Get Mystery Box with random crypto!

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ) Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ)
የሰርጥ አድራሻ: @zemedkun_zemede
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.26K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 18

2023-03-17 08:09:39 ማለዳ! ዓርብ መጋቢት 8/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ የግብጽ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ሁሉም አማራጮች ክፍት ናቸው በማለት መናገሩን""ሃላፊነት የጎደለው" ንግግር በማለት እንዳወገዘው ፋና ብሮድካስት ዘግቧል። ኢትዮጵያ፣ የግብጽ ዛቻ የተመድ እና አፍሪካ ኅብረት ቻርተሮችን እንዲሁም በግድቡ ላይ ከራሷ ከግብጽ እና ሱዳን ጋር የተደረሰውን የሦስትዮሽ ስምምነት የሚጻረር መሆኑን መግለጧን ዘገባው ጠቅሷል። ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ ግብጽ በግድቡ ዙሪያ "ተገቢ እና ሕጋዊ ካልሆኑ" መግለጫዎችን ከመስጠት እንድትቆጠብ ማሳሰቡንም ዘገባው አመልክቷል።

2፤ በደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን አሁንም በርካታ ሰዎች ታስረው እንደሚገኙ ቪኦኤ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል። አሁንም እስር ላይ ከሚገኙት መካከል፣ ቁጥራቸው ያልታወቁ የምክር ቤት አባላት ይኙበታል መባሉን ዘገባው ጠቅሷል። የደቡብ ክልል ፖሊስ በበኩሉ፣ ከዞኑ የታሠሩት ሰዎች ከ40 እንደማይበልጡ ገልጦ፣ የመታሠራቸው ምክንያት "ብጥብጥ ከማስነሳት" ጋር የተያያዘ መሆኑን መናገሩን ዘገባው አመልክቷል። ሆኖም እስሩ በአብዛኛው ከጉራጌ ዞን የክልልነት ጥያቄ ጋር በቀጥታ የተያያዘ ስለመሆኑ፣ ዘገባዎች ሲወጡ መቆየታቸው ይታወሳል። ከዞኑ ዋና ከተማ ወልቂጤ የተያዙት ሰዎች፣ ወደ ቡታጅራ ከተማ ተወስደው እንደታሠሩ ቤተሰቦቻቸው መናገራቸውን ዘገባው ጨምሮ አመልክቷል

3፤ የኢትዮጽያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ፣ ሰሞኑን በኢትዮጵያ ጉብኝት ካደረጉት የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን ጋር አዲስ አበባ ውስጥ መወያየታቸውን ኮሚሽኑ ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል። የኮሚሽነሩና የብሊንከን ውይይት፣ በሰብዓዊ ዕርዳታ ተደራሽነት፣ በድርቅና ግጭት ተጎጂዎች የሰብዓዊ ዕርዳታ ፍላጎት እና በወንጀል ተጠያቂነት ዙሪያ ያተኮረ እንደነበር ኮሚሽኑ ጠቅሷል። የመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች ያልተመጣጠነ ኃይል መጠቀም፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች፣ ጋዜጠኞች እና የፖለቲካ ፓርቲ አባላት እስሮች ጭምር ውይይት እንደተደረገባቸው ተገልጧል።

4፤ አሜሪካ ለሱማሊያ ጦር ሠራዊት ልዩ ኮማንዶ "ደናብ" የምትሰጠውን ሥልጠናና የወታደራዊ ትጥቅ አቅርቦት እንድትቀጥል ከሱማሊያ ጋር ስምምነት መፈረሟን የሱማሊያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። አሜሪካ ለ"ደናብ" ልዩ ብርጌድ አባላት ሥልጠና ከመስጠትና ትጥቅ ከማቅረብ በተጨማሪ፣ ለእያንዳንዱ ሰልጣኝ 300 ዶላር ወርሃዊ አበል ትከፍላለች። "ደናብ" ልዩ ብርጌድ፣ ከአልሸባብ ጋር በሚደረገው ሁለንተናዊ ጦርነት ቁልፍ ሚና እየተጫወተ እንደሆነ ይነገርለታል። ከአሜሪካ በከል ስምምነቱን የፈረሙት፣ በሱማሊያ የአሜሪካ አምባሳደር ላሪ አንድሬ ናቸው ተብሏል።

ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ
@emsmereja
288 views05:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-16 20:36:33
እንዳትሸወዱ
ሁሌም ጥያቄያችን መሆን ያለበት፤
""""አንድ ሀገር ድጋፍ አደረገ ሲባል፣ ስንት ሰጠ? ሳይሆን ምን ወሰደ ይሁን። አሺ?
@emsmereja
290 views17:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-16 20:16:13 የዕለተ ሐሙስ መጋቢት 7/2015 ዓ.ም ውሎ ዐበይት ዜናዎች

1፤ ኢሰመኮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በባለ ሦስትና ባለ አራት እግር ባጃጆች ላይ ከየካቲት 30 ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ በመላ ከተማዋ የጣለውን እገዳ እንዲያነሳ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። ኮሚሽነ፣ እገዳው በተለያዩ ሰብዓዊ መብቶች ላይ "ተገቢ ያልሆነ ገደብ የሚጥል" እና በሹፌሮች፣ በቤተሰቦቻቸውና በባጃጅ ተጠቃሚዎች ላይ ችግር የፈጠረ ርምጃ መሆኑን ገልጧል። የከተማዋ አስተዳደር፣ የሥራ ፍቃድ ያልተሰጣቸው10 ሺህ ባጃጆች እንዲሁም ከተፈቀደላቸው መስመር ውጪ በዋና መንገዶች ላይ የሚሠሩ ባጃጆች መኖራቸውን ጠቅሶ፣ "አገልግሎትን የሚያሻሽል አሠራር እስክዘረጋ እገዳውን ጥያለሁ ማለቱን ኢሰመኮ ጠቅሷል። ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ፣ አስተዳደሩ አነስተኛ ገቢ ያላቸውን ነዋሪዎች፣ አካል ጉዳተኞችን፣ አረጋዊያንን፣ ሴቶችንና ሕጻናትን ታሳቢ ያደረገ ዘላቂ መፍትሄ እንዲፈልግ ጠይቀዋል።

2፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማዋን ከፍተኛ የመኖሪያ ቤት እጥረት ለመቅረፍ በመንግሥትና በግል አጋርነት 100 ሺህ መኖሪያ ቤቶችን ለማስገንባት ዛሬ ከግል ባለሃብቶች ጋር ስምምነት መፈራረሙን የከንቲባ ጽሕፈት ቤት በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል። መኖሪያ ቤቶቹ በ70/30 የቤት መርሃ ግብር እንደሚገነቡ የገለጠው አስተዳደሩ፣ መኖሪያ ቤቶቹ መካከለኛ ገቢ ያላቸውን የከተማዋ ነዋሪዎች ተጠቃሚ ያደርጋሉ ብሏል። አስተዳደሩ፣ ለቤቶቹ ግንባታ በቂ መሬት ማቅረቡንና ግንባታውም በሁለት ወራት ውስጥ እንደሚጀመር ገልጧል።

3፤ የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ዛሬ ወደ ምዕራብ አፍሪካዊቷ ኒዠር ተጉዘዋል። ብሊንከን ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከሕወሃት ባለሥልጣናት በተጨማሪ፣ ከሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችና ከረድኤት ድርጅቶች ተወካዮች ጋር ተነጋግረዋል። ዛሬ ረፋዱ ላይ ደሞ፣ ብሊንከን በቅርቡ ዋሽንግተን ላይ የተካሄደው የአሜሪካና አፍሪካ መሪዎች ጉባኤ የተስማማባቸውን የአሜሪካና አፍሪካ የትብብር መስኮች ማጎልበት በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ጋር እንደተወዩ በትዊተር ገጻቸው ገልጸዋል።

4፤ የሱማሊያ ፌደራል መንግሥት ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሐመድ እና የፌደራል ግዛቶች መሪዎች ለኢትዮጵያ አጎራባች በሆነችው ባይደዋ ከተማ ዛሬ ብሄራዊ ምክክር ጀምረዋል። የፌደራል መንግሥቱ እና የፌደራል ግዛቶች ምክክር አጀንዳዎች፣ የአገሪቱን የጸጥታ መዋቅር መልሶ በማዋቀር አስፈላጊነት፣ የበጀትና ሌሎች ፋይናንስ ነክ ሥልጣኖችን ያልተማከለ ማድረግ በሚችልበት ሁኔታ እና በፌደራል እና በፌደራል ግዛቶች ደረጃ በሚካሄዱ ምርጫዎች ዙሪያ እንደሆነ የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። በምክክሩ ላይ ከፑንትላንድ ራስ ገዝ ፕሬዝዳንት አብዱላሂ ደኒ በስተቀር የሁሉም ግዛቶች ፕሬዝዳንቶች ተገኝተዋል ተብሏል። ፕሬዝዳንት ሞሐመድ ሥልጣን ከያዙ ወዲህ፣ ቀደም ሲል በፌደራል መንግሥቱ እና በተወሰኑ የፌደራል ግዛቶች መካከል ሻክሮ የቆየውን የበይነ መንግሥታት ግንኙነት ለመጠገን ጥረት ሲያደርጉ ቆይተዋል።

5፤ የተመድ ጸጥታው ምክር ቤት በደቡብ ሱዳን ያሠማራውን የሰላም አስከባሪ ተልዕኮ ቆይታ ላንድ ዓመት አራዝሟል። 17 ሺህ ያህል ሰላም አስከባሪ ወታደሮች ያሉት የሰላም ማስከበር ተልዕኮው፣ በዓመት በዓለም ከፍተኛው 1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር በጀት የሚወጣበት ተልዕኮ ነው። የሰላም ማስከበር ተልዕኮው፣ ሰላማዊ ሰዎችን ከጥቃት የመከላከል፣ ለሰብዓዊ ዕርዳታ ሥርጭት ምቹ ሁኔታ የመፍጠር፣ በፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር እና በተቃዋሚው መሪ በተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ሬክ ማቻር መካከል የተደረሰውን የሰላም ስምምነት አተገባበር የመደገፍ እና ዓለማቀፍ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን የመከታተል ሃላፊነት አለበት።

6፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 53 ብር ከ8251 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 54 ብር ከ9016 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 62 ብር ከ2387 ሳንቲም እና መሸጫው 63 ብር ከ4835 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ57 ብር ከ4421 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ58 ብር ከ5909 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼርርር ይደረግ
@emsmereja
@emsmereja
292 views17:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-13 07:43:05 """"የጠዋት ዜናዎች ሰኞ መጋቢት 4/2015 ዓ.ም

1፤ ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ትናንት በአዲስ አበባ ጠቅላላ ጉባኤ እንዳላካሂድ ተከልክያለሁ ሲል ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ አስታውቋል። ፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤውን ማካሄድ ያልቻለው፣ ጠቅላላ ጉባኤው የተጠራበት ጋምቤላ ሆቴል ጉባኤውን እንዳናስተናግድ የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ አዞናል በማለቱ እንደሆነ ፓርቲው ገልጧል። ሆኖም ፓርቲው ለጉባኤው ከአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ የተጻፈ የፍቃድ ወረቀት ይዞ እንደነበር ተናግሯል።

2፤ መንግሥት ቅዳሜ'ለት በአዲስ አበባ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በሽግግር ፍትህ ፖሊሲ አማራጮች ረቂቅ ሰነድ ላይ ለመወያየት ከጠራው ስብሰባ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሰነዱን ወቅታዊነት መተቸታቸውን ሪፖርተር ዘግቧል። የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካዮች ከሽግግር ፍትህ በፊት አገራዊ መግባባትና የግጭቶች መቆም ይቅደም በማለት ተመሳሳይ አቋም ማንጸባረቃቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ፓርቲዎቹ የአገሪቱ ሰላምና ጸጥታ የሽግግር ፍትህ ለማስፈን አመቺ አለመሆኑን የጠቀሱ መሆኑን ያመለከተው ዘገባው፣ ፍትህ ሚንስቴር ግን ለፓርቲዎቹ ስጋት ምላሽ የሚሰጡ ተወካዮቹን እንዳልላከ አውስቷል። በስብሰባው ከተሳተፉት ፓርቲዎች መካከል፣ ኢዜማ፣ አብን፣ መኢአድ፣ እናት ፓርቲ እና ኢሕአፓ ይገኙበታል ተብሏል።

3፤ አዲስ አበባ የሚገኘው የአፍሪካ ኅብረት ዋና መስሪያ ቤት በሳይበር ጥቃት እንደተመታ ፎርቹን ዘግቧል። በሳይበር ጥቃቱ ሳቢያ፣ የድርጅቱ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የድርጅቱን የኮምፒውተር ቴክኖሎጂ ሥርዓት ወዲያውኑ እንደዘጉትና በዚህም ሳቢያ በርካታ ሥራዎች ላንድ ሳምንት እንደተስተጓጎሉ መረዳቱን ዘገባው ጠቅሷል። የሳይበር ጥቃቱ በበርካታ ኮምፒውተሮች ላይ ጉዳት ማድረሱን የጠቀሰው ዜና ምንጩ፣ ድርጅቱ ጥቃቱን ያደረሰውን አካል ለመለየት፣ ምርመራ መጀመሩን አመልክቷል።

4፤ የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት ሊቀመንበር ጀኔራል ቡርሃንና ምክትላቸው ጀኔራል ደጋሎ ላንድ ወር የዘለቀውን ቅራኔያቸውን በመፍታት የአገሪቱን ብሄራዊ ጸጥታ በበላይነት የሚቆጣጠር ኮሚቴ ማቋቋማቸውን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ኮሚቴው ከመደበኛ ሠራዊቶች፣ ከመንግሥት ተቋማትና የሽግግር ሰነዱን ከፈረሙ ታጣቂ ቡድኖች እንደሚውጣጣ ዘገባዎች አመልክተዋል። ጀኔራል ቡርሃንና ጀኔራል ደጋሎ ቅራኔ ውስጥ የገቡት፣ ጀኔራል ቡርሃን በቅርቡ በተፈረመው የሽግግር የፖለቲካ ሰነድ ውስጥ ተጨማሪ የፖለቲካ ኃይሎች ካልተካተቱ ሥልጣን አላስረክብም በማለታቸውና ጀኔራል ደጋሎ ደሞ የቡርሃንን አቋም በመቃወማቸው ነበር።

5፤ የሱማሊያ መንግሥት ከበድ ያሉ አንቀጾችን የያዘ የጸረ-ሽብር ሕግ አርቅቋል። የጸረ-ሽብር ሕጉ፣ መንግሥት በሕግ የተፈረደባቸው የአሸባሪ ቡድን አባላት ንብረቶችን እንዲሁም ለሌላ ሰው ያስተላለፏቸውን ንብረቶች ጭምር እንዲወርስ ሥልጣን እንደሚሰጥ የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ረቂቅ ሕጉ የሽብር ክሶች በወታድራዊ ፍርድ ቤት ብቻ እንዲታዩ እንደሚደነግግ ዘገባዎቹ አመልክተዋል። ረቂቅ ሕጉ በፓርላማው የጸደቀ ሲሆን፣ የላይኛው እንደራሴዎች ምክር ቤት እና ፕሬዝዳንቱ ሲያጸድቁት ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል።

6፤ የደቡብ አፍሪካ የሙስና ተቆጣጣሪ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ሴሪል ራማፎዛ ከተጠረጠሩበት የሙስና ቅሌት ነጻ ሆነው አግኝቻቸዋለሁ ማለቱን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ራማፎዛ፣ ከገጠር ባድማቸው በዘራፊዎች ከ500 ሺህ ዶላር በላይ ሲዘረፉ ለፖሊስ ያላሳወቁት፣ ገንዘቡን በሙስና ስሏገኙት ሊሆን ይችላል የሚል ክስ ቀርቦባቸው ነበር። ጸረ ሙስና ኮሚሽኑ ግን፣ ፕሬዝዳንት በክስተቱ ሥልጣናቸውን ያላግባብ እንዳልተጠቀሙ ወይም የስነ ምግባር መርሆዎችን እንዳልጣሱ እና ዝርፊያውን በሦስት ሳምንት ውስጥ ለፖሊስ እንዳሳወቁ ገልጧል። የአገሪቱ ፓርላማ ያቋቋመው መርማሪ ኮሚሽን፣ የፕሬዚዳንቱ ድርጊት መልስ ሊሰጡበት የሚገባቸው ነው የሚል ሪፖርት ማውጣቱ ይታወሳል። #ሼርርር
@emsmereja
@emsmereja
10 views04:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-12 14:34:50
አይ ባለጌዜ
መረጃውን እናቀርብላቹሃለን
188 views11:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 22:10:42
ከዚህ በላይ ግፍ ምናለ? በኦሮሚያ 1,000 የአማራ ብሔር ተወላጆች ህፃናት ላይ የተፈፀመው ግፍ


ይህንን ጉድ ይመልከቱ
257 views19:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 08:52:49 ክብሯን የEMS Mereja ተከታዮቻችን እንደምን አላችሁ፣ እስካሁን የEMS አባላትን በተለይ የመሳይና የእኔ የፋሲልን መልዕክቶችን ብቻ ስናደርሳችሁ ነበር። ሆኖም ግን ከእናተው በተደጋጋሚ በመጣ አስተያየት መሰረት፣ የተለያዩ መረጃዎችን ቶሎ ቶሎ እንድናደርሳችሁ በጠየቃቹን መሰረት፤ የእኛንና የተለያዩ ዜናዎችን በዚሁ ቻናል የምናደርሳችሁ ይሆናል። ከእናተ የሚጠበቀው መረጃዎቹን፣ ለብዙ ሰው እንዲደርስ #ሼርርር በማድረግና ማስታወቂያዎችን በቅናሽ ዋጋ እንድታሰሩን ማድረግ ብቻ ነው። ከፊትለፊታችን እየመጣ ያለው ከባድ ጊዜ ነውና ተጋግዘን እንለፈው። ለእኛ መረጃዎችን፣ አስተያየቶችን ለማድረስና የማስታወቂያ ስራዎችን ለማሰራት የምትፈልጉ ከሆነ፣ በዚህ @infoetrobot ይህንን በመጫን start ብላችሁ አናግሩን ይደርሰናል። ለህዝባችን ነፃነት እየታገልን እናታግላቹሃለን፣ እያየን ያለነው ነገር ከአዕምሮ በላይ ነውና አንድ እንሁን። መረጃውን ለብዙ የቴሌግራም ጓደኞቻችሁ #ሼርር በማድረግ አድርሱልን
ለአስተያየቶች @infoetrobot

@emsmereja
293 views05:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 23:30:54 ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ሳይጠሩ አቤት ብለዋል። 15 በዲያስፖራ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ማህበራት በግልጽ ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በግላቸው እንዲደርሳቸው የጻፉት ደብዳቤ ነበር። ለመንግስት አልተጻፈም። ከደብዳቤው መንፈስ እንደምንረዳው ማህበራቱ መንግስትን አምነው አልነበረም ላለፉት 5ዓመታት ከዶ/ር አብይ ጎን ቆመው የድርሻቸውን ሲወጡ የነበሩት። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገቡትን ቃል እንደዋስትና ወስደው ነበር በየአቅጣጫው ሲሰሩ የከረሙት። ብልጽግና የሚመራው መንግስትን ስለመደገፋቸው አልያም እውቅና የሰጡት መንግስት ሆኖ መልካም ግንኙነት መፍጠራቸውን አልገልጹም። እስከማውቀውም ግንኙነቱ እንደዛ አልነበረም። ለዚህም ነው ደብዳቤአቸው በቀጥታ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲሆን ያደረጉት። የዶ/ር ለገሰ ጥልቅ ብሎ ምላሽ መስጠት አስገራሚ ነው። እሳቸውም እንደጉዑዛኑ የህወሀት ኮሚኒኬተሮች አንድ አስልቺ ትርክት ይዘው ለመወረፍ ሞክረዋል። ሳይጠሩ አቤት ማለታቸው ሳያንስ የጻፉት ደግሞ የኢህአዴግ የአንጎል ማምረቻ ከአንድ ዓይነት ምርት ውጭ የተለየ እንደማያመርት የሚያመላክት ነው።

ዶ/ር ለገሰ ሞቱን፡ ግድያውን፡ የተፈጠረው ምስቅልቅል ያለ ነገር ሁሉ ተፈጥሮአዊ፡ የለውጥ ጊዜ መገለጫ ስለሆነ አምናችሁ ተቀበሉ ዓይነት የሚመስል ነገር ይዘው መጥተዋል። መንግስታቸው ሲያጠፋም፡ ሲገድል፡ ሲያበላሽም ምስጋና እንጂ ወቀሳ አይገባውም ለማለት አፋቸው ላይ ደርሶ የመለሱት ይመስለኛል። የኢትዮጵያ ህዝብ ስለሚሆነው ነገር ሁሉ የማንንም ስብከትና ጉትጎታ ስይፈልግ መረዳት የሚችለው መሆኑ አይጠፋቸውም። ህይወት የሌለው የኩረጃ ፖለቲካ ሰላባ በመሆናቸው አንድ ዓይነት ዲስኩር ይዘው አደባባይ መውጣትን ነው የመረጡት። ቢያንስ በጨዋነት የጀመሩትን በትህትና ቢጨርሱት አንጎላቸውን ተጠቀሙበት ብለን ከቁምነገር እንወስድላቸው ነበር። ያቺኑ የኢህአዴግ ቤት ማሸማቀቂያ የሆነው ስድብ መለስ ምላሽ መስጠታቸው ግምት ላይ ከመውደቅ ያለፈ የሚያገኙት ነገር የለም። የተሰጠውን ለመጋት የተዘጋጀ የካድሬ መንጋን እያሰቡ የሰጡት ምላሽ ይመስለኛል።

ለውጡ እንዴት መጣ? ህወሀት ከአዲስ አበባ ሸሽቶ መቀሌ እንዲገባ የተደረገበት ትግል ላይ ማን ምን ሚናና ድርሻ ነበረው? የሚለውን ለህዝብ ፍርዱን መተው ነው። እንኳን እሳቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በስም ያወቅናቸው ለውጡ ሊከሰት በዋዜማው መሆኑን መካድ የሚያስፈልገው አይመስልም። በኢህ አዴግ ውስጥ የተደረገውን ትግል እውቅና መስጠት ተገቢ ቢሆንም እስከሞት ድረስ ዋጋ የከፈሉትን ዋጋ ለማሳጣት የሚሄዱበት ርቀት ግን እጅግ አሳፋሪ ነው። የምንተዋወቅ መስሎኝ ነበር። ከዶ/ር ለገሰ ቱሉ ያነሰ ሚና በለውጡ ላይ ያለው የህወሀት ወገን ካልሆነ በቀር ዛሬ እሳቸው በጭቃ ጅራፍ የተጋረፉት የዲያስፖራ ስብስብ የለም። መገፋፋትና የታሪክ ሽሚያ ውስጥ መግባት አስፈላጊ አይደለም። እኛ ለውጥ አመጣን፡ እናንተንም ወደሀገር ቤት አስመጣን፡ እያሉ መኮፈስ ትዝብት ላይ ይጥላል።
መሳይ
324 views20:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-09 20:51:11

413 views17:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-07 10:55:49 ወዴት እያመራን ይሆን? የሆነ የሚቀፍ ስሜት ውስጤን መውረር ከጀመረው ሳምንታት ተቆጥረዋል። የሆነ አንዳች አይነት ክስተት በቅርቡ ሳይመጣ አይቀርም የሚል አስቀያሚ ድብርት ሁለመናዬን ከተቆጣጠረው ከረምረም ብሏል። ወደኮንፌዴሬሽን እያመራን ይሆን? ህወሀት ትግራይ ላይ ስለሚያደርገው፡ ስለሚፈልጠውና ስለሚቆርጠው ፌደራል መንግስት ጉዳዩም እስከማይመስል በዳር ተመልካችነት ተቀምጧል። የኦሮሚያ ክልል እንደፈለገው ሲሆን፡ የጨበጠውን ስልጣን የራሱን ክልል በማጠናከሩ ላይ መጠመዱ ሲታይ ሀገሪቱ ላይ ምን እየተፈጠረ ነው የሚያሰኝ ፍርሃት ሰውነትን ይንጣል። አማራ ክልል አዲስ የትግል ስልት ያስፈልጋል ዓይነት ቅኝት ውስጥ ገብቷል። ብልጽግናዎች እየተናበቡ አይመስልም። ደቡብ ክልል ተሽንሽኖ እስኪያልቅ መጻዒ እድሉ አለየለትም። ሶማሌ፡ አፋር፡ ቤንሻንጉል፡ ጋምቤላ ሁሉም ክልሎች በራሳቸው ዓለም ውስጥ እየኳተኑ ነው። ግራ የገባቸው ሆነው ይታያሉ። ሁሉም በየፊናው የተባለ ይመስላል።

እውነት ለመናገር የሚታየው ነገር የኮንፌደሬሽን ዋዜማ ነው። አንዱ ክልል ከአንዱ ጋር በምንም የሚገናኝበት፡ የሚተሳሰርበት ነገር እየጠፋ ነው። ባለፈው ሳምንት በዝግ ስብሰባ ያደረጉት የአማራና የኦሮሚያ ብልጽግናዎች በሁለት ራሳቸውን በቻሉ ሀገራት መሀከል የተደረገ በሚመስል ስምምነት ነው የተለያዩት። ክልል የግል፡ ሀገር የጋራ ዓይነት ጨዋታ በደንብ ይስተዋላል። የበላይ ስልጣኑን የጨበጠው የኦሮሚያ ብልጽግና መሬት የመሰብሰብ፡ ግዛት የማስፋፋት አጀንዳ ላይ ተጥዷል። ከሲዳማ ክልል ጋር የቀጠለው የግዛት ይገባኛል ጦርነት ሳምንቱን ተሻግሯል። ከቤንሻንጉል ጉምዝ የተወሰኑ ወረዳዎችን መጠቅለሉ እየተነገረ ነው። ከደቡብ ክልል የሚፈልጋቸው መሬቶች አሉ። ክልሉ ተሸንሽኖ እስኪያልቅ እየጠበቀ ነው። ሀገር የመምራት ሃላፊነቱን ዘንግቶ(እርግፍ አድርጎ ትቶት ወይም ሆን ብሎ) ክልል የመገንባቱና ሀገር ለመሆን የሚያስችል ዝግጅቶች የሚመስሉ ተግባራት ላይ ትኩረቱን አድርጓል።

አንዳንድ የክልል ባለስልጣናትን ሰሞኑን አነጋግሬ ነበር። ደብሮአቸዋል። የሚሆነው ነገር ቅፍፍ ብሎአቸዋል። አላወቅነውም እንጂ ተነጣጥለን እየኖርን ነው የሚል ስሜት ውስጣቸው ገብቷል። በ2013 መስከረም ወር፡ ህወሀት ሰሜን ዕዝን ከመምታቱ አንድ ወር በፊት ያወጣው አንድ ሰነድ ነበር። ሰነዱ የኮንፌዴሬሽን ስርዓት ኢትዮጵያ ላይ እንዲሰፍን የሚያበረታታና የሚሰብክ ነው። ሁሉም ክልሎች ከሀገር በመለስ በሁሉ መስክ ራሳቸውን የሚመሩ፡ የራሳቸው ሰራዊት የሚኖራቸው፡ ከፊል በሆነ ስልጣን የውጭ ጉዳይ ግንኙነት የሚያደርጉ፡ ኢትዮጵያ የምትባለው ሀገርና ማዕከላዊ መንግስት ሲፈልጉ የሚገናኙት፡ በጋራ ሀብት የሚካፈሉበት በአጭሩ ኮንፌደሬሽን ስቴትስ ሆነው የሚታዩበት መዋቅር እንዲተከል ህወሀት በግልጽ ፍላጎቱን አሳይቷል። በጦርነቱ ወቅት ሙከራ አድርጎ አሳይቶናል። አሁንም በአንዳንድ እንቅስቃሴዎቹ ኮንፌደሬሽንን ዳር ዳር እያለበት ነው።

ጎበዝ እስቲ አይናቹን ግለጡ። በዙሪያችሁ የሚሆነውን ተመልከቱ። የአማራ ተወላጆች ከአዲስ አበባ ዙሪያ የሚፈናቀሉበትን ምክንያት መርምሩ። ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ ለመግባት የኦሮሚያ ክልል ፍቃድ ያስፈለገበት ሚስጢሩን ፈትሹ። በአዲሱ የትምህርት ፖሊሲ ሀገራዊ የመግባቢያ ቋንቋ እንዳይኖር የተደረገበት ሴራውን ለምንድን ነው ብላችሁ ጠይቁ። ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን በየክልሉ የተለያዩ ሲኖዶሶች እንዲፈጠሩ ውስጥ ለውስጥ እየተዘረጋ ያለው ወጥመድ መጨረሻው ምን እንዲመጣ ተፈልጎ ነው?! በእርግጥም ክልሎች እንደፍጥርጥራችሁ የተባሉ ይመስል እንደፈለጋቸው እንዲወስኑና ከሌሎች ጋር የሚጋሯቸው ሀገራዊ ራዕዮች እየኮሰሱ የመጡበት ሁኔታ በግልጽ እግር አውጥቶ እየተራመደ ለእኔ ይታየኛል። እናም ፍርሃት ፍርሃት ይለኛል። ይህ ስሜት የእኔ ብቻ ይሆን? ምነው ቅዥት ባደረገው። የቀን ህልም ሆኖ ቢቀር ደስታውን አልችለውም። #ሼር በማድረግ አግዙኝ
ሙሉውን በዩቱቤ ተመልከቱት



መሳይ
562 views07:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ