Get Mystery Box with random crypto!

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ) Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ)
የሰርጥ አድራሻ: @zemedkun_zemede
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.26K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 17

2023-03-20 20:33:28
ሀገሬ ኢትዮጵያ ለከፈልሽኝ ውለታ አመሰግናለው
ታዬ ቦጋለ
የዶ/ር አብይ አህመድ መንግስት የትርክትና የህዝብ ግንኙነት የበላይነቱን እየተነጠቀ መምጣቱን የምናረጋግጠው በጋዜጠኞች ላይ የሚወስደውን የአፈና እርምጃ ስናይ ነው። ትናንት በየኛ ቲዩብ ጋዜጠኛው ንጉሴ ብርሃኑ ላይ የተፈጸመው ድብደባ አልበቃ ብሎ ዛሬ ደግሞ የ ኢትዮ 251 ሚዲያ ንብረት መዘረፉን ስንሰማ፣ አገዛዙ ከሃሳብ ትግል ወደ አፈና ትግል እየገባ እንደሆነ እናያለን። "መግደል መሸነፍ ነው" ሲል የነበረው መንግስት፣ ወደዚሁ የሽንፈት መንገድ በፍጥነት እየተንደረደረ እየገባ ይመስላልና ፍሬን ከመበጠሱ በፊት በጊዜ ታኮ ድንጋይ ቢያስቀምጡለት ጥሩ ይመስለኛል። #ሼር_ፖስት

ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
217 views17:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-20 15:54:24
ኢትዮጵያ በዓለም ደስታ ከራቃቸዉ አገራት ዝርዝር ዉስጥ በ14ኛ ደረጃ ተቀመጠች

የአለም የደስታ ሪፖርት ደረጃን ይፋ ያደረገው ፎርብስ በሰበሰበዉ ድምጽ መሰረት ኢትዮጵያ በዓለም ደስታ ከራቃቸዉ አገራት ዝርዝር ዉስጥ በ14ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡

በዝርዝሩ ለስድስት ተከታታይ ዓመታት ፊንላንድ በአለም ደስተኛ አገር ሆና የተመረጠች ሲሆን፤ የኖርዲክ አገራት የሆኑት የፊላንድ ጎረቤቶች ዴንማርክ፣ አይስላንድ፣ ስዊድን እና ኖርዌይ በሪፖርቱ ግኝት ጥሩ ውጤት አስመዝግበዋል፡፡

ደስተኛ አገራት ተብለዉ ከ1ኛ እስከ 5ኛ ደረጃ የያዙት ፊላንድ፣ ዴንማርክ፣ አይስላንድ፣ እስራኤልና ኔዘርላንድ ሲሆኑ፤ ስዊዲን፣ ኖርዌይ፣ ስዊዘርላንድ፣ ሉክዘንበርግና ኒዉዝላንድ እስከ አስረኛ ያለዉን ደረጃ ይዘዋል፡፡ እንዲሁም አሜሪካና ጀርመን በ15ኛ እና በ16ኛ እንዲሁም እንግሊዝ በ19ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡

ሪፖርቱ በአለም ደስተኛ ከሆኑ አገራት በተጨማሪ ሰዎች ደስተኛ ያልሆኑባቸውን አገራቶችንም ተመልክቷል።

በዝርዝሩ ደስታ ርቋቸዋል ከተባሉ 20 የዓለም አገራት ዉስጥ 15ቱ ከአፍሪካ ሲሆኑ፤ በጦርነት ምክንያት የተመሰቃቀሉ ናቸው። በዚህም መሰረት ከ20 የዓለም አገራቱ ውስጥ አፍጋኒስታን በ1ኛ ደረጃ ስትቀመጥ፣ ሊባኖስ ፣ ሴራሊዮን፣ ዚምባብዌና ኮንጎ እስከ 5ኛ ደረጃ ይዘዋል፡፡

ኢትዮጵያ በዓለም ደስታ ከራቃቸው ዝርዝር ዉስጥ በ14ኛ ደረጃ የያዘች ሲሆን፤ በዚሁ ዝርዝር ውስጥ ላይቤሪያ በ13ኛ እንዲሁም ግብጽ በ17ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡

ለሪፖርቱ መነሻ ከሆኑ የመመዘኛ ነጥቦች መካከል ጤናማ የሕይወት ዘመን፣ የአገር ውስጥ ምርት እድገት በነፍስ ወከፍ ደረጃ፣ ማኀበራዊ ድጋፍ፣ ዝቅተኛ ሙስና፣ በማኀበረሰብ ውስጥ ያለ ልግስና እና ቁልፍ የሕይወት ውሳኔዎችን የማድረግ ነፃነት ይገኙበታል፡፡ሼር ይደረግ
@emsmereja
246 views12:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-18 22:19:18
ብዙ የሃገር መሪዎች መጽሃፍ የሚጽፉት ስልጣን ከያዙ ወይም ከለቀቁ በኋላ ነው። ምክንያታቸውም በስልጣን ዘመናችን መጽሃፍ ለመጻፍ ጊዜ የለንም የሚል ነው። አጼ ሃይለስላሴ ብዙ ጊዜ በስልጣን ላይ ስለነበሩ አንድ መጽሃፍ የመጻፊያ ጊዜ አግኝተዋል። መንግስቱ ሃይለማርያም ስልጣን ከለቀቀ በኋላ ነው የጻፈው። መለስ በይፋ የሚታወቅ መጽሃፍ ሳይጽፍ ነው የሞተው። ኢሳያስ አፈወርቂ እስካሁን አልጻፈም።

መሪዎች ለመጻፍ አይደለም ለማንበብ እንኳን ጊዜ እንደሌላቸው ነው የሚናገሩት። ታዲያ ዶ/ር አብይ በ 5 ዓመት ውስጥ በየትኛው ጊዜው አንብቦና አሰላስሎ ነው 3 መጽሃፎችን ለመጻፍ የቻለው? የመንግስቱን ስራ እርግፍ አድርጎ ስለተወው ነው እንዳንል ከሰኞ እስከ እሁድ ስራ ላይ ወይም ጉዞ ላይ እንደሆነ ነው የምናየው። መጽሃፍ መጻፉ እስካሁን ካወቅነው በላይ የበለጠ እንድናውቀው የሚያደርገን ጥሩ ስራ ቢሆንም፣ እስካሁን ያሳወቀንን ብቻ ወደ መሬት አውርዶ ቢያሳየን፣ ይህ ሁሉ ምስቅልቅል በአገራችን ላይ ባልተፈጠረ ነበር ብዬ አስባለሁ። ያው ሁሉንም ማንበብ ስለማልጠላ መጽሃፉን የሚልክልኝ ሰው ባገኝ፣ እኔ ደግሞ አንድ አሪፍ መጽሃፍ ግዝቼ እልክለታለሁ።#share Godhii

    ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
244 views19:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-18 20:08:40 የቅዳሜ ምሽት መጋቢት 9/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ የሕወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ የፓርቲውን ቃል አቀባይና የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ጌታቸው ረዳ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት እንዲሆኑ ትናንት በአብላጫ ድምጽ መምረጡን የትግራይ ክልል ቴሌቪዥን ዛሬ ዘግቧል። የክልሉን ጊዜያዊ አስተዳደር የሚያዋቅረው፣ ለዚሁ ዓላማ የተቋቋመውና ጀኔራል ታደሠ ወረደ የሚመሩት ክልል ዓቀፍ ኮሚቴ ነው። ኮሚቴው፣ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ ሁሉን አካታች እንደሚሆን ሲገልጽ የቆየ ሲሆን፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩን ፕሬዝዳንት የሚያቀርበው ግን ሕወሃት እንዲሆን እንደተወሰነ ቀደም ሲል ተገልጧል።

2፤ አዲሱ ጎጎት የጉራጌ አንድነትና ፍትህ ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ዛሬ በአዲስ አበባ ባደረገው ስብሰባ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላቱን፣ ሊቀመንበሩንና ምክትል ሊቀመንበሩን መምረጡን በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል። የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ 11 የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን የመረጠ ሲሆን፣ መሐመድ አብራርን የፓርቲው ሊቀመንበር እንዲሁም እስር ላይ የሚገኙትን እንዳለ ንዳን ደሞ ምክትል ሊቀመንበር አድርጎ መምረጡን ገልጧል። ፓርቲው ከሳምንት በፊት ባካሄደው መስራች ጉባኤ፣ 29 ቋሚ አባላት ያሉት ማዕከላዊ ኮሚቴ አቋቁሟል። ፓርቲው፣ ጉራጌ ዞን ራሱን የቻለ ክልል እንዲሆን እንደሚታገል ቀደም ሲል መግለጡ ይታወሳል።

3፤ በሰሜኑ ጦርነት ሳቢያ ከሁለት ዓመት በላይ የተዘጉ የትግራይ ክልል ትምህርት ቤቶችን እንደገና ለማስከፈት ዕቅድ መውጣቱን የተመድ ሕጻናት ድርጅት- ዩኒሴፍ ለቢቢሲ ሬዲዮ ተናግሯል። ድርጅቱ፣ ከክልሉ አስተዳደር ጋር የተያዘው ዕቅድ ትምህርት ቤቶችን በመጭው ሚያዝያ ወር ለመክፈት መሆኑን ገልጧል። በክልሉ በጦርነቱ ሳቢያ 2.3 ሚሊዮን ሕጻናት ከትምህርት ገበታ ውጭ ሆነው እንደሚገኙ ድርጅቱ ጨምሮ ጠቅሷል።

4፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ "የመደመር ትውልድ" የተሰኘውን አዲሱን መጽሃፋቸውን ዛሬ በታላቁ ቤተ መንግሥት በተካሄደ ስነ ሥርዓት ማስመረቃቸውን የመንግሥት ዜና አውታሮች ዘግበዋል። መጽሃፉ በአማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች እንደተዘጋጀና፣ ክልሎች ከመጽሃፉ ሽያጭ የሚያገኙትን ገቢ ለትውልድ ግንባታና ታሪካዊ ቦታዎችን ለማደስ ያውሉታል መባሉን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። በመጽሃፉ ምረቃ ስነ ሥርዓት ላይ፣ ዐቢይ፣ የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የክልሎች ርዕሰ መስተዳድሮች፣ የገዥው ብልጽግና ፓርቲ አመራሮችና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል ተብሏል።

5፤ የደቡብ አፍሪካ መንግሥት የአገሪቱን ጦር ሠራዊት ቁልፍ መሠረተ ልማቶችን እንዲጠብቅ በዋና ዋና ከተሞች ሊያሠማራ መሆኑን የአገሪቱ ዜና አውታሮች ዘግበዋል። መንግሥት ሠራዊቱን በከተሞች የሚያሠማራው፣ ተቃዋሚው "የኢኮኖሚ ነጻነት ተፋላሚዎች" ፓርቲ የመንግሥትና የግል ተቋማትን የሚያዘጋ አገር ዓቀፍ የተቃውሞ ሰልፍ በቀጣዩ ሳምንት መጥራቱን ተከትሎ ነው። ፓርቲው የተቃውሞ ሰልፉን የጠራው፣ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎዛ የአገሪቱን ኢኮኖሚ ለውድቀት ዳርገውታል በማለት ፕሬዝዳንቱ ሥልጣን እንዲለቁ ግፊት ለማድረግ ነው። ወጣቱ ጁሌስ ማሌማ የሚመራው የኢኮኖሚ ነጻነት ተፋላሚዎች ፓርቲ፣ በአገሪቱ ፓርላማ በመቀመጫ ብዛት ሦስተኛው ትልቅ ፓርቲ ነው።

6፤ አወዛጋቢውን በብሪታኒያ ጥገኝነት ጠያቂዎችን በሩዋንዳ የማስፈር ፖሊሲን የነደፉት የብሪታንያ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚንስትር ስቴላ ብሬቨርማን ዛሬ ኪጋሊ መግባታቸውን የብሪታንያ ጋዜጦች ዘግበዋል። ብሬቨርማን በሩዋንዳ በሚኖራቸው የሁለት ቀናት ቆይታ፣ ብሪታኒያ "ሕገወጥ" የምትላቸውን ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች በሩዋንዳ ለማስፈር በተደረሰው ስምምነት አተገባበር ዙሪያ ከአገሪቱ ባለሥልጣናት ጋር እንደሚነጋገሩ ተገልጧል። የብሪታንያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ የአገሪቱ መንግሥት በ"ሕገወጥ" መንገድ የሚገቡ ጥገኝነት ጠያቂዎችንና ስደተኞችን በሩዋንዳ ማስፈር ይችላል ሲል በቅርቡ መወሰኑ ይታወሳል።

7፤ የዩክሬን የምግብ እህል ምርት በጥቁር ባሕር ወደቦች በኩል ለዓለም ገበያ እንዲቀርብ ባለፈው ዓመት ሐምሌ ላይ ከሩሲያ ጋር የተደረሰው ስምምነት ዛሬ በድጋሚ ለአራት ወራት መታደሱን የፈረንሳዩ ዜና ወኪል ዘግቧል። ሩሲያና ዩክሬን ስምምነቱን ያደሱት፣ በተመድና በቱርክ አደራዳሪነት ለበርካታ ቀናት ድርድር ከተደረገ በኋላ ነው። ሩሲያ ስምምነቱ ለሁለት ወራት ብቻ እንዲታደስ ከቀናት በፊት ሃሳብ አቅርባ ነበር። ባለፈው ኅዳር ለአራት ወራት የታደሰው ይኼው ስምምነት፣ የቆይታ ጊዜው በዛሬው ዕለት ይጠናቀቅ ነበር። #share

  ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
252 views17:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-18 09:08:23 ኢትዮጵያን ""ብልፅግና""" የሚለውን ስም ትከሻዋ ላይ ጭነውባት፣ ከወደቀችበት መነሳት አቅቷት እየተንፈራፈረች ትገኛለች።

የቃላት ጋጋታ፡ የተረት ክምር፡ ራዕይ አልባ፡ ዝም ብሎ እንቶፈንቶ ነገር። እውነት ከአንድ ገዢ ፓርቲ፡ ያውም መስቀለኛ መንገድ ላይ የቆመችን ሀገር ከሚመራ አካል እንዲህ የቃላትና የተረት ትርዒትና አክሮባት የሚታይበት መግለጫ መስማት በህመም ላይ ሌላ ህመም ይጨምራል። መግለጫው ምንድን ነው የሚያወራው? ስለማነው የሚናገረው? እጅና እግር የሌለው፡ ጫፉን ለማግኘት ምጥ የሚያሲዝ፡ የእውር ድንብር አይነት ስሜት ውስጥ የሚከት እርባነ ቢስ መግለጫ ነው። ራስን ከተጠያቂነት አውጥቶ ሌሎችን ለመክሰስና ለመውቀስ ጋራ ሲቧጥጥ የሚታይበት መግለጫ። ብልጽግና ተሰርቶ ያላለቀ ፓርቲ፡ ጀምረው የተዉት፡ ጎዶሎ አካል ይዞ የቀረ መሆኑን ለመቶ ምናምነኛ ጊዜ የተጋለጠበት መግለጫ።

ኢትዮጵያ ብልጽግና የሚለው ስም የከበዳት ሆናለች። ስሙ ሸክም ነው። የሚላስ የሚቀመስ ብርቅ የሆነባትን ሀገር ''ብልጽግና'' የሚል ስም ትከሻዋ ላይ ጭነውባት ከወደቀችበት መነሳት አቅቷት ትንፈራፈራለች። ብልጽግናው ቀርቶ ሰው ሰላም አግኝቶ፡ የመኖር ህልውናውን ሳያጣ ወጥቶ የሚገባባት ሀገር ብትሆን ለአንድ ኢትዮጵያዊ ትልቅ ምርቃቱ ነው። ቶምቦላ ደረሰው ማለት ነው:: ሰዎቹ ዳመና ውስጥ ሆነው እኛ እነሱን ልናያቸው፡ እነሱም እኛን ሊያዩን አልቻሉም። ነገሩ አልተገናኝቶም ነው። እነሱ በብልጽግና መጠቅለያ ውስጥ ሆነው ዳመና እየዘገኑ በምናብ ይኖራሉ፡ ምስኪኑ ህዝብ ገርጥቶ፡ የሞት ሳል እያሳለ፡ ተራራ የሆነበትን ኑሮ ይገፋል። ወይ ወደ ዳመናው ውሰዱት፡ አልያም እናንተ መሬት ውረዱና ኑሮዉን ኑሩለት።

ማላገጫው ምሽቴን አደበዘዘው!
እናተ ግን መልዕክቴን ብቻ #ሼር አድርጉልኝ
መሳይ መኮንን

ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
249 views06:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-18 07:27:30 ማለዳ! ቅዳሜ መጋቢት 9/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ የሕወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ የፓርቲው ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት እንዲሆኑ ማጨቱን ቪኦኤ ዘግቧል። ሕወሃት የክልሉን ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ ካዋቀረ በኋላ፣ ከፌደራል መንግሥቱ ጋር በሚያደርጋቸው ድርድር መዋቅሩ መጽደቅ ይጠበቅበታል። የትግራይ ዓለማቀፍ ምሁራን ማኅበር ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ምክትል ፕሬዝዳንት ዕጩ እንድጠቁም በቀረበልኝ ጥያቄ መሠረት፣ ጡረተኛውን ጀኔራል ጻድቃን ገ/ተንሳይን እጩ አድርጌ አቅርቤያለሁ ማለቱ ይታወሳል። በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የሚቋቋመው፣ ፕሪቶሪያ ላይ በፌደራል መንግሥቱና ሕወሃት መካከል በተደረሰው የሰላም ስምምነት መሠረት ነው።

2፤ የገዥው ብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ሰሞኑን ያካሄደውን ስብሰባ አስመልክቶ ትናንት ማምሻውን ባወጣው መግለጫ፣ የፓርቲው ባለሥልጣናት ከጥላቻና ከግጭት ቀስቃሽ ንግግሮችና ድርጊቶች እንዲቆጠቡ አሳስቧል። ምሁራን፣ የሐይማኖት አባቶች፣ መገናኛ ብዙኀን፣ የማኅበረሰብ አንቂዎችም፣ ከጥላቻና ግጭት አባባሽ እንዲሁም የአገርን ሰላምና ደኅንነት ለአደጋ ከሚያጋልጡ ንግግሮች እንዲቆጠቡ ያሳሰበው ፓርቲው፣ የፍትህና ጸጥታ አካላትም እንዲህ ዓይነት ድርጊቶችን በቸልተኝነት እንዳይመለከቱ ጠይቋል። ፓርቲው አገሪቱ የገጠሟትን ችግሮች በዝርዝር መመርመሩን ገልጦ፣ ከዋና ዋና ችግሮች መካከል የታሪክ እዳዎች፣ የነጻነት አያያዝ ችግሮችና የኑሮ ውድነት ተጠቃሽ እንደሆኑ አብራርቷል።

3፤ የጉሙዝ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ የታሠሩ 46 አባላቱ መፈታታቸውን መናገሩን ዶይቸቨለ ዘግቧል። ሆኖም በመተከልና ካማሺ ዞኖች ከተከሰተው ግጭት ጋር በተያያዘ የታሠሩ አባላቱ በሙሉ አለመፈታታቸውን ፓርቲው መግለጡን ዘገባው አመልክቷል። ንቅናቄው ከስድስት ወር በፊት ትጥቁን ፈትቶ በሰላማዊ መንገድ ለመንቀሳቀስ ከክልሉ መንግሥት ጋር በፈረመው የሰላም ስምምነት መሠረት፣ ሦስት ሺህ የቀድሞ ታጣቂዎቹ ከማኅበረሰቡ ጋር መቀላቀላቸውን የንቅናቄው ሊቀመንበር ግራኝ ጉታ ተናግረዋል ተብሏል። የክልሉ ፖሊስ በበኩሉ፣ የሰው ሕይወት በማጥፋት ከተጠረጠሩት ውጭ ሌሎቹ በሙሉ ፕፈታሉ ማለታቸውን ዜና ምንጩ ጠቅሷል። ምርጫ ቦርድ የሰረዝኩትን የንቅናቄውን የሕጋዊ የፓርቲነት ፍቃድ መልሼ ሰጥቻለሁ ማለቱ ይታወሳል።

4፤ ባይደዋ ከተማ ላይ በብሄራዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር ያደረጉት የሱማሊያ ፌደራል መንግሥት እና የፌደራል ግዛቶች መንግሥታት ስምምነት ላይ መድረሳቸውን በጋራ ባወጡት መግለጫ መግለጣቸውን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የበይነ መንግሥታት ምክክሩ ያተኮረው፣ የአገሪቱን ተቋማት በማጠናከር፣ የጸጥታ መዋቅር ማሻሻያ በማድረግ እና የፋይናንስ ሥልጣኖችን ያልተማከሉ በማድረግ አስፈላጊነት ላይ ነው። በብሄራዊ ምክክሩ ላይ ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሐመድ እና የፌደራል ግዛቶች ፕሬዝዳንቶች የተሳተፉ ሲሆን፣ የፑንትላንድ ራስ ገዝ ፕሬዝዳንት አብዱላሂ ደኒ ግን እንዳልተሳተፉ ተገልጧል። ፑንትላንድ በምክክሩ አለመሳተፏ አሳሳቢ መሆኑን የገለጸው መግለጫው፣ ምክንያቱን ለማወቅ ወደ ፑንትላንድ ኮሚቴ እንዲላክ ተወስኗል ብሏል።

5፤ ዓለማቀፉ የነፍስ አድን ድርጅት አይ አር ሲ የዩክሬን የእህል ምርት በጥቁር ባሕር በኩል ለዓለም ገበያ እንዲቀርብ ባለፈው ሐምሌ የተደረሰው ስምምነት ካልታደሰ በምሥራቅ አፍሪካ የ40 ሚሊዮን ሰዎች ሕይወት አደጋ ላይ ይወድቃል በማለት አስጠንቅቋል። ተመድ ስምምነቱ ለአንድ ዓመት እንዲታደስ እንዲያደርግ ድርጅቱ ጠይቋል። ከስምምነቱ ወዲህ በጥቁር ባሕር በኩል ወደ ውጭው ዓለም ከወጣው የዩክሬን የምግብ እህል ውስጥ፣ ኢትዮጵያ፣ ሱዳን፣ ሱማሊያ፣ የመን እና አፍጋኒስታን የደረሰው 10 በመቶው ብቻ እንደሆነ ድርጅቱ ገልጧል። ሩሲያ ስምምነቱ ለሁለት ወራት ብቻ እንዲታደስ ሃሳብ አቅርባለች። በተመድና ቱርክ አደራዳሪነት ሩሲያና ዩክሬን የደረሱበት ስምምነት ባለፈው ኅዳር አንድ ጊዜ የታደሰ ሲሆን፣ ቀነ ገደብም ዛሬ ይጠናቀቃል። #share ይደረግ

ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
254 views04:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 21:35:41 ውድ የEMS Mereja ተከታዮች፣መፅሐፍ ማንበብ የእድሜ ልክ እውቀት ነው! ባልነው መሰረት የትረካ መፅሐፍ፤ እናቅርብ ወይስ ይቅር ብለን ለእናተው ባቀረብነው፣ የድምፅ መስጫ ላይ 90%ቱ ይቅረብ ባላችሁት መሰረት መፅሐፉን ልናቀርብላችሁ አስበናል። ስለሆነው የትረካ መፅሐፎቹን ከመግዛታችን በፊት፣ አሁን በእናተው ምርጫ የማን መፅሐፍ እንዲቀርብላችሁ እንደምትፈልጉ ከስር ባለው ኮመንት መስጫው ላይ፣ የምትፈልጉትን የመፅሐፍ ስም እንድታሳውቁን እንጠይቃለን። ብዙ ሰው የወደደውን መፅሐፍ የምናቀርብላችሁ ይሆናል። መፅሐፍ ማንበብ ሙሉሰው ያረጋል።
ቶሎ በሉና ከስር በኮመንት መስጫው ላይ ንገሩን
259 views18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 20:07:58 ዓርብ መጋቢት 8/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ ካለፈው ሳምንት ሐሙስ ጀምሮ በከተማዋ የባጃጅ ትራንስፖርት ላይ የጣለውን እገዳ ከነገ ጀምሮ እንደሚያነሳ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ መናገሩን የአገር ውስጥ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የባጃጅ አሽከርካሪዎች መደበኛ ትራንስፖርት በሌለባቸው አካባቢዎች እስከ 2 ነጥብ 45 ኪሎ ሜትር ርቀት ብቻ አገልግሎት እንዲሰጡና ባንድ ተሳፋሪ ከ5 ብር በላይ እንዳያስከፍሉ ቢሮው የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎትን ለመምራት ባዘጋጀው አዲስ መመሪያ ላይ ወስኛለሁ ማለቱን ዘገባዎቹ አመልክተዋል። አዲሱ መመሪያ፣ የስምሪት መስመሮችን፣ ታሪፎችንና የአገልግሎት መስጫ ሰዓትን የሚወስን እንደሆነ ተገልጧል። በመመሪያው መሠረት፣ ባጃጆች አገልግሎት የሚሰጡት ከንጋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ ሦስት ሰዓት ድረስ ብቻ ይሆናል ተብሏል።

2፤ የሕወሃት ሥራ አስፈጻሚ አባልና የድርጅቱ ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳ ከአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን ገለጻ ማድረጋቸውን በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል። ጌታቸው ለብሊንከን ገለጻ ያደረጉት፣ በትግራዩ ጦርነት ለተፈጸሙ ወንጀሎች ተጠያቂነት በማስፈን አስፈላጊነት፣ በፌደራል መንግሥቱና ሕወሃት መካከል የተደረሰውን ሰላም ስምምነት ለመቀልበስ በሚጥሩ ኃይሎችና የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርን በማቋቋም ሂደት ባጋጠሙ ተግዳሮቶች ዙሪያ መሆኑን ገልጸዋል። "በጦርነቱ በትግራይ ላይ የተፈጸሙ ወንጀሎች ከብሄራዊ የሕግ ማዕቀፍ የሚያልፉ ናቸው" ያሉት ጌታቸው፣ መንግሥት ባዘጋጀው የሽግግር ፍትህ ማዕቀፍ ላይ "ዓለማቀፍ ጥረቶች ያስፈልጋሉ" ብለዋል።

3፤ ስድስት አባላት ያሉት የተመድ እና አውሮፓ ኅብረት ልዑካን ቡድን በአማራ ክልል ተገኝቶ በፌደራል መንግሥቱና በሕወሃት መካከል በተደረሰው የሰላም ስምምነት አተገባበር ዙሪያ ከክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር መነጋገሩን የአገር ውስጥ ዜና አውታሮች ዘግበዋል። ልዑካን ቡድኑ የሰላም ስምምነቱ አተገባበር በአማራ ክልል በኩል ምን እንደሚመስል የመገምገም፣ ለአተገባበሩ እንቅፋት የሆኑ ችግሮችን የመለየት እና በተግዳሮቶቹ ዙሪያ የክልሉን ባለሥልጣናት ምላሽ እና ፍላጎቶች የመስማት ተልዕኮ እንዳለው ዘገባዎቹ አመልክተዋል።

4፤ ከሱማሊያ ወደ ኢትዮጵያ የሚሰደዱ ስደተኞች ቁጥር ማሻቀቡ በሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት ላይ ከፍተኛ ጫና መፍጠሩን የዓለም ጤና ድርጅት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ድርጅቱ፣ ለስደተኞቹ መርጃ ተጨማሪ የመድኃኒት፣ የሕክምና ቁሳቁሶችና የሕክምና ባለሙያዎች ድጋፍ ያስፈልጋል ብሏል። ድርጅቱ፣ ካለፈው ጥር ወር ጀምሮ ከሱማሊያ ሕጻናትና ሴቶች የሚበዙባቸው ከ100 ሺህ በላይ ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያው መግባታቸውን ገልጧል። አብዛኞቹ ስደተኞች ተጠልለው የሚገኙት በክልሉ ዶሎ ዞን እንደሆነ የገለጠው ድርጅቱ፣ ለስደተኞቹና በከባድ ድርቅ ለተመታው የስደተኞቹ ተቀባይ ማኅበረሰብ ለ9 ወራት ሰብዓዊ ዕርዳታ ለማቅረብ፣ 101 ሚሊዮን ዶላር ያስፈልጋል ብሏል።

5፤ ዓለማቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ዛሬ በሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ላይ የእስር ማዘዣ አውጥቷል። ፍርድ ቤቱ በፕሬዝዳንት ፑቲን ላይ የእስር ማዘዣ ያወጣው፣ በዩክሬን ላይ ተፈጽመዋል ላላቸው የጦር ወንጀሎች ተጠያቂ ናቸው በማለት ነው። ፍርድ ቤቱ፣ ፕሬዝዳንት ፑቲን ሕጻናትን ጨምሮ ዩክሬናዊያን ዜጎችን ከሕግ ውጭ ወደ ሩሲያ በመላክ ወንጀል ፈጽመዋል ብሏል። በፍርድ ቤቱ በታሪኩ የተመድ ጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ አባል በሆነች አገር መሪ ላይ የእስር ማዘዣ ሲያወጣ የአሁኑ የመጀመሪያው ነው። ሩሲያ የዓለማቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤቱን መመስረቻ ስምምነት ፈርማ የነበረ ቢሆንም፣ ፍርድ ቤቱ ከ6 ዓመት በፊት ሩሲያ የዩክሬኗን ክራይሚያ ግዛት "በወረራ ይዛለች" የሚል ሪፖርት ማውጣቱን ተከትሎ ግን ፊርማዋን አንሳታለች።

6፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 53 ብር ከ8305 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 54 ብር ከ9071 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 61 ብር ከ9108 ሳንቲም እና መሸጫው 63 ብር ከ1490 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ57 ብር ከ0711 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ58 ብር ከ2125 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። አንድ የቻይና ዩዋን ደሞ በ7 ብር ከ0609 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ7 ብር ከ2021 ሳንቲም እንደተሸጠ ባንኩ ገልጧል።#share
ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ
@emsmereja
@emsmereja
262 views17:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 16:31:35
ብዙ ጊዜ የመንግስትን ምላሽ ለማግኘት ስልክ ስደውልላቸው ''እባክዎትን የፈለጓቸው ሰው ዳመና ላይ ናቸውና ቆየት ብለው ይደውሉ'' የሚል በሚያምር ድምጽ የምሰማው ለካ ለዚህ ነው። ዶ/ር ለገሰ ዳመና ላይ ተሰቅለው እንዴት የህዝብ ግንኙነት ስራዎን ይሰራሉ? አረ! በፈጠርዎ ወደ ምድር ይውረዱና ያናግሩን?! እሱን ዳመና ግን ቦረና ላይ ዝናብ አድርገውት ቢጥሉልን ወገን ትንሽ እፎይ ይል ነበር። አይ ኮሚኒኬተር?! #ሼር
መሳይ መኮንን
@emsmereja
232 views13:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 12:45:05
ሚዲያዎች እባካችሁን ዶክተር ነን የሚሉ ሰዎችን ከማቅረባችን በፊት፣ መድሀኒታቸውን መውሰዳቸውን አረጋግጡ

ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ
                                   @emsmereja
253 views09:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ