Get Mystery Box with random crypto!

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ) Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ)
የሰርጥ አድራሻ: @zemedkun_zemede
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.26K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 11

2023-04-14 07:21:38 ዓርብ ማለዳ! ሚያዝያ 6/2015 ዓ.ም የEMS Mereja ዐበይት ዜናዎች

1፤ በትግራይ ክልል ጉብኝት እያደረጉ ያሉት በኢትዮጵያ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዋና ኃላፊ ክሎድ ጃቢዳር በመቀሌና ሽሬ ከተሞች ለሕጻናት በዕርዳታ መልክ የተከፋፈለ አልሚ ምግብ ገበያ ላይ በብዛት ሲሸጥ ድርጅታቸው መመልከቱን ትናንት በሰጡት መግለጫ ላይ መናገራቸውን የአገር ውስጥ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ኾኖም ኃላፊው፣ አንዳንድ ተረጂዎች ጥሬ ገንዘብ ለማግኘት ሲሉ ዕርዳታውን ለገበያ አቅርበውት ሊኾን እንደሚችል እንገምታለን ማለታቸው ተገልጧል። ከሕጻናት አልሚ ምግብ በተጨማሪ፣ ለተረጂዎች የተከፋፈለ ስንዴ ከታለመለት ዓላማ ውጭ በርካሽ ዋጋ ገበያ ውስጥ እየተሸጠ እንደኾነ ኃላፊው ገልጸዋል ተብሏል።

2፤ የኢትዮጵያ እና አሜሪካ የቢዝነስ ምክክር መድረክ ትናንት በዋሽንግተን መካሄዱን ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል። በምክክር መድረኩ ላይ፣ ከኹለቱም አገራት የተውጣጡ 100 ያህል የንግዱ ማኅበረሰብ ተወካዮች መገኘታቸውን ሚንስቴሩ ገልጧል። ጉባዔውን በንግግር የከፈቱት የገንዘብ ሚንስትር አሕመድ ሽዴ፣ የአሜሪካ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ሙዓለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ እንደጋበዙ ተገልጧል። በጉባኤው ላይ፣ የብሄራዊ ባንክ ገዢው ማሞ ምኅረቱና የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽነር ሌሊሴ ነሜ ጭምር ተገኝተዋል ተብሏል።

3፤ በአማራ ክልል ለቀናት የቀጠለው ተቃውሞ ጋብ ማለቱን የፈረንሳዩ ዜና ወኪል ዘግቧል። በባሕርዳር ከተማ ባንኮች እና ሱቆች ተከፍተው ሥራ መጀመራቸውን ነዋሪዎች መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ከሰሞኑ በነበረው ውጥረትና ግጭት፣ መዘዞ ከተማ ውስጥ ታጣቂዎች ከፖሊስ ጣቢያ ጦር መሳሪያ መዝረፋቸውን የዘገበው ደሞ ቪኦኤ ነው። በተያያዘ፣ በደቡብ ወሎ ዞን የሚንቀሳቀሱ የክልሉ ልዩ ኃይል አባላት ወደ መደበኛ ፖሊስ ወይም ወህኒ ቤት ፖሊስ ለመቀላቀል ፍቃደኛ ኾነዋል ሲል የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

4፤ በትግራይ ክልል በጦርነቱ ለተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በሽግግር ፍትህ ማዕቀፍ ተጠያቂነት በሚሰፍንበት ኹኔታ ዙሪያ ትናንት መቀሌ ውስጥ ምክክር እንደተደረገ የክልሉ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። በምክክሩ ላይ፣ የፍትህ ሚንስቴርና የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ተወካዮች እና የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ባለሥልጣናት እንደተገኙ ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።

5፤ የ"ኢትዮ ሰላም" ዩትዩብ ጣቢያ መስራች፣ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ ቴዎድሮስ አስፋው ትናንት በድጋሚ በመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር መዋሉን አዲስ ስታንዳርድ ዘግቧል። ጸጥታ ኃይሎች የቴዎድሮስን ፓስፖርት እና የሞባይል ስልክ መውሰዳቸውን ቤተሰቦቹ መናገራቸውን የጠቀሰው ዘገባው፣ ቴዎድሮስ የተወሰደው ወደ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ መኾኑን አመልክቷል። ጸጥታ ኃይሎች ቴዎድሮስን በቁጥጥር ስር ባዋሉበት ወቅት፣ ኹከትና ብጥብጥ በማስነሳት ወንጀል ተጠርጥረሃል በማለት እንደነገሩት ዘገባው ጨምሮ ገልጧል። ቴዎድሮስ በተመሳሳይ ወንጀል ተጠርጥሮ ለቀናት ከታሰረ.በኋላ፣ ባለፈው የካቲት አጋማሽ በ30 ሺህ ብር ዋስትና መፈታቱ ይታወሳል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
249 views04:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 23:25:38
ምን አይነት ዘመን ነው??!
#ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
259 views20:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 22:03:29 ሐሙስ ምሽት! ሚያዝያ 5/2015 ዓ.ም የEMS Mereja ዐበይት ዜናዎች

1፤ በኢትዮጵያ የሕጻናት አድን ድርጅት በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ሳቢያ 2.5 ሚሊዮን ሕጻናት እስካሁንም ከትምህርት ገበታ ውጭ እንደኾኑ ትናንት ባወጣው መግለጫ ገልጣል። ድርጅቱ፣ በትግራይ፣ አማራ እና አፋር ክልሎች በጦርነቱ ውድመት በደረሰባቸው አካባቢዎች ትምህርት ቤቶችን እንደገና አገልግሎት ለማስጀመር የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ጠቅሷል። በተለይ በትግራይ 85 በመቶዎቹ ትምህርት ቤቶች በጦርነቱ "ከባድ" ወይም "ከፊል ጉዳት" እንደደረሰባቸው በጥናት መረጋገጡን የጠቀሰው ድርጅቱ፣ በክልሉ ኹሉም ትምህርት ቤቶች ዛሬም ዝግ ናቸው ብሏል። ባጠቃላይ በመላ አገሪቱ ባሁኑ ወቅት 3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሕጻናት ከትምህርት ገበታ ውጭ እንደኾኑ ድርጅቱ ጨምሮ ገልጧል።

2፤ "አቫንቲ ኮምንኬሽን" የተሰኘው የብሪታኒያ የሳተላይት የቴሌኮም ኩባንያ በኢትዮጵያ የቴሌኮም ገበያ ለመሠማራት አቅጃለሁ በማለት መናገሩን እፍሪካ ሪፖርት መጽሄት አስነብቧል። "አቫንቲ" ኢትዮጵያ ውስጥ የቴሌኮም አገልግሎት ፍቃድ እንዲሰጠው ለአገሪቱ መንግሥት ጥያቄ ማቅረቡን የገለጠው ዘገባው፣ የኢንቨስትመንት አጋርነት ለመፍጠር ከኢትዮ ቴሌኮምና ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኩባንያዎች ጋር ንግግር መጀመሩን የኩባንያው ሥራ አስኪያጅ እንደነገሩት ጠቅሷል። "አቫንቲ" በኢትዮጵያ ውስጥ መሠማራት የፈለገው፣ የአገሪቱን የኢንተርኔት ሽፋን በማስፋፋት መስክ እንደኾነ ዘገባው ገልጧል።

3፤ የኢትዮጵያ ብዙኀን መገናኛ ባለሥልጣን ለኢሳት ቴሌቪዥን "የመጨረሻ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ" መስጠቱን ፋና ብሮድካስት ዘግቧል። ባለሥልጣኑ ማስጠንቀቂያውን የሰጠው፣ ኢሳት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ "ሚዛናዊነት የጎደላቸው፣ በተጨባጭ መረጃ ያልተደገፉ፣ የሕዝቦችን መተማመንና አንድነት ሊሸረሽሩ የሚችሉ" ዘገባዎችን በተደጋጋሚ አቅርቧል በማለት መኾኑን ዘገባው አመልክቷል። ባለሥልጣኑ፣ ኢሳት መጋቢት 6 ቀን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ወደ ዋና ከተማዋ በብዛት ስለሚገቡ ሰዎች ያደረጉት ንግግር "ሕዝብን ከሕዝብ የሚያጋጭና የሰዎችን የመንቀሳቀስ መብት የሚጥስ መኾኑን የፖለቲካ ፓርቲዎች አስታወቁ" የሚል ዜና መስራቱን ለአብነት መጥቀሱን ዘገባው አብራርቷል።

4፤ የግብጽ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ኢትዮጵያ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ውዝግብ ግድቡን ውሃ ለመሙላት "ለጊዜ መግዣነት እየተጠቀመችበት" ትገኛለች በማለት መክሰሷን የግብጹ አሕራም ዘግቧል። ሚንስቴሩ፣ ትናንት በሰጠው መግለጫ፣ ግብጽ የግድቡን ውዝግብ ፖለቲካዊ አድረገዋለች በማለት ኢትዮጵያ የምታሰማውን ወቀሳም ነቅፏል። ኢትዮጵያ ግድቡን በተናጥል መሙላቷን አቁማ፣ በቅድሚያ በግድቡ አስተዳደርና ውሃ አሞላል ዙሪያ አስገዳጅ የሦስትዮሽ ስምምነት ይፈረም የሚለውን የሱዳንና ግብጽ አቋም ኢትዮጵያ እስካሁን አልተቀበለችውም። የኢትዮጵያ መንግሥት የግድቡ አጠቃላይ ግንባታ 90 በመቶ ላይ መድረሱን በቅርቡ የገለጠ ሲሆን፣ በተያዘው ዓመት ክረምት ለአራተኛ ጊዜ የግድቡን ውሃ ሙሌት እንደሚከናወን ይጠበቃል።

5፤ ጋና "አር21" የተሰኘውን አዲስ የወባ በሽታ መከላከያ ክትባት ጥቅም ላይ እንዲውል በማጽደቅ የመጀመሪያዋ አገር መኾኗን ዓለማቀፍ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ከ30 ዓመታት እልህ አስጨራሽ ምርምር በኋላ ያገኘው ይኼው ክትባት፣ በወባ በሽታ ለመሞት ከፍተኛ ተጋላጭነት ያላቸውን ከ5 ወር እስከ 3 ዓመት የሚኾኑ ሕጽናትን 77 በመቶ ከበሽታው የመከላከል አቅም እንዳለው ቡርኪናፋሶ ላይ በተደረጉ ሙከራዎች መረጋገጡን ዘገባዎቹ ጠቅሷል። ጋና ክትባቱን ጥቅም ላይ ለማዋል የወሰነችው፣ የዓለም ጤና ድርጅት ክትባቱ ገና ሳያጸድቀው ነው። ድርጅቱ የብሪታኒያ የመድኃኒት ኩባንያ ያመረተው "ጂኤስኬ" የተሰኘ ሌላ የወባ ክትባት ጥቅም ላይ እንዲውል ባለፈው ዓመትያጸደቀ ሲሆን፣ የክትባቱ የመከላከል አቅም ግን 60 በመቶ ብቻ ነው።

6፤ የሱዳን ጦር ሠራዊትና ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት አዲስ ፍጥጫ ውስጥ መግባታቸውን የውጭ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ፍጥጫው የተከሰተው፣ ጀኔራል ሞሐመድ ደጋሎ የሚመሩት ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት በካርቱም ሰሜናዊ አካባቢዎችና ግዛቶች በድንገት መሠማራቱን ተከትሎ ነው። የሱዳን ጦር ሠራዊት፣ የፈጥኖ ደራሽ ሠራዊቱ አዲስ ሥምሪት ከእውቅናውና ከፈጥኖ ደራሹ ሠራዊት የድንበር ጠባቂነት ሃላፊነት ውጭ መኾኑን ገልጦ፣ ድርጊቱ በኹለቱ ሠራዊቶች መካከል ግጭት ሊቀሰቅስ ይችላል ሲል ማስጠንቀቁን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ይህንኑ ተከትሎ፣ ብሄራዊው ጦር ሠራዊት በካርቱም ዙሪያ ወታደሮች ማስፈር መጀመሩ ተሰምቷል። ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊቱ ሲቪል የሽግግር መንግሥት ከተመሠረተ በኋላ ከአገሪቱ ጦር ሠራዊት ጋር በሚቀላቀልበት ጊዜ ላይ እስካሁን ስምምነት ላይ አልተደረሰም።

7፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ0117 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ0919 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 64 ብር ከ1360 ሳንቲም እና መሸጫው 65 ብር ከ4187 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ58 ብር ከ9106 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ60 ብር ከ0888 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
254 views19:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 08:15:07 ሐሙስ ማለዳ ሚያዝያ 5/2015 ዓ.ም የEMS Mereja ዐበይት ዜናዎች

1፤ ኢሰመኮ በአማራ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች ጸጥታ ኃይሎች በወሰዱት ርምጃና ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ጥቃት የረድኤት ድርጅት ሠራተኞችን ጨምሮ ሲቪል ሰዎች ተገድለዋል ሲል ትናንት ምሽት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። በክልሉ የተፈጠረው ኹኔታ መፍትሄ ካላገኘ፣ "ለከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ስጋት" መኾኑን የጠቀሰው ኢሰመኮ፣ ሁሉም አካላት ችግሩን "በምክክርና መግባባት" እንዲፈቱትና መንግሥትም የፖሊሲ ውሳኔውን ለባለድርሻዎች እንዲያስረዳ ጠይቋል። ኢሰመኮ፣ ጸጥታ ኃይሎች "ያልተመጣጠነና ሕይወት የሚያጠፋ ኃይል ከመጠቀም እንዲቆጠቡ" እና መንግሥትም ስለደረሰው ጉዳት ምርመራ አድርጎ ተጠያቂነትን እንዲያረጋግጥ ጥሪ አድርጓል።

2፤ የሱማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፋ ኡመር የክልሉ ልዩ ኃይል አባላት ከፌደራልና ክልል ጸጥታ ኃይሎች ጋር በሚዋሃዱበት ሁኔታ ዙሪያ ትናንት ከክልሉ ልዩ ኃይል ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ጋር መወያየታቸውን የክልሉ ኮምንኬሽን ቢሮ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል። ቢሮው፣ ሙስጠፋና የክልሉ ጸጥታ ኃላፊዎች በመንግሥት ውሳኔ ዙሪያ ለልዩ ኃይሉ አመራሮች ማብራሪያ እንደሰጡና በጉዳዩ ላይ መግባባት ላይ እንደተደረሰ ጨምሮ ገልጧል።

3፤ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በአማራ ክልል ማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምሥራቅ በለሳ ወረዳ የአምቡላንስ ሹፌርና አዋላጅ ነርስ በኾኑ ኹለት ሠራተኞቹ ላይ ማንነታቸው ያልታወቀ ታጣቂዎች ሚያዝያ 1 ቀን ጥቃት እንዳደረሱ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል። ኹለቱ ሠራተኞች አይባሽካ ቀበሌ ውስጥ ጥቃቱ የተፈጸመባቸው በምጥ የተያዘችን አንዲት እናት ጤና ጣቢያ ለማድረስ ሲጓዙ መኾኑና የጠቀሰው ማኅበሩ፣ ሠራተኞቹ ሕክምና ላይ መኾናቸውን ገልጧል። ማኅበሩ ጥቃቱን አውግዞ፣ ታጣቂ ኃይሎች ከመሰል ጥቃት እንዲቆጠቡ ተማጽኗል።

4፤ የዓለም ምግብ ፕሮግራም በአማራ ክልል ለዕርዳታ ፈላጊዎች የምግብ ዕርዳታ ሥርጭት ማቆሙን መግለጡን ሮይተርስ ዘግቧል። ድርጅቱ በክልሉ የዕርዳታ ምግብ ሥርጭት ለማቆም የተገደድኩት፣ በክልሉ ባለው የጸጥታ ኹኔታ ሳቢያ ነው ማለቱን ዘገባው ጠቅሷል። ድርጅቱ ይህንኑ ውሳኔውን የገለጸው፣ የካቶሊክ ተራድዖ ድርጅት ኹለት ሠራተኞቹ በሰሜን ወሎ ዞን ቆቦ ከተማ አካባቢ በተከሰተ ግጭት መገደላቸውን መግለጡን ተከትሎ ነው።

5፤ "አራት ኪሎ ሜዲያ" የተሰኘው የዩትዩብ ጣቢያ ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው ባሕርዳር ውስጥ ትናንት በቁጥጥር ስር መዋሉን ጣቢያው በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል። ዳዊትን ይዘው የወሰዱት የመከላከያ ሠራዊት አባላት መኾናቸውን ጣቢያው ገልጧል። ዳዊት ቀደም ሲል "የአል ዓይን ኒውስ" ጣቢያ ጋዜጠኛ የነበረ ሲሆን፣ ባኹኑ ወቅት ደሞ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ባለሙያዎች ማኅበር የሥራ አመራር ቦርድ አባል ጭምር እንደኾነ ተገልጣል።

6፤ በቱኒዝያ ጥቁር አፍሪካዊያን ፍልሰተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች የደኅንነት ስጋት እንደተጋረጠባቸው በመግለጽ በተመድ የስደተኞች ኮሚሽን መስሪያ ቤት ያደረጉትን ሰልፍ ፖሊስ በአስለቃሽ ጭስ በትኖ 80 ሰልፈኞችን ማሰሩን የፈረንሳዩ ዜና ወኪል ዘግቧል። ሰልፈኞቹና ጥገኝነት ጠያቂዎቹ ኮሚሽኑ ከአገሪቱ ባስቸኳይ እንዲያስወጣቸው መጠየቃቸውን ዘገባው ጠቅሷል። አፍሪካዊያን ፍልሰተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች የደኅንነት ስጋታቸው የተባባሰው፣ የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ካይስ ሳዒድ ጥቁር አፍሪካዊያን ፍልሰተኞች በብዛት መግባታቸው የቱኒዚያን ዓረባዊ ማንነት ለማጥፋት ያለመ ሴራ እንደኾነ በመግለጽ ፖሊስ "ሕገወጥ" ፍልሰተኞችን እንዲያባርር ባለፈው የካቲት ትዕዛዝ ከሰጡ በኋላ ነበር። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
285 views05:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 23:36:49

292 views20:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 21:41:30


269 views18:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 19:34:20 ረቡዕ ምሽት! ሚያዝያ 4/2015 ዓ.ም የEMS Mereja ዐበይት ዜናዎች

1፤ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮንዶሚኒየዬም ቤቶች ዕጣ አወጣጥ ላይ ተፈጸመ በተባለው የማጭበርበር ወንጀል ከተከሰሱ 11 ግለሰቦች መካከል 5ቱን በነጻ እንዳሰናበተ የአገር ውስጥ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ዛሬ በነጻ ከተሰናበቱት መካከል፣ የከተማዋ አስተዳደር የቴክኒክና ሙያ ሥልጠናና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቀድሞ ሃላፊ ሙሉቀን ሃብቱ እንደሚገኙበት ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ቀሪዎቹ አምስት ተከሳሾች በገንዘብ ዋስትና ከእስር ተለቀው ጉዳያቸውን በውጭ እንዲከታተሉ የተወሰነላቸው ሲሆን፣ በቀጣዩ ግንቦት 2 ቀን የመከላከያ ምስክሮቻቸውን እንዲያሰሙ እንደተቀጠሩ ተገልጧል። አንድ ተከሳሽ ግን በሌለበት የጥፋተኛነት ውሳኔ ተወስኖበታል ተብሏል።

2፤ በደቡብ ክልል ቡታጅራ ከተማ የክልሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከጉራጌ ዞን የክልልነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ ከታሠሩ ግለሰቦች መካከል ለ17ቱ የዋስትና መብት እንደፈቀደላቸው ዶይቸቨለ ዘግቧል። ፍርድ ቤቱ የዋስትና መብታቸውን ከጠበቀላቸው ታሳሪዎች መካከል፣ የጉራጌ ዞን የብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ አለማየሁ ገብረ መስቀል እና የዞኑ የውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ሃላፊ ፍስሃ ዳምጠው እንደሚገኙበት ዘገባው ጠቅሷል።

3፤ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ መለስ ዓለም የጣሊያን ጠቅላይ ሚንስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በሳምንቱ መገባደጃ ላይ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ዛሬ በሰጡት መግለጫ መናገራቸውን መግለጫውን የተከታተሉ የአገር ውስጥ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ጠቅላይ ሚንስትር ሜሎኒ በኢትዮጵያ ቆይታቸው፣ ከኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር በሁለትዮሽና ቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚነጋገሩ መለስ መግለጣቸውን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በጦርነት የወደሙ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባትና በሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት ጣሊያን ድጋፍ የማድረግ ፍላጎት እንዳላት መለስ ጠቁመዋል ተብሏል። ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ከጥቂት ሳምንታት በፊት በጣሊያን ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወሳል።

4፤ የተመድ ስደተኞች ኮሚሽን በኢትዮጵያው ሱማሌ ክልል ዶሎ ዞን የተጠለሉ ከሱማሌላንዱ የላስ አኖድ ከተማ የተሰደዱ ስደተኞችን ወደ አዲስ መጠለያ ጣቢያዎች ማዛወር መጀመሩን አስታውቋል። ኮሚሽኑ ሰሞኑን በሦስት ቀናት ውስጥ ለጉዳት ተጋላጭ የኾኑ 1 ሺህ 36 የሱማሌላንድ ስደተኞችን ወደ አዲሶቹ መጠለያዎች ማዛወሩን ገልጧል። ከ3 ሺህ በላይ ሕጻናትና ታዳጊዎች በግጭቱ ከወላጆቻቸው እንደተለያዩ የገለጠው ኮሚሽኑ፣ በጠቅላላው በዶሎ ዞን የተጠለሉ 91 ሺህ ስደተኞችን መዝግቤያለሁ ብሏል። ስደተኞቹ እስካሁን በቂ ሰብዓዊ ዕርዳታ እንዳልቀረበላቸው ኮሚሽኑ ጨምሮ አመልክቷል።

5፤ ኬንያ በገጠማት ከፍተኛ የገንዘብ እጥረት ሳቢያ ለመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ በወቅቱ ለመክፈል በመቸገሯ የመንግሥት ሠራተኞች ሰልፍ እንደሚወጡ ማስጠንቀቃቸውን ደይሊ ኔሽን ዘግቧል። የመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ክፍያ መዘግየት እንደሚያጋጥማቸው ተገንዝበው ከወዲሁ ዝግጅት እንዲያደርጉ ባለሥልጣናት ማሳሰባቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ መንግሥታቸው ለሠራተኞቹ ደመወዝ ለመክፈል ሲል ከውጭ ምንጮች የመበደር ፍላጎት እንደሌለው መናገራቸውን ዜና ምንጩ ጨምሮ አመልክቷል። በገንዘብ እጥረቱ ሳቢያ፣ ማዕከላዊው መንግሥት ራሳቸውን ለሚያስተዳድሩ አውራጃዎች ድጎማና የአገሪቱን የውጭ ዕዳ ክፍያ ለጊዜው መክፈል ማቆሙ ተገልጧል።

6፤ የጣሊያን መንግሥት የሜድትራኒያን ባሕርን አቋርጠው ወደ አገሪቱ የሚገቡ በርካታ "ሕገወጥ" ፍልሰተኞችንና ጥገኝነት ጠያቂዎችን ለመቆጣጠር ያለመ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ትናንት ማውጣቱን የውጭ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ጠቅላይ ሚንስትር ጆርጂያ ሜሎኒ የሚመሩት የቀኝ አክራሪ ፓርቲዎች ጥምር መንግሥት ያወጣው ይኼው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ፣ ለስድስት ወራት የሚቆይ እንደኾነ ዘገባዎቹ አመልክተዋል። ጣሊያን ለ"ሕገወጥ" አፍሪካዊያን ፍልሰተኞች ላምባዱሳ ወደብ ላይ ጊዜያዊ መቆያ ማዕከል አላት። በተያያዘ፣ የተመድ ፍልሰተኞች ድርጅት ከጥር ወር ወዲህ ብቻ ከሰሜን እፍሪካ ወደ ጣሊያን በጀልባ ለመግባት የሞከሩ 400 ፍልሰተኞች ሜድትራኒያን ባሕር ላይ ሰጥመው እንደሞቱ ዛሬ አስታውቋል።

7፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ0117 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ0919 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 64 ብር ከ1360 ሳንቲም እና መሸጫው 65 ብር ከ4187 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ58 ብር ከ9106 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ60 ብር ከ0888 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
288 views16:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 14:06:14 በግድቡ አጠገብ የተለያዩ ቡድኖች ሕገወጥ ሆቴል ግንባታና ሰፈራ ጀምረዋል ተባለ

በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የተለያዩ ግለሰቦችና ቡድኖች ሕገወጥ ሰፈራዎችን እና ግንባታቸውን መጀመራቸው ተገለጸ።

ግድቡ ሙሉ በሙሉ ከመጠናቀቁ በፊት ከወዲሁ የተለያዩ ግለሰቦች እና ቡድኖች በዙሪያው በሕገወጥ መንገድ ይዞታዎችን በመያዝ ሆቴሎችን መገንባት፣ ዓሳ ማስገር፣ የጀልባ አገልግሎት መስጠት እንዲሁም በሐይቁ ዙሪያ ሕገወጥ ሰፈራዎች መስፋፋት መጀመራቸውን ታውቋል።

ይህን ያለው የቦሮ ዴሞክራሲ ፓርቲ ዛሬ ባወጣው መግለጫ፤ እንደዚህ ዓይነት ግልጽነት የጎደላቸው ሕገወጥ አካሄዶች ነገ ሌላ ስጋት እንዳይሆኑ በጥንቃቄ መመራት አለባቸው ሲል አሳስቧል።

ስለሆነም ከግድቡ ዙሪያ ተያያዥ በሆኑ የልማት ፕሮጀክቶች አወሳሰንና አፈጻጸም በተመለከተ የክልሉ እና የፌዴራል መንግሥት ግልጽ አሰራርና ፖሊሲ ኖሯቸው በግልጽነት እንዲሠሩ ፓርቲው ጠይቋል።

የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የታላቁ ሕዳሴ ግድብ መገኛ እንደመሆኑ የክልሉ ሕዝብ ከፕሮጀክቱ ትሩፋቶች ተጠቃሚ መሆን እንደሚገባው በመግለጽም፤ የክልሉ ሕዝብ ፍትሐዊ ተጠቃሚ የሚሆንበት ግልፅ አሰራርና የፖሊሲ ማዕቀፍ ሊዘጋጅ ይገባል ብሏል።

በሌላ በኩል ፓርቲው፤ ‹‹የክልሉ ሕዝብ በነበረው የሰላም እጦት የተነሳ በ6ኛው አገራዊ ምርጫ የመሳተፍና የሚፈልገውን መርጦ በመረጠው መንግሥት የመተዳደር እድል አላገኘም።›› ብሏል። አሁን ላይ በክልሉ የተሻለ የሰላም ሁኔታ በመኖሩ የተያዘው ዓመት ከመገባደዱ በፊት ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በክልሉ ምርጫ እንዲያካሂድ ጥሪ አቅርቧል።

በክልሉ በ71 የክልል ምክር ቤት እና በስድስት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ አለመካሄዱንም ጠቅሶ፤ በዚህም ምክንያት በሕዝብ የተመረጠ ክልላዊ መንግሥት አልተደራጀም ብሏል።

ፓርቲው እንዲሁም የክልሉን ልዩ ኃይል የማደራጀት ውሳኔ ላይ ሐሳብ ሰጥቷል። በዚህም ‹‹የክልላችን ልዩ ኃይል የተቋቋመው በክልሉ ካብኔ በጸደቀ ደንብ በመሆኑ የክልሉ መንግሥት በቅድሚያ የማቋቋሚያ ደንቡን ሕጋዊ አካሄድን ተከትሎ መሻር ይኖርበታል። በአፈጻጸሙ ላይም በክልሎች መካከል የመርሃ ግብር ልዩነት ሊኖር አይገባም›› ሲል ገልጿል።
#ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
281 views11:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 12:47:41 በመተሐራ የቆቦ ቀበሌ ሊቀመንበር ከአንድ የቤተሰባቸው አባል ጋር ተገደሉ

በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ፈንታሌ ወረዳ የቆቦ ቀበሌ ሊቀመንበር እና የባለቤታቸው እናት ሰኞ ሚያዚያ 2/2015 ምሽት ሦስት ሰዓት ገደማ መገደላቸውን መተሐራ የሚገኙ የአዲስ ማለዳ ምንጮች ተናግረዋል።

ግድያው የተፈጸመው ራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ብሎ በሚጠራውና በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሽብርተኛ ተብሎ በተፈረጀው በሸኔ ታጣቂዎች እንደሆነ የተናገሩት ምንጮች፤ ምሽቱን በከተማው ረዘም ያለ የተኩስ ልውውጥ ይሰማ እንደነበርም ገልጸዋል።

ሊቀመንበሩ ከመተሐራ ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ የምትገኘዋ ቆቦ ቀበሌን የሚያስተዳድሩ ሲሆን፤ ባለባቸው የደኅንነት ስጋት ምክንያት ከቀበሌዋ ውጭ መተሐራ ከተማ ውስጥ ይኖሩ እንደነበር ነው የተጠቀሰው።

በሊቀመንበሩ ላይ ተኩስ የተከፈተው በረንዳ ላይ ሆነው ከቤተሰቦቻቸው ላይ እራት በመመገብ ላይ እንደነበሩ ሲሆን፤ ጥቃቱ ከደረሰባቸው በኋላ ወደ ሕክምና ሳይደርሱ ሕይወታቸው ማለፉ ተነግሯል።

አሁንም በቆቦ ቀበሌ በስፋት ይንቀሳቀሳሉ የተባሉት የሸኔ ታጣቂዎች ሰኞ ዕለት በአካባቢው አሰሳ በማድረግ ላይ በነበሩ የፌዴራል ፖሊስ አባላት ላይም ጥቃት ማድረሳቸው የተገለጸ ሲሆን፤ በዚህም ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የፌዴራል ፖሊስ አባላት መገደላቸው ተሰምቷል።

EMS Mereja ከአካባቢው የመንግሥት አስተዳደር ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ያደረገችው ጥረት አልተሳካም።
#ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
261 views09:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 12:29:58 "ግብፅ የአባይን ውሃ እና ግድቡን የፖለቲካ መልክ ለማሰጠት እየሄደች ያለችበት መንገድ የትኛውን አካል የሚጠቅም አይደለም" ፦ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ

አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማህመት ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል በውይይታቸውም ስለ ዓባይ ግድብ የተለያዩ ነጥቦችን አንስተዋል።

አምባሳደር ምስጋኑ አረጋ ምን አሉ?

አምባሳደሩ ግብፅ የአባይን ውሃ እና ግድቡን የፖለቲካ መልክ ለማሰጠት እየሄደች ያለችበት መንገድ የትኛውንም አካል የሚጠቅም አይደለም በማለት አጽንኦት ሰጥተዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው የታላቁ ህዳሴ ግድብን በሚመለከት የኢትዮጵያን አቋም ለሊቀመንበሩ ሲያስረዱ÷ "የሶስትዮሽ ድርድሩ በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስራ መከናወኑ መቀጠል እንዳለበት ኢትዮጵያ የፀና አቋም አላት" ሲሉ ተደምጠዋል።

አምባሳደሩ አክለው ይህ እንቅስቃሴ ተገቶ መሬት ላይ ያለውን እውነት መነሻ ያደረገ ወይይትና ድርድር እንዲቀጥል ህብረቱ በጎ ሚናውን ይወጣል በማለት ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

የህብረቱ ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማህመት ምን አሉ?

ሊቀመንበሩ አባይ አፍሪካዊ ወንዝ በመሆኑ አጀንዳው አህጉራዊ መሆን እንዳለበት ህብረቱ እንደሚያምን ገልፀዋል።

ድርድሩም በአፍሪካ ማዕቀፍ እልባት እንዲያገኝ ህብረቱ የማያይቋረጥ ድጋፍ እንደሚያደርግ አንስተዋል፡፡

ህብረቱ በሚያከናውነው ተቋማዊ ሪፎርምም የሰራተኞችን መብትና ጥቅም ባከበረ መልኩ  እንደሆነ ማረጋገጣቸውን ጨምሮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ቀጥሎ እየተካሄደ ሲሆን የውሃ ሙሌት በቀጣዩ ክረምት የሚይዘው የውሃ መጠን ከ22 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ወደ 42 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ከፍ እንደሚልና ቀሪ ሥራዎችን ለማጠናቀቅ ከ50 ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ያስፈልጋል ተብሏል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
260 views09:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ