ። ደሞዝ ስጡን እንጅ፣ ከእናንተ ጋር ጉዳይ የለንም ይባላል?

3) በደል በሞላበት ኢትዮጵያ በደልን
የኃይማኖታዊ ማኩረፊያ አድርጎ መውሰድ ምክንያታዊ አይደለም። ጦርነቱ ያልጎዳው የለም። በአማራም በአፋርም የእምነት ተቋማት፣ የኃይማኖት አባቶች፣ ምዕመናን ተጎድተዋል። ኦሮሚያ ክልል ቤተ ክርስቲያን ስትነድ ነው የከረመችው። ሲኖዶሱ ታንክና ድሮን አላከም። ማኩረፊያው ራሱ ትክክል አይደለም። በየአገሩ በደል ሲበዛስ ተነጥሎ ኩርያ ነው መፍትሄው?

4) በጣም አደገኛው ይህ ፕሮጀክት የፅንፈኛ ብሔርተኛ ፕሮጀክት መሆኑ ነው። መጀመርያ የትግራይ ቤተ ክርስቲያን ብለው የጀመሩት በውጭ አገር ነው። አርብና ሮብን የማይፆሙ ብቻ ሳይሆን መገዳደልን የሚሰብኩ እምነት አልባ ፖለቲከኞች የጀመሩትን ፕሮጀክት የሲኖዶስ ደሞዝ እየተቀበሉ ማስቀጠል ኃይማኖታዊ ነው?

የቤተ ክርስቲያን አንድነት ከተባለ ትህነግ ታርቆ፣ የተነጣይነት ባህሪን ያልተው ኃይማኖተኞችም ተው እንጅ መባል አለባቸው።

ያ ሲዘልል የነበረው ብሔርተኛ ሁሉ ስለ እርቀ ሰላም እያወራ፣ ኮሚኒስት ነኝ የሚለው ትህነግ ለጊዜውም ቢሆን እየተደራደረ የኃይማኖት አባት ከራሱ ተቋም ጋር ከደሞዝ ውጭ የሚያገናኘን ነገር የለም አይነት እርምጃ ሲመርጥ ግራ ያጋባል። አሳዛኝም ነው።

5) በማንነት ከሆነ ፓትሪያርኩም አምስት ኪሎ ነው ያሉት። በጦርነቱ ወቅት አንዱን የሚያስደስት ሌላውን የሚያስከፋ ተናግረውም ቢሆን ችግር ሲመጣባቸው የተቀየማቸው ሳይቀር "አባታችን" ብሎ ከጎናቸው ቆሟል። ከእሳቸው በላይ መንበር ይዞ የተናገረ የለም። ከካድሬውም ከጳጳሱም በላይ ልሁን ማለት ምክንያታዊ ነውን? ጥያቄዎቼን ግን ድንገት አይተው እንዲመልሱልኝ እንደው አደራ ብዙ #ሼር አድርጉልኝ

@emsmereja
82 views18:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 20:36:59
ካህኑን ማን ገደላቸው ?

" ኃይሌ ጋርመንት " የሁርሲሳ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ቀዳሽ ካህን ቀሲስ ዐባይ መለስ " ማንነታቸው አልታወቀም " በተባሉ አካላት በተፈፀመባቸው ጥቃት ተገድለዋል።

ካህኑን የሚያውቋቸው አገልጋዮች /ምዕመናን  ስለነበረው ሁኔታ / ስለጥቃቱ ምን አሉ ?

(ለማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ከተናገሩት የተወሰደ)

ቃላቸውን የሰጡ ምዕመን አንድ ፦

" ትላንት/መጋቢት 14 ቅዳሴ ቀድሰው በአጋጣሚ እኔ በውጪ አስቀድሼ ነበር ፤ ወደ ደጀሰላም ገባን ምግብ ተመግበን ተለያይተን ነው እነሱ ወደ ኃላ ነበሩ ከምግብ በኃላ እኛ እዚህ አካባቢ ነበርን ተሻግረው ቤታቸው ቆይተው የሌላ (ቄስ አሰፋ ይባላሉ) የእሳቸው ቤት ነው የፈረሰው የእሳቸው ቤት ፈርሶ ሊሻገሩ ገና ከቤታቸው ወጥተው ትንሽ እራመድ እንዳሉ ነው ተመቱ የሚባል ወሬ ሰማን።

ተደወለና ባጃጅ አምጡ ተብለን እስከቤታቸው ድረስ እንደምንም ተቋቁመውት ሄደዋል ከቤታቸው በኃላ አንድ ካህን አብረው ይዘዋቸው መጡ ቤተክርስቲያን አካባቢ ሲደርሱ ተሸነፉ ወደቁ ፤ እኔ ለማናገር ሞከርኩኝ ምንድነው ? ምን ሆነው ነው ? ምንድነው የተፈጠረው ? ስላቸው ምንም ሊመልሱልኝ አልቻሉም ወዲያው ተናነቃቸው ባጃጅ ላይ አስገባናቸው ወደ ክሊኒክ ወሰድናቸው እዛሪ ሪፈር ተባለ ወደ ጥሩነሽ (ሆስፒታል) ወስደው ሌሊት አረፉ የሚለውን ሰማሁ በጣም አዝኛለሁ። "

ቃላቸውን የሰጡ አገልጋይ ሁለት ፦

" ዘጠኝ ሰዓት ከለሊቱ አረፉ ይሉኛል የደብሩ ዋና ፀሀፊ ፤ እንዴት ? አልኳቸው ፈረሳ ነበረና እዛ ፈረሳ እኔ መጠምጠሜን አልያዝኩም፣ ጋቢም አልያዝኩም ማንም ያወቀኝ ሰው የለም ካህንም ልሁን ምዕመንም ልሁን አሉ፤ እሳቸው ግን ጋቢያቸውን ቆባቸውን አድርገው መጥተው እዛ ነው የደበደቧቸው አሉኝ።  ቅዳሴ ውለዋል ቀድሰው እዛ ማዶ ፈረሳ አለ  ሲባል ግን የኛ የማርያም አገልጋዮችም የፈረሰባቸው ነበረና እዛ ሄጄ አብሬም ልቀላቀል ፤ ባለኝ አቅም ልርዳቸው ብለው ነው ተነስተው የሄዱት፤ እጂ ቀድሰው ውለው ነው የሄዱት። "

ቃላቸውን የሰጡ ምዕመን ሶስት ፦

" የአሟሟታቸውን ሁኔታ ሲነግሩኝ በዕለቱ በ14 ማለት ነው ፤ ቅዳሴ ቀድሰው ቅዱስ ስጋውን ክቡር ደሙን ተቀብለው አቀብለው ወጣ እንዳሉ ነው ያልታወቁ ሰዎች መንገድ ላይ አደጋ ያደረሱባቸው የሚል ነው የተሰጠኝ መረጃ።

ቤት የላቸውም ፤ ስለቤቴ ብለው የተከራከሩትም ነገር የለም መንገድ ላይ እየሄዱ ነው የሌላ ሰው ቤት ፈርሶ ወደዚያ ለማስተዛዘን ሲሄዱ ነው ጥቃት የደረሰባቸው ብለው ነው የነገሩኝ አብረዋቸው የነበሩ ሰዎች። "

ቃላቸው የሰጡ ምዕመን አራት፦

" ባጃጅ ላይ ስናስገባቸው አንድ ነገር ብቻ ነው የተናገሩት ' እባካችሁ እዚሁ ቤተክርስቲያን አድርጉኝ አትውሰዱኝ ' ሲሉ ተነፈሱ ከዚያ መናገርም አልቻሉም ፤ ውሃም ስንሰጣቸው መቀበል አልቻሉም እዛም ስንወስዳቸው መረጃ ሊነግሩን አልቻሉም "

የካህኑ ልጅ ፦

" ቤት ሲመጣ ደም ደምቶ እራሱ ላይ ነጠላ አድርጎ ነው የመጣው ከዚያ በኃላ ምን ሆነህ ነው ስለው መተውኝ ነው ያለው ሌላ ቄስ ነበሩ መጡና ሃኪምቤት ወሰዱት።

ሃዘን ናፍቆት ነው የሚሰማኝ አባ አባቴ ስለው በጣም ነው የምወደው ስለዚህ ካለሱ ማንም የሚያሳድገኝ የለም። "

ቀሲስ ዐባይ መለሰ በምዕመኑ እጅግ የሚወደዱ፣ የሚከበሩ፣ ሰርተው የሚያሰሩ ያላቸውን ሁሉም አቅም ለቤተክርስቲያኗ የሚሰጡ ትልቅ አባት እንደነበሩ ምዕመናኑ ገልጸዋል።

ካህናት በአካባቢው ላይ የተፈፀመው ድርጊት ፍርሃት ላይ እንደጣላቸው የተገለፀ ሲሆን በእሳቸው ህልፈት ከፍተኛ ሀዘን ውስጥ እንዳሉ ተጠቁሟል።

ፖሊስ ስለጉዳዩ ምን አለ ? ያንብቡ : https://telegra.ph/Police-03-24-2

@tikvahethiopia
106 views17:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 20:23:14 ደራ
#በኦሮሚያ ክልል ታጣቂዎች ሸዋ ደራ ጉንደ መስቀል ጥቃት መፈጸማቸው ተነገረ!!!
ዛሬ ለሊት ደራ  ራቾ ከፍተኛ ቁጥር  ያላቸው ታጣቂዎች የአማራዎችን ቤት እየመረጡ ሲያቃጥሉ አድረዋል።
እነዚህ ሀይሎች ቤቶችን ሲያቃጥሉ አድረው  አሁን ላይ ወደ ሮብ ገበያ መግባታቸው ታውቋል።
ታጣቂዎቹ ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ ሰዎችን አግተው  መውሰዳቸውን ገልፀዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ እስከ አሁን በመንግሥት በኩል የተደረገ መከላከል እንደሌለ ነዋሪዎች ገልፀዋል።
በመሆኑም በአካባቢው ያለው ህዝብ ከደረሰው ጥፋት የባሰ ነገር እንዳይከሰት ጥንቃቄ ማድረግ አለበት፣መንግስት ተገቢውን ትኩረት መስጠት አለበት ሲሉ ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።
#ሼርርር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
111 views17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-25 22:04:13
ዛሬ እናቴን ለመቀበል ዋሽንግተን ዲሲ አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝቼ ነበር። ድንገት አንድ ሰው በዊልቸር እየተገፋ ከመንገደኞች መግቢያ በኩል ብቅ አለ። አቶ ስብሃት ነጋ ነበሩ። ቶሎ ብዬ ካሜራዬን አወጣሁና በፎቶግራፍ ምስላቸውን ለማስቀረት ሙከራ አደረኩ። የትግራይ ተወላጆች የህወሀትን ባንዲራ ይዘው አቀባበል ሊያደርጉላቸው ከበቧቸውና ከእይታዬ ተሰውሩ። እዚያው እያለሁ ብ/ጄ ተፈራ ማሞ ትዝ አሉኝ። ትላንት ባለቤታቸውን ወ/ሮ መነን ሃይለን አግኝቼአቸው ነበር። በጠና ታመዋል። የሀኪሞች ቦርድ ውጪ ሄደው እንዲታከሙ ቢፈቅድም ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ እንዳይወጡ ተከልክለዋል። ትላንት ባለቤታቸው ሲነግሩኝ ህመማቸው እየባሰባቸው ነው። በእግራቸው የገባው ጥይት መቆምና መቀመጥ እንዳይችሉ አድርጎ እያሳመማቸው ነው። ለምን ከሀገር እንዳይወጡ እንደተከለከሉ የሚታወቅ ነገር የለም። እንግዲህ ጋሽ ስብሃትን ዋሽንግተን ዲሲ ሳያቸው አይኔ ላይ ድቅን ያሉት ጄነራሉ ናቸው።
መሳይ መኮንን

#ሼርርር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
208 views19:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-25 08:44:09 የመፅሐፉ ትረካ ላመለጣችሁ፣ ይሄንን ሊንክ በመጫን ይከታተሉ ሙሉውን አድምጡት ትወዱታላችሁ
ንኩት


222 views05:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-25 08:10:13 ቅዳሜ ማለዳ! መጋቢት 16/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ አብን የአሜሪካ መንግሥት በሰሜኑ ጦርነት ተሳታፊዎች ላይ ያሳለፈው የወንጀል ፍረጃ ሕወሃት "ወልቃይትን መልሶ በኃይል እንዲቆጣጠር ዓላማ ያለው ነው" ሲል ትናንት ባወጣው መግለጫ ተቃውሟል። የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ያወጣው ፍረጃ፣ "መሠረተ ቢስ፣ ሃላፊነት የጎደለው እና አድሏዊ" መሆኑን የጠቀሰው አብን፣ የአማራ ክልል ኃይሎች "በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን" አልፈጸሙም በማለት አስተባብሏል። የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በአማራ ክልል ኃይሎች ላይ ያሳለፈውን ፍረጃ እንደገና እንድትፈትሽና እንዲያስተካክልም አብን ጠይቋል። የአሜሪካ መንግሥት የወልቃይት አማራዎች በሕወሃት አስተዳደር ስር ለዓመታት ለደረሰባቸው በደልና ለማንነት ጥያቄያቸው እውቅና እንዲሰጥም አብን ጨምሮ ጠይቋል።

2፤ የጉሙዝ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ 300 ያህል አባላቱ ከእስር እንደተፈቱለት መናገሩን ዶይቸቨለ ዘግቧል። ሆኖም የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግሥት ክሳቸውን ካቋረጠላቸው 463 የድርጅቱ አባላት መካከል፣ 214ቱ አሁንም በእስር ላይ ይገኛሉ ሲሉ የድርጅቱ ሊቀመንበር ግራኝ ጉታ መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል። የቡድኑ አባላት ከእስር እየተለቀቁ ያሉት፣ ቡድኑ የትጥቅ ትግሉን አቁሞ በሰላማዊ መንገድ ለመንቀሳቀስ ከክልሉ መንግሥት ጋር በደረሰበት የሰላም ስምምነት መሠረት ነው።

3፤ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ቀሲስ ዐባይ መለስ የተባሉ ካህን የተገደሉት ሸገር ከተማ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው አካባቢ መጋቢት 13 በተፈጠረ ጠብ በደረሰባቸው ጉዳት እንደኾነ ትናንት ባሰራጨው መረጃ ገልጧል። ፖሊስ፣ በአንዳንድ ማኅበራዊ ትስስር ገጾች ዘንድ ክስተቱ ፖለቲካዊ ትርጉም እንዳለው ለማስመሰል የተደረገው ሙከራ ትክክል አይደለም ብሏል። የግለሰቡ አስከሬን ለምርመራ ሆስፒታል ውስጥ እንደሚገኝ የገለጠው የከተማዋ ፖሊስ፣ ክስተቱ አዲስ አበባ ውስጥ እንደተፈጸመ ተደርጎ የተሠራጨው መረጃ ስህተት መኾኑን ጨምሮ ጠቅሷል። ኾኖም ካህኑ ተገደሉ የተባሉበት ጠብ ምክንያቱ ምን እንደኾነ ፖሊስ አላብራራም።

4፤ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ የኤርትራ ወታደሮች አሁንም ትግራይ ውስጥ አሉ በማለት ትናንት ለትግራይ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃለ ምልልስ መናገራቸውን የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል። ጌታቸው የኤርትራና የአማራ ክልል ታጣቂዎች ባሉባቸው አካባቢዎች "የሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን" ፌደራል መንግሥቱ ማስቆም አለበት ብለዋል። ከአማራ ክልል ጋር ያለው ችግር በሕገ-መንግስታዊ መንገድ እንዲፈታ የጠየቁት ጌታቸው፣ በኃይል በታያዙ አካባቢዎች ያለው ጉዳይ ካልተፈታ የሰላም ስምምነቱን በማደብዘዝ ወደለየለት ቁርቁስ ለመግባት የሚያስችል ሁኔታ ሊፈጥር እንደሚችልም ገልጸዋል። #ሼርርር ይደረግ


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
224 views05:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-24 21:16:14 """"""""""ክፍል 2 ተለቀቀ""""""""""
የሳጥናኤል ጎል ኢትዮጵያ ቁጥር 1 ክፍል 2 ተለቀቀ! ሊንኩን(ፎቶውን) በመጫን ይመልከቱ


202 views18:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ