Get Mystery Box with random crypto!

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ) Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ)
የሰርጥ አድራሻ: @zemedkun_zemede
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.26K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 16

2023-03-24 21:09:21
እንዴት ብዬ እንደምገልጸው አላውቅም። ግፉ በዛ። እንዲህ ዓይነት አረመኔያዊ ተግባር ኢትዮጵያ ምድር ላይ ይፈጸማል ብሎ ውስጤ መቀበል አልቻለም። ግን ሆኗል። እዚያው አዲስ አበባ። አንድ ካህን በድንጋይ ተቀጥቅጠው ተገደሉ። እጅግ ልብ የሚሰብር ነገር ነው። ጋርመንት አከባቢ በሚገኝ ቤተክርስቲያን አጋልጋይ የሆኑት አባታችንን መንገድ ላይ ወጣቶች ጠብቀው በድንጋይ ቀጥቅጠው መግደላቸውን ከደብሩ ሰበካ ጉባዔ አጣርቼአለሁ። ሌሎች የቤተክርስቲያኒቱ አገልጋዮች በስጋት እንደሚኖሩም ሰማሁ። እዚያ ባሉ በተደራጁ ወጣቶች የሚደርስባቸውን ግፍ ቢናገሩት የሚያልቅ አይደለም። በመጨረሻም የደብሩን ዋና ካህን ለአሰቃቂ ግድያ አበቃቸው። ይህቺ ናት እንግዲህ የአብይ አህመድ ኢትዮጵያ! #ሼርርር ይደረግ


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
188 views18:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-24 20:24:30 ዓርብ ምሽት! መጋቢት 15/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ የዓለም ገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) ኢትዮጵያ ላቀረበችው የገንዘብ ድጋፍ በጎ ምላሽ ለመስጠትየቴክኒክ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን የድርጅቱ ቃል አቀባይ ጆሊ ኮዛክ ዛሬ ዋሽንግተን ውስጥ ለውጭ ዜና ምንጮች ጋዜጠኞች መናገራቸውን ቪኦኤ ዘግቧል። ድርጅቱ የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት ያስቆመው የሰላም ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ፣ በአገሪቱ መንግሥት የኢኮኖሚ ተሃድሶ ዕቅድ ዙሪያ ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር ውይይት እየተደረገ ስለመሆኑ ቃል አቀባይዋ መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል። የሰላም ስምምነቱ ከአገሪቱ መንግሥት ጋር በቅርበት እንዲሰራ መልካም ዕድሎችን እንደፈጠረለት ድርጅቱ ጨምሮ ገልጧል ተብሏል።

2፥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ በትግራይ የሚገኙ ጳጳሳት መጋቢት 13 ቀን "መንበረ ሰላማ የትግራይ ጠቅላይ ቤተክህነት" የተባለ "ሕገወጥ ክልላዊ መዋቅር" መፍጠራቸው፣ የቤተክርስቲያኗን "ተቋማዊ አንድነትና ነባር መዋቅራዊ አደረጃጀት" የሚንድ መሆኑን ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ለአሕጉረ ስብከቶች ሊቀ ጳጳስ መሾም የሚችለው የሲኖዶሱ ምልዓተ ጉባኤ መሆኑን የጠቀሰው መግለጫው፣ አዲስ የትግራይ ሊቃነ ጳጳሳት በውጭ አገራት የቤተክርስቲያኗ አሕጉረ ስብከቶች ራሳቸውን በራሳቸው መመደባቸው የቤተክርስቲያኗን "ቀኖናዊና አስተዳደራዊ አሠራር" ይጥሳል ብሏል። ቤተክርስቲያኗ የጦርነቱ ደጋፊ እንደነበረች የሚያስመስሉ መግለጫዎች ተቀባይነት እንደሌላቸው የገለጸው ሲኖዶሱ፣ በትግራይ የሚገኙ የአሕጉረ ስብከቶችን በጀት ከቆመበት ጀምሮ እንደሚልክ ገልጧል። ሲኖዶሱ፣ ሁሉንም ችግሮች ለመፍታት ለመጋቢት 21 ለጠራሁት ምልዓተ ጉባኤ በክልሉ ያሉ አባቶች ይገኙ ሲል ጥሪ አድርጓል።

3፤ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ የክልሉን "ሕገመንታዊ ግዛቶች ማስመለስ" የአስተዳደራቸው ተቀዳሚ ተግባር እንደሚሆን ዛሬ በሰጡት የመጀመሪያ መግለጫቸው መናገራቸውን የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል። ጌታቸው ምዕራብ ትግራይ፣ ደቡባዊ ትግራይ እና ጸለምት አካባቢዎች በኃይል ተይዘው እንደሚገኙና አሁንም የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እንደሚፈጸሙባቸው መግለጻቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ የክልሉን የጦርነት ተፈናቃዮች ወደቀያቸው ለመመለስ በትኩረት እንደሚሠራም ጌታቸው ተናግረዋል ተብሏል። ጌታቸው የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር የሆኑት፣ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ሕወሃት ባቀረበው ጥቆማ መሠረት የጌታቸውን ሹመት ትናንት ካጸደቁ በኋላ ነበር።

4፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ነገ ከጉራጌ ዞን ተወካዮች ጋር ወልቂጤ ከተማ ውስጥ ሊወያዩ መሆኑን ከምንጮቼ ሰምቻለሁ በማለት "ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ዘግቧል። ዐቢይ ከዞንና ከወረዳ ተወካዮች እንዲሁም ከአዲስ አበባ ከሚውጣጠ የጉራጌ ብሄር ተወካዮች ጋር የሚወያዩት፣ በጉራጌ ዞን የክልልነት አደረጃጀት ጥያቄ ዙሪያ ሳይሆን እንደማይቀር ምንጮች መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ዐቢይ ትናንት በአዲስ አበባ ከጉራጌ ባለሃብቶች ጋር በዞኑ የክልልነት አደረጃጀት ጥያቄ ላይ መወያየታታቸውና የጠቀሰው ዘገባው፣ ዐቢይ በዚሁ ስብሰባ ላይ የጉራጌ ሕዝብ ከሌሎች አጎራባች ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ጋር ባንድ ክልል ቢዋቀር እንደሚሻል መናገራቸውን አመልክቷል። ጉራጌ ዞን የራሱን ክልል ለማቋቋም ቢወስንም፣ ፌደሬሽን ምክር ቤት ግን ከደቡብ ክልል ቀሪ ዞኖች ጋር ወደፊት በሚዋቀረው "ማዕከላዊ ኢትዮጵያ" ክልል ስር እንዲዋቀር ወስኖበታል።

5፤ ኦሮሚያ እና ሱማሌ ክልሎች በተከሰተው ድርቅ ሳቢያ በርካታ ሰዎች በኮሌራ በሽታ መምታቸውን የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት መናገሩን ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል። ኮሌራ ወረርሽኙ ባለፈው ነሐሴ ከተከሰተ ወዲህ 48 ሰዎች እንደሞቱና፣ ድርቁ ወረርሽኙን እንዳባባሰው ተቋሙ መናገሩን ዘገባው ጠቅሷል። ወረርሽኙ በኦሮሚያ ክልል በ15 ወረዳዎች እንዲሁም በሱማሌ ክልል በሦስት ወረዳዎች መከሰቱን ተቋሙ መግለጡን የጠቀሰው ዘገባው፣ በኦሮሚያ ክልል ከ1 ሺህ 800 በላይ ሰዎች በበሽታው ተይዘዋል ማለቱን አውስቷል። በበሽታው ሕይወታቸው ካለፉት መካከል፣ 31 ያህሉ ከኦሮሚያ ክልል ናቸው ተብሏል።

6፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 53 ብር ከ8704 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 54 ብር ከ9478 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 63 ብር ከ2737 ሳንቲም እና መሸጫው 64 ብር ከ5392 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ58 ብር ከ5841 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ59 ብር ከ7558 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። አንድ የቻይና ዩዋን ደሞ በ7 ብር ከ1385 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ7 ብር ከ2813 ሳንቲም እንደተሸጠ ባንኩ ገልጧል። #ሼርርር ይደረግ


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
195 views17:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-24 07:32:28 የመፅሐፉ ትረካ ላላዳመጣችሁ፣ ፎቶውን በመጫን ማዳመጥ ትችላላችሁ


202 views04:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-24 07:32:28 ዓርብ ማለዳ! መጋቢት 15/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ ብሄራዊ ባንክ ለሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኩባንያ የሞባይል ገንዘብ ማስተላለፊያ አገልግሎት ፍቃድ በቅርቡ ሊሰጥ መሆኑን ሪፖርተር ዘግቧል። ይህን ትናንት ማምሻውን ያስታወቁት የባንኩ ገዥ ማሞ ምኅረቱ እንደሆኑ ዘገባው ጠቅሷል። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኩባንያ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚጀምረው የሞባይል ገንዘብ ዝውውርና ግብይት አገልግሎት፣ የኬንያው ሳፋሪኮም ኩባንያ በኬንያና ሌሎች የቀጠናው አገራት የሚጠቀምበትን "ኤምፔሳ" የተባለውን የገንዘብ መላላኪያና መገበያያ ዘዴ ነው።

2፤ ኢትዮ ቴሌኮም የ"ቴሌ ብር" የሞባይል ገንዘብ መላላኪያና መገበያያ አገልግሎት መስጫ መተግበሪያው በርካታ አገልግሎቶችን እንዲሰጥ አድርጎ በአዲስ መልክ ማበልጸጉን አስታውቋል። የተሻሻለው የ"ቴሌ ብር" መተግበሪያ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ የ23 ሌሎች አገልግሎት መስጫ ተቋማትን መተግበሪያዎች አቅፎ የያዘ እንደሆነ የአገር ውስጥ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የተሻሻለው መተግበሪያ፣ የታቀደ ክፍያ መክፈልን፣ የዕድል ጨዋታን እና ለቡድን ገንዘብ መላክን ያካትታል ተብሏል። "ቴሌ ብር" ባሁኑ ወቅት 30 ሚሊዮን ደንበኞች እንዳሉት ኩባንያው ትናንት የተሻሻለውን መተግበሪያ ይፋ ባደረገበት ስነ ሥርዓት ላይ ተናግሯል።

3፤ አብን ከኢዜማ ጋር በወቅታዊ አገራዊ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ዙሪያ የመጀመሪያ ዙር ውይይት ማድረጉን ትናንት ማምሻውን በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል። ሁለቱ ፓርቲዎች ወደፊትም በሚግባቡባቸው አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለመወያየትና የጋራ አቋሞችን ለመያዝ መስማማታቸውን አብን ጨምሮ ገልጧል። ሁለቱ ፓርቲዎች እዚህ ስምምነት ላይ መድረሳቸው የተገለጠው፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕወሃትን ከአሸባሪነት መዝገብ መሰረዙ ትልቅ ስህተት መሆኑን ጠቅሰው ተቃውሟቸውን ባሰሙ ማግስት ነው።

4፤ የኤርትራው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ኦስማን ሳለህ እና የፕሬዝዳንት ኢሳያስ የፖለቲካ አማካሪ የማነ ገ/አብ ወደ ሩሲያ አቅንተው ከአገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ጋር መወያየታቸውን የኤርትራ ቃል አቀባይ የማነ ገ/መስቀል በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል። ኦስማን እና ላቭሮቭ ሶቺ ከተማ ውስጥ፣ በሁለትዮሽና የዩክሬኑን ጦርነት ጨምሮ በዓለማቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ እንደተወያዩ ከውይይታቸው በኋላ በሰጡት መግለጫ መግለጣቸውን የማነ ገልጸዋል። ላቭሮቭ ከጥቂት ሳምንታት በፊት በኤርትራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወሳል። #ሼርርር ይደረግ


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
210 views04:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-23 21:17:09 ተለቀቀ!
የሳጥናኤል ጎል ኢትዮጵያ ትረካ- ክፍል 1- ቁጥር 1 ሙሉ ክፍል ተለቀቀ!! ሊንኩን በመንካት ትረካውን ያድምጡ


221 views18:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-23 20:05:14 ሐሙስ ምሽት! መጋቢት 14/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ ኢትዮጵያ የተመድ ሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ለሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ያቋቋመው የሰብዓዊ መብት ጥሰት መርማሪ ኮሚሽን እንዲበተን የጀመረችውን ጥረት ማቋረጧን ሮይተርስ ዲፕሎማቶችንና የሰብዓዊ መብት ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል። የኢትዮጵያ መንግሥት ይህንኑ ጥረቱን ያቋረጠው፣ የመርማሪ ኮሚሽኑ የጊዜ ቆይታ ከመስከረም በኋላ እንደማይራዘም ከምዕራባዊያን አገራት ጋር መግባባት ላይ በመድረሱ እንደሆነ ዘገባው ጠቅሷል። ምዕራባዊያን መንግሥታት ኢትዮጵያ የኮሚሽኑ ተልዕኮ እንዲያበቃ አሁን ጉባኤ ለተቀመጠው የተመድ ሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ረቂቅ የውሳኔ ሃሳብ ብታቀርብ "ድጋፍ ልታገኝ ትችላለች" በሚል ስጋት፣ ከመስከረም በኋላ የኮሚሽኑ ቆይታ እንደማይራዘም መግባባት ላይ መድረስን መርጠዋል ተብሏል። አገራት ለጉባዔው ረቂቅ የውሳኔ ሃሳብ የሚያቀርቡበት ቀነ ገደብ ዛሬ ያበቃ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ያቀረበችው ረቂቅ የውሳኔ ሃሳብ እንደሌለ ታውቋል።

2፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ከትግራይ በቀረበላቸው ጥቆማ መሠረት ጌታቸው ረዳ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አንዲሆኑ ማጽደቃቸውን ጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤት አስታውቋል። ጌታቸው የክልሉን ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲመሩ ሕወሃት ለጊዜያዊ አስተዳደሩ መስራች ኮሚቴ መርጦ ማቅረቡ ይታወሳል። ዐቢይ ጥቆማውን ተቀብለው ያጸደቁት፣ የሚንስትሮች ምክር ቤት ቀደም ሲል ባጸደቀው የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አስተዳደር መሠረት ነው። የክልሉ ጊዜያዊ ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው፣ የክልሉን የፖለቲካ ኃይሎች ውክልና በሚያረጋግጥ ሁኔታ ጊዜያዊ አስተዳደሩን ዩማዋቀር ሃላፊነት እንዳለባቸው ጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤት ገልጧል።

2፤ አብን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕወሃትን ከአሸባሪነት ፍረጃ መሰረዙ "ተገማች በሆነ ጊዜ ውስጥ ለሌላ ዙር ግጭትና ጦርነት" አገሪቱን ያጋልጣታል ሲል ዛሬ ባወጣው መግለጫ ውሳኔውን ተቃውሟል። አብን፣ በዚህ ውሳኔ ሳቢያ ለሚመጣው ጥፋት መንግሥት ተጠያቂ ይሆናል በማለት አስጠንቅቋል። ሕወሃት የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ተግባራዊ አላደረገም ያለው አብን፣ የጦርነት ቀጠና ሆነው የቆዩትን አካባቢዎች፡ለአራተኛ ዙር "የጦርነት አደጋ የሚያጋልጡ ሁኔታዎች" እየተፈጠሩ መሆኑን ገልጧል። አብን፣ ውሳኔው በጸደቀበት ስብሰባ በርካታ የምክር ቤት አባላት አለመገኘታቸውና 60 አባላት ውሳኔውን መቃወማቸው፣ ውሳኔውን ቅቡልነት ያሳጣዋል ብሏል። ሕወሃት "የአዲስ ታጣቂ ምልመላ፣ ሥልጠና እና የጦርነት ዝግጅት" እያደረገ ይገኛል በማለትም አብን ከሷል።

3፤ አፍሪካ ኅብረት በሱማሊያ ላሠማራው የሰላም አስከባሪ ኃይል 90 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ጠይቋል። ኅብረቱ ለሰላም ማስከበር ተልዕኮው የጠየቀው የገንዘብ ድጋፍ ካልተገኘ፣ ተልዕኮው ለሱማሊያ መንግሥት እና ጦር ሠራዊት ወታደራዊ ድጋፍ እየሰጠ ለመቀጠል እብደሚቸገር ኅብረቱ ተናግሯል። ይህንኑ የኅብረቱን የገንዘብ ድጋፍ ጥያቄ የተናገሩት፣ የኅብረቱ የፖለቲካ፣ ሰላምና ጸጥታ ኮሚሽን ኮሚሽነር ባንኮሌ ናቸው። ዛሬ ኒውዮርክ ላይ ተልዕኮው በሚያስፈልገው የገንዘብ ድጋፍ ዙሪያ አፍሪካ ኅብረት እና ተመድ የጋራ ውይይት አድርገዋል። አፍሪካ ኅብረት ባሁኑ ወቅት በሱማሊያ የኢትዮጵያ ወታደሮችን ጨምሮ ከ19 ሺህ 600 በላይ ሰላም አስከባሪዎች አሉት።

4፤ የኬንያው አንጋፋው የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ራይላ ኦዲንጋ ለቀጣዩ ሰኞ "የተቃውሞ ሰልፎች ሁሉ ቁንጮ" ያሉትን የተቃውሞ ሰልፍ ጠርተዋል። ኦዲንጋ፣ የተቃውሞ ሰልፉ ሰላማዊ እንዲሆን ጥሪ አድርገዋል። ኦዲንጋ ባለፈው ሰኞ የጠሩት አገር ዓቀፍ ሰልፍ የተካሄደ ሲሆን፣ በዋና ከተማዋ ናይሮቢ ከፖሊስ በተተኮሰ ጥይት አንድ ሰልፈኛ ተገድሏል። የሰኞውን የተቃውሞ ሰልፍ ተከትሎ፣ ኦዲንጋ በሳምንት ሁለት ጊዜ ማለትም ሰኞ እና ሐሙስ የተቃውሞ ሰልፎች እንዲደረጉ ጥሪ አድርገዋል። ኦዲንጋ አገር ዓቀፍ የተቃውሞ ሰልፍ የጠሩት፣ የፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ መንግሥት የአገሪቱን የኑሮ ውድነት አልቀረፈም በማለት እንዲሁም እሳቸው የተሸነፉበት ያለፈው የነሐሴው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ተጭበርብራል በሚል ምክንያት ነው።

5፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 53 ብር ከ8607 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 54 ብር ከ9379 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 63 ብር ከ1749 ሳንቲም እና መሸጫው 64 ብር ከ4384 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ58 ብር ከ1049 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ59 ብር ከ2670 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼርርር ይደረግ


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
239 views17:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-23 07:21:17 ሐሙስ ማለዳ! መጋቢት 14/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ የሕወሃት ሊቀመንበር ደብረጺዮን ገ/ሚካዔል የፌደራሉ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕወሃትን ከአሸባሪነት ፍረጃ ማንሳቱ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርን ለማዋቀር ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል በማለት መናገራቸውን የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል። ደብረጺዮን፣ በትግራይ ክልል በጀት ዝግጅት እና በእስረኞች ዙሪያ ከፌደራሉ መንግሥት ጋር ግንኙነት እንደተጀመረ እና አዲስ የሚዋቀረው የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር እደረጃጀት ለፌደራሉ መንግሥቱ እንደተላከ መግለጻቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ደብረጺዮን ይህን የተናገሩት፣ ትናንት በመቀሌ ለክልሉ ጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ላይ ነው።

2፤ የሕወሃት ከፍተኛ አመራር ጌታቸው ረዳ የትግራይ የጦር ጉዳተኞች ሰሞኑን ያነሷቸው ቅሬታዎች በከፍተኛ ትኩረት እንደሚታዩ እና ማጣራት እንደሚደረግባቸው መናገራቸውን አዲስ ስታንዳርድ ዘግቧል። የጦር ጉዳተኞቹ ለእነሱ ተብሎ የተገዛ የሕክምና አቅርቦት እየተሸጠ ስለመሆኑ ነግረውኛል ያለው ዜና ምንጩ፣፣ የጦር ጉዳተኞቹ የጉዳት ካሳ እንዲከፈላቸው መጠየቃቸውንም ጠቅሷል። የጦር ጉዳተኞቹ ከፍተኛ የሆነ የምግብ፣ የሕክምናና የንጽሕና መጠበቂያ አቅርቦት እጥረት እንዳለባቸው በሰላማዊ ሰልፍና ከጌታቸው ጋር ባደረጉት ውይይት መናገራቸው ተዘግቦ ነበር። የጦር ጉዳተኞቹ፣ በመቀሌ አካባቢ ኩዊሃ እና ደጀን ሆስፒታል በተባሉ ሁለት ማገገሚያ ማዕከሎች የሚገኙ ናቸው።

3፤ በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኢምባሲ ጉዳይ አስፈጻሚ አምባሳደር ትሬሲ ጃኮብሰን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት የጦር ወንጀሎች እና በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ተፈጽመዋል በማለት መፈረጁ በአሜሪካና ኢትዮጵያ ግንኙነት ላይ "አንዳችም ሕጋዊ አንድምታ የለውም" በማለት ማረጋገጫ መስጠታቸውን ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በትዊተር ገጹ ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል። አምባሳደር ጃኮብሰን ይህን ማረጋገጫ የሰጡት፣ ትናንት ከውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ሚንስትር ደዔታ ምስጋኑ አረጋ ጋር በተወያዩበት ወቅት እንደሆነ ሚንስቴሩ ገልጧል። ምስጋኑ የአሜሪካ ፍረጃ ተገቢ እንዳልሆነ ለጃኮብሰን ገልጸውላቸዋል ተብሏል።

4፤ የተመድ ስደተኞች ኮሚሽን እና ሌሎች ዓለማቀፍ የረድዔት ድርጅቶች ከሱማሊያ ተሰደው ወደ ኢትዮጵያ ለገቡ ስደተኞች ሰብዓዊ ዕርዳታ ለማቅረብ 116 ሚሊየን ዶላር እንደሚያስፈልግ አስታውቀዋል። ድርጅቶቹ የሰብዓዊ ዕርዳታ ልገሳ ጥሪውን ያቀረቡት፣ በሱማሌላንድ መንግሥት ወታደሮች እና በጎሳ ታጣቂዎች መካከል ከሚካሄደው ግጭት ሸሽየው ወደ ኢትዮጵያው ሱማሌ ክልል ለገቡ ሕጻናትና ሴቶች ለበዙባቸው ስደተኞች ነው። ከግጭቱ የሸሹ ከ100 ሺህ በላይ ስደተኞች ወደ ሱማሌ ክልል ዶሎ ዞን መግባታቸውን የተመድ መረጃዎች ያመለክታሉ። #ሼርርር ይደረግ


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
258 views04:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-21 20:56:27 ጥሩ ሀገርማ አለን። የተባረከ አባት አጣን እንጂ። ጠ/ሚሩ ከሀገርና ህዝብ ጋር እልህ ተጋብተዋል። በሚጽፏቸው የማህበራዊ ሚዲያ መልዕክቶች ስር ተደራጅተው በሚያንቆለጳጵሷቸው ካድሬዎችና የእንብላው፥ እንጋጠው ማህበር አባላት ጭብጨባ የኢትዮጵያን ህዝብ እየለኩት፡ እየመዘኑት እንደማይሆን ተስፋ አደርጋለሁ። የዚህን ያህል የግንዛቤ ችግር ካለባቸው እጅግ አስቸጋሪ ነው። ካፈርኩ አይመልሰኝ ደማቸው ውስጥ የሚንተከተክ መለያ ባህሪያቸው እንደሆነ ይገባኛል። እውነት አጠገባቸው እንደሌለች ከማንም በላይ ራሳቸው እንደሚያውቁት በተለያዩ አጋጣሚዎች በነበረኝ የቅርብ ትውውቅ ተረድቼአለሁ። ያኔ በቅዠት ውስጥ የሳሏት ሀገር፡ በምናባቸው የገነቧት ምድር ትመጣ ዘንድ ሁሌም እንደሚናፍቁ ከሁኔታቸው መረዳት ይቻላል። እሳቸውንና ተከታዮቻቸውን እዚያ የምናብ ዓለም ውስጥ ይዘው ነጉደዋል። እሳቸው ሌላ ዓለም ነው ያሉት። አብረውን እየኖሩ አይደለም። ዳመና ውስጥ ጎጆአቸውን ቀልሰው ኑሮ ከጀመሩ አመታት ተቆጥረዋል። ከእውነት ጋር ከተላተሙ ሰነባብተዋል። መሬት ካለው ሀቅ ጋር ሆድና ጀርባ ከሆኑ አያሌ ንጋትና ምሽት አልፈዋል። ከፊት ያለው ገደል ለጥ ያለ ሜዳ ሆኖ የሚታያቸው ለምን እንደሆነ አይባኝም። የሚሾፍሩት ባቡር ሀዲዱን ስቶ ወደ ጥልቁ ባህር እያንደረደረን መሆኑን እያወቁት ነዳጁን ለምን እንደሚጨምሩት ምክንያቱ ሊገለጥልኝ አልቻለም።

የሀገር ውስጥ በረራ ተጨናንቋል የሚል መረጃ ሰማሁና ለማጣራት ሞከርኩ።በየብስ የሚደረግ የመንገድ ላይ ጉዞ ከነፍስ ጋር ተወራርዶ ካልሆነ በቀር የማይታሰብ ነው የሚል ምላሽ አገኘሁ። ከአዲስ አበባ ወደ አዋሽ መስመር መጓዝ ከሞት ጋር ቁማር የመጫወት ያህል ሆኗል። በህወሀት ዘመን የነበረው የመንቀሳቀስ 'ነጻነት' አሁን በህልም እንጂ በእውን የሚገኝ አልሆነም። አዲስ አበባ በቅርብ የማውቃቸው ቤተሰብ እናትና አባት ምግብ ሳይበሉ እንደሚያድሩ፡ ያለችዋን ልጆቻቸው እንዲቃመሱ አድርገው እነሱ ባዶ ሆዳቸውን ወደ መኝታቸው እንደሚሄዱ ሰማሁኝ። ጥልቅ ድህነት ሰማይ ምድሩን ወርሶታል። የከተማ ረሃብ ቤተመንግስት ደጃፍ ደርሷል። ኑሮ የሰማይ እንቅብ ሆኖ ህዝቡ ላይ ተደፍቷል። ረሃብ ጥሙን ልቻል ብሎ የተቀመጠን ደግሞ ባለጊዜው፡ ተረኛው በቆመጥ እየነረተ፡ በሰደፍ እየቀጠቀጠ እንዳሻው የሚፈነጭባት ሀገር ሆናለች። የኢትዮጵያ ነገር ይጨንቃል። የምሰማው ሁሉ ጆሮን ጭው የሚያደርግ ነው። እንደዚህ ዘመን ከብዶ አያውቅም። ሰው መሄጃ አጥቷል። መላወሻ የለውም። በገዛ ሀገሩ ግዞተኛ፡ እስረኛ ሆኗል።

እሳቸው ይመጡና ''ብልጽግና'' ገለመሌ ይሉና ባልበላ አንጀት ህዝቡን ያሳምሙታል። የመደመር ትውልድ እያሉ በረሃብ የዛለ ሰውነቱን በሀሰተኛ ዲስኩር ጨምረው ያደክሙታል። በምናባቸው የሳሏትን ምድር ትወርሳላችሁና ተከተሉኝ እያሉ ይጫወቱበታል። ዘረኝነትን እየጋቱት ዘረኝነትን እንዋጋ የሚል ቅንነት የጎደለው እጅግ ነውረኛ መልዕክት በጆሮው ያንቆረቁሩለታል። አንጀቴ ደረቀ፡ ሆዴ ተላወሰ፡ እርቦኛል ለሚለው የመላ ህዝባቸው ጥያቄ መዝናኛ ሎጅ ቢሊየን ዶላሮችን አውጥተው ይገነቡለታል። ጠኔ ይዞት ዳቦ ለለመነ ህዝብ ኬክ ለምን አትሰጡትም እንዳለችው የአውሮፓዊቷ ንግስት እሳቸውም ሀገር በቁሟ ተርባ የህንዱን ታጅማሃል ህንጻ የመሰለ ግዙፍ ሎጅ በሰቃ ሀይቅ ላይ በመገንባቱ ስራ ተጠምደው ሰንብተዋል። የሃላላ ሎጅን በማስዋቡ ተግባር ላይ እንቅልፋቸውን አጥተዋል። እውነት ግፍም ልክ አለው። ህዝብን በዚህ ደረጃ መናቅ ውጤቱ አያምርም። የቅርብም ሆነ የሩቅ ታሪኮች የሚነግሩን እውነት በሰፈሩት ቁና መሰፈር የማይቀር ምድራዊ ሀቅ መሆኑን ነው።

ፈጣሪ ልቦና ይስጣቸው። አምላክ የእሳቸውን እብሪትና ትዕቢት ሳይሆን ልበ ሩህሩህ የሆነውን ህዝብ ይመልከትና ከመጣብን መከራ ይገላግለን። ከባድ ነው።መልዕክቴን #share አድርጉልኝ


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
118 views17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-21 07:22:09 ማክሰኞ ማለዳ መጋቢት 12/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት፣ የአማራ ክልል ታጣቂዎች እና የኤርትራ ሠራዊት በትግራይ ክልል ግድያ፣ አስገድዶ መድፈር፣ ጾታዊ ጥቃትን ጨምሮ "በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን" ፈጽመዋል በማለት ፈርጀዋል። በተለይ የአማራ ክልል ኃይሎች፣ በምዕራብ ትግራይ "ሰዎችን በግዳጅ የማፈናቀል" እና "የብሄር ማጽዳት ወንጀሎችን" መፈጸማቸውን ብሊንከን ጨምረው ገልጸዋል። ብሊንከን፣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት፣ የአማራ ክልል ታጣቂዎች፣ የትግራይ ኃይሎችና የኤርትራ ሠራዊት ደሞ፣ "የጦር ወንጀሎችን" ፈጽመዋል ብለዋል። ፍረጃው፣ በአሜሪካ ፖሊሲ ላይ ወዲያውኑ የሚያስከትለው ለውጥ አይኖርም ተብሏል። ብሊንከን፣ ወንጀሎቹን የፈጸሙ አካላት በሕግ መጠየቅ አለባቸው ብለዋል። ብሊንከን ይህን የተናገሩት፣ ዓመታዊውን የዓለም ሰብዓዊ መብቶች ሪፖርት ይፋ ባደረጉበት ወቅት ነው።

2፤ የኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን አካባቢ አባ ገዳዎችና የአገር ሽማግሌዎች መዳ ወላቡ ወረዳ አዲስ በተዋቀረው ምሥራቅ ቦረና ዞን ሥር መካለሉን ተቃውሞው ቅሬታ ማሰማታቸውን ቪኦኤ ዘግቧል። አባ ገዳዎቹና የአገር ሽማግሌዎቹ ቅሬታቸውን ለፌደራሉና ለክልሉ መንግሥት ማቅረባቸውን መስማቱን ዘገባው ጠቅሷል። የጉጂ ዞን አባ ገዳዎችም፣ የዞኑ ዋና ከተማ ነገሌ ቦረና ለአዲሱ ምሥራቅ ቦረና ዞን መካለሏን በመቃወም ተመሳሳይ ቅሬታ አቅርበው፣ የክልሉ መንግሥት አደረጃጀቱን እንደማይቀይር መግለጡ ይታወሳል። አዲሱ ምሥራቅ ቦረና ዞን፣ ከቦረና፣ ጉጂ እና ባሌ ዞኖች አንዳንድ አካባቢዎችን በማካተት በቅርቡ የተዋቀረ ዞን ነው።

3፤ በኬንያ 43 የፌስቡክ የመልዕክት ይዘት ተቆጣጣሪዎች ያላግባብ ከሥራ ተሰናብተናል በማለት ክስ መመስረታቸውን የኬንያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ግለሰቦቹ ክሱን የመሠርቱት፣ በፌስቡክ እናት ኩባንያ ሜታ እና ሜታ ለይዘት ተቆጣጣሪነት ኮንትራት በስጣቸው "ሳማ" እና "ማጆሬል" በተባሉ ሁለት ኩባንያዎች ላይ እንደሆነ ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። የከሳሾቹ አንደኛው ክስ፣ "ሳማ" ኩባንያ ሠራተኛ ማኅበር በማቋቋማችን ከሥራ አባሮናል የሚል ነው ተብሏል። ሌላኛው ክስ ደሞ፣ ከ"ሳማ" በኋላ ኮንትራት የወሰደው "ማጆሬል" ኩባንያ ለተመሳሳይ የሥራ ቦታ እንዳንወዳደር በሜታ ኩባንያ ትዕዛዝ ስማችን በጥቁር መዝገብ አስፍሮ ከውድድር ከልክሎናል የሚል መሆኑን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።

4፤ በሱማሊያ በተከሰተው ድርቅ እስካለፈው ጥር ወር ድረስ በነበረው አንድ ዓመት 43 ሺህ ያህል ሰዎች ሞተዋል ተብሎ በጥናት እንደተገመተ ዓለማቀፍ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። በጥናቱ ግምት መሠረት፣ ከሟቾቹ መካከል ግማሾቹ ከአምስት ዓመት በታች የሆኑ ሕጳናት እንደሆኑ ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። የሟቾችን አሃዝ ሪፖርት ያወጡት፣ የዓለም ምግብ ድርጅት እና የዓለም ሕጻናት ድርጅት ናቸው። ባሁኑ ወቅት በአገሪቱ የቀጠለው ድርቅ ምን ያህል ሰው እንደገደለ ኦፊሴላዊ አሃዝ ሲወጣ የአሀኑ የመጀመሪያው ነው። የተመድ የአየር ትንበያ ተቋም፣ ድርቁ ለስድስተኛ የዝናብ ወቅት ይቀጥላል የሚል ስጋቱን በቅርቡ መግለጡ ይታወሳል።#ሼር ይደረግ

ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
193 views04:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-20 22:16:36
የዶ/ር አብይ መንግሥት ዜጎችን በድብደባና በግድያ አሰፈራርቼ እገዛለሁ ካለ: ከታሪክ አለመማሩን ያሳያል:: ዶ/ር አብይ በዚህ ጉዳይ ላይ የጻፈውንና የተናገረውን መለስ ብሎ አይቶ እርሱ በሚመራው ስርዓትም እየተደገመ መሆኑን ቢያይ: በራሱ የሚያፍር ይመስለኛል:: ግን ህዝብ ፍርሃትን የሚፈራው ለተወሰነ ጊዜ ነው:: እንዲያውም ከህዝብ በፊት ቀድመው የሚፈሩት ዜጎች ሳይሆኑ ራሳቸው የመንግሥት ባለስልጣናት ናቸው:: እነሱ ሲፈሩ ደግሞ የውስጥ ተቃውሞዋቸውን በተለያዩ መንገዶች ማካሄድ ይጀምራሉ:: ይህ ከውጭ ካለው የህዝብ ተቃውሞ ጋር ሲቀናጅ: ህዝባዊ አመጽ ይነሳል::

የአብይ መንግሥት በዚህ የአፈና ባህሪው ከቀጠለ: ቀኑን መናገር ባይቻልም: በተቃውሞ መናጡ አይቀርም:: የአሁኑን የከፋ የሚያደርገው ግን ለስልጣኑ ሲል የብሄርን አጀንዳ ለመጠቀም ወደሁዋላ የማይል መንግሥት መሆኑ ነው:: የሚያስፈራውም ይህ ነው::

መንግሥታዊ ጥጋብና ፍርሃት አገራችንን ወደ መቀመቅ ይዟት እንዳይሄድ: ለመሪዎቹ ልቦና ይስጣችው::#share ይደረግ

ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
199 views19:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ