Get Mystery Box with random crypto!

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ) Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ)
የሰርጥ አድራሻ: @zemedkun_zemede
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.26K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 14

2023-03-30 07:35:07 አቶ አዲሱ አረጋ አለቃዬ ተነኩ፥ ስልጣን ልቀቁ ተባሉብን አይነት ለስለስ ያለች ለቅሶ አድርሰውናል። 'የማይመቱት ልጅ ሲቆጡት ያለቅሳል' ን መተረት አልፈልግም። አቶ አዲሱ ሞራል፥ ህሊና፥ ይሉኝታ አፈር ከድሜ በጋጡባት ሀገር ይህን ማለታቸው ብዙም አያስደንቅም። ስለገደልነው፥ ስለበደልነው፥ ስላበላሸነው ሁሉ ለምን አልተሸለምን፥ ስለምንስ አልተመሰገንም አለማለታቸው በራሱ አንድ ነገር ነው። ከአንድ ወንዝ የሚቀዳ፡ እንደሳሙና ፋብሪካ አንድ ዓይነት አስተሳሰብ ከሚያመነጭ ቡድን የተለየ ሀሳብ፥ ስሜት የሚሰጥ ሙግት ለማግኘት እጅግ አስቸጋሪ ነው። አቶ አዲሱ ምንም ሊነግሩን አልመጡም። ሊነግሩንም የሚችሉት ሀሳብ የላቸውም። ለአለቃቸው ታማኝነታቸውን፡ ለተወላገደው አካሄዳቸው ጭብጨባቸውን ሊያሰሙን እንጂ ከጠ/ሚሩ የተለየ ምንም አልነገሩንም። ጆሮአችን በከንቱ ደነቆረ።

በእኔ በግል እይታ ጠ/ሚሩ ከህወሀት ጋር በነበሩት ሶስቱ ጦርነቶች በሰጡት አመራር ብቻ ከስልጣን መልቀቅ ባለፈ በህግ ሊጠይቁ በተገባቸው ነበር። ሌላ ሌላውን እንተወው። በመላ ሀገሪቱ በበረከተው ዕልቂት፡ በነገሰው ሞት፡ ምድሩን በሞላው መፈናቀል ይቅርታ ብናደርግላቸው እንኳን መንገድ ላይ እያዘረከረኩ ወደኋላ በመለሷቸውና አሁንም ድረስ መቋጪያ ባለበጁላቸው ጦርነቶች ብቻ በፍርድ መጠየቅ የሚገባቸው መሪ ናቸው። ይህ ሁሉ፥ በመንግስታዊ እንዝህላልነት በፓርቲያቸውና በግልም እሳቸው በነበራቸው ድርሻ የተከሰተ ግዙፍ ሀገራዊ ኪሳራና ሰብዓዊ ዕልቂት ነው። ጠሚ/ሩ ገና ከመነሻው እኔ አሻግራችኋለሁ ብለው ሃላፊነቱን በግል ወስደዋል። በቅርቡ በቤተክርስቲያኒቱ ጉዳይ ካቢኔአቸውን በሙሉ ''አይመለከታችሁም'' በሚል ቁጣ አዘል ማስጠንቀቂያ ተጠያቂነቱን ራሳቸው ላይ አሸክመዋል።

ኦቦ አዲሱ አረጋ የብሽሽቅ ፖለቲካ ሱሳቸው እንደሆነ ባውቅም በልካቸው ሊነገራቸው እንደሚገባ ስለማምን ነው ለአጭር መልዕክታቸው አጭር አስተያየት መስጠት የፈለኩት። በሀሳብ እንዳልሞግታቸው ሀሳብ ይዘው አልመጡም። በአመክኒዮ እንዳልከራከራቸው ደረቅ የካድሬ ትርክት እንጂ ሌላ መልክ ያለው ለሙግት የሚጋብዝ ነገር አልጻፉም። ዝም ብሎ ግትትት ያለ የ'ጌታዬ ለምን ተነካ' እሮሮ ነው ያቀለጡት። እናም በአጭሩ መልስ ለመስጠት ያህል ጠ/ሚሩ ስልጣን ልቀቁ መባላቸው ሊያስገርምዎት አይገባም። ከትንሹ እግዚያብሄር ከሆነው ህሊና ስለተጣሉ እንጂ የተጠየቀው በጣም ጥቂቱ፡ ከውቅያኖስ በጭልፋ እንደመጨለፍ ያህል የሚታይ ነው። መደመር በምትሉት ባዶ ፍልስፍና ሰክራችሁ ሀገር እያሳበዳችሁ በመሆናችሁ አሁን ላይ ምንም ላይሰማችሁ ይችላል። የስልጣን ስካር አይጣል ነው። ልቦና ያውራል። አይንን ይጋርዳል። ልክ እንደአረቄ ስካር ነው። ሲለቅና ሲበርድ ግን ያን ጊዜ ነው እናንተን ማየት።

ለማንኛውም አይደንግጡ። ኮንትራት ምናምን ያሉት ተራ መከራከሪያ ነው። ስልጣንኑን የሰጣችሁን ህዝብ መከራ በአናት አናቱ እየጋታችሁት ጊዜአችንን እስከምንጨርስ እየሞትክ ጠብቀን የሚሉት ፈሊጥ ብልጽግና መንደር ብቻ የሚሰራ ሎጂክ ሊሆን ይችላል። በነገራችን ላይ ከእርስዎ ጋር የሚያገናኘኝ አንድ ጉዳይ ከሰሞኑ ይኖረኛል። ለስልጣን እንዲህ አውሬ እንድትሆኑ ያደረጋችሁ የዘረፋ ጉዳይን በተመለከተ መረጃዎችና ማስረጃዎች እየመጡ ናቸው። በሱ ቋንቋ ብንነጋገር የሚሻል ይመስለኛል። ህዝብን ዘረኝነት እየጠቀጠቃችሁበት፡ በቤተሰብ፡ በአምቻና ጋብቻ ተጣምዳችህ ሀገርን በቁም እየዘረፋችሁ ስለመሆናችሁ ህዝብ እንዲውቀው የምናደርግ ይሆናልና ያን ጊዜ ስልጣን መልቀቅ ምን እንደሚመስል ይነግሩናል። ገለቶማ ጃል! #ሼር ብቻ Godhaa
#ሼር በማድረግ ተባበሩኝ


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja

መሳይ መኮንን
295 views04:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-30 07:27:16 ሐሙስ ማለዳ! መጋቢት 21/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ የአውሮፓ ኅብረት ኮሚሽን ለኢትዮጵያ ለሰብዓዊ ዕርዳታ የሚውል የ60 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዩሮ ለመስጠት መወሰኑን ትናንት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ኅብረቱ ለኢትዮጵያ የገንዘብ ዕርዳታ ለመስጠት የወሰነው፣ የሰሜኑ ጦርነት፣ ግጭቶች እና ድርቅ በአገሪቱ ላይ ከፍተኛ የሰብዓዊ ቀውስ እንዳስከተሉ በመጥቀስ ነው። ኅብረቱ ኢትዮጵያን ጨምሮ በከፍተኛ ሰብዓዊ ቀውስ ለተመቱ ሰባት የአፍሪካ ቀንድ አገራት ለመስጠት የወሰነው፣ 331 ሚሊዮን ዩሮ እንደሆነ ገልጧል። ኅብረቱ ለደቡብ ሱዳን ከፍተኛውን 82 ሚሊዮን ዶላር መድቤያለሁ ብሏል።

2፤ በሱማሌ ክልል ሲቲ ዞን የመከላከያ ሠራዊት አባላት ተኮሱት በተባለ ጥይት ሦስት ሰዎች መገደላቸውንና ስድስቱ መቁሰላቸውን ሰምቻለሁ ሲል አዲስ ስታንዳርድ ዘግቧል። ሰዎቹ የተገደሉት፣ ሰኞ'ለት የአይሻ ወረዳ ነዋሪዎች መከላከያ ሠራዊት በሱማሌ ክልልና አፋር ክልል የድንበር ውዝግብ የአፋር ክልል ልዩ ኃይልን ያደግፋል በማለት ተቃውሟቸውን ለማሰማት አደባባይ በወጡበት ወቅት እንደኾነ ዘገባው ጠቅሷል። የመከላከያ ሠራዊት አባላት ከመድረሳቸው በፊት፣ ተቃዋሚዎች የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ሐዲድ መስመርን ዘግተው እንደነበርና መስመሩን ለማስከፈት በተፈጠረ ውዝግብ ሰዎቹ እንደተገደሉ ምንጮች ነግረውኛል ሲል ዜና ምንጩ አትቷል።

3፤ 33 ኢትዮጵያዊያን "ሕገወጥ" ፍልሰተኞች ከሱማሊያዋ ፑንትላንድ ራስ ገዝ ወደ አገራቸው መመለሳቸውን ፋና ብሮድካስት ዘግቧል። ከተመላሾቹ መካከል፣ 12ቱ ሴቶች ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹ ወንዶች እንዲሁም አራቱ ሕጻናት እንደሆኑ ዘገባው ጠቅሷል። ፍልሰተኞቹ የተመለሱት፣ ፑንትላንድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ ከዓለማቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት ጋር በመተባበር ነው። ተመላሾቹ በሕገወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች አማካኝነት ወደ የመን ለመሻገር ፑንትላንድ የገቡ መሆኑ ተገልጧል።

4፤ የተመድ አባል አገራት ዓለማቀፉ የዳኝነት ፍርድ ቤት የበለጸጉ አገራት ለአየር ንብረት ለውጥ ባለባቸው ሃላፊነት ላይ የሕግ አስተያየት እንዲሰጥ በአብላጫ ድምጽ ወስነዋል። ፍርድ ቤቱ የሕግ ውሳኔ እንዲሰጥ የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ 130 አገራት ደግፈውታል። አሜሪካና ቻይና የውሳኔ ሃሳቡን በግልጽ አልተቃወሙም ወይም አልደገፉም። የፍርድ ቤቱ የሕግ አስተያየት አስገዳጅ ባይሆንም፣ ወደፊት በሚደረጉ የአየር ንብረት ለውጥ ድርድሮችና ክሶች ላክ ግን ተጽዕኖ ይኖረዋል ተብሏል። ፍርድ ቤቱ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የሕግ አስተያየት የመስጠት ሥልጣን ሲያገኝ፣ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።

5፤ አሜሪካ የተቃውሞ ሁከት ወደቀጠለበት ኬንያ ሴናተር ክሪስ ኩንስን ልካለች። ሴናተር ኩንስ፣ ክኬንያ ባለሥልጣናት ጋር በሁለትዮሽ የጸጥታ እና ንግድ ግንኙነቶች ዙሪያ እንደሚነጋገሩ የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ኩንስ፣ በኬንያ ሰሞኑን ከተፈጠረው ሁከት የተቀላቀለበት ጸረ-መንግሥት የተቃውሞ ሰልፍ ዙሪያ ጭምር ከአገሪቱ ባለሥልጣናት ጋር ይነጋገሩ እንደኾነ ወይም ተልዕኳቸው ከዚሁ ጋር የተገናኘ ይኹን አይኹን ለጊዜው አልተገለጸም። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የኬንያ ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ራይላ ኦዲንጋ የጠሩት ሦስተኛው አገር ዓቀፍ የተቃውሞ ሰልፍ ዛሬ ይካሄዳል። #ሼር በማድረግ ተባበሩኝ


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
271 views04:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-29 21:43:52
ጌታቸው ረዳ
የትግራይ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳና ከፍተኛ ባለስልጣናት አዲስአበባ ውስጥ እየተዟዟሩ የፌደራሉ መንግስት ተቋማትን እየጎበኙ ሲሆን በቀጣይ በትግራይና በፌደራሉ መንግስት ሆነ ከሌሎች ክልሎች ጋር የሚኖረውን ግንኙነት መስመር እያስያዙ ይገኛል። በነገራችን ላይ ጌታቸው ረዳ የሚጠበቀው በUN High Security Agents ጠባቂዎች እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
ሰሞኑን በአዳማ ከኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ጋር ተገናኝተዋል። #ሼር በማድረግ ተባበሩኝ


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
249 views18:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-29 20:37:36 ረቡዕ ምሽት! መጋቢት 20/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ከኢትዮጵያ መንግሥት የቀረበልኝ የሰላም ንግግር ጥሪ የለም በማለት አስተባብሏል። የኢትዮጵያ መንግሥት የሰላም ጥረት አደረኩ የሚለው፣ የቡድኑን አመራሮችና አባላት የትጥቅ ትግላቸውን ትተው ለመንግሥት እጃቸውን እንዲሰጡ በአካባቢ ሽማግሌዎች አማካኝነት ያደረገውን ያልተሳካ ሙከራ ነው በማለት ቡድኑ ገልጧል። ቡድኑ፣ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ትናንት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ ላይ፣ ግጭቱን ለመፍታት 10 ያህል ሙከራዎች ተደርገዋል በማለት የተናገሩት ንግግር ተጨባጭ ሁኔታውን በትክክል አይገልጽም ብሏል። ሆኖም ቡድኑ አሁንም በገለልተኛ ሦስተኛ አካል ለሚደረግ ድርድር ዝግጁ መሆኗን በድጋሚ ገልጧል።

2፤ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂዎች በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ 100 ያህል ሰዎችን አግተው እንደሚገኙ መስማቱን ጠቅሶ ሪፖርተር ዘግቧል። በአካባቢው የፌደራል ፖሊስ አባላት ሠፍረው እንደሚገኙ ነዋሪዎች መናገራቸውን የጠቀሰው ዘገባው፣ ሆኖም ፖሊሶች ታጋቾቹን ለማስለቀቅ የወሰዱት ርምጃ የለም ማለታቸውን ገልጧል። የወረዳው አስተዳዳሪ ሺበሺ አያሌው በበኩላቸው፣ ታጣቂዎቹ በተደጋጋሚ እገታ እንደሚፈጽሙ አምነው፣ ሆኖም የመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች በቡድኑ ታጣቂዎች ላይ ርምጃ እየወሰዱ መሆኑን መናገራቸውን ዜና ምንጩ አመልክቷል። አጋቾቹ ላንድ ታጋች እስከ 200 ሺህ ብር ድረስ ይጠይቃሉ ተብሏል።

3. የዋጋ ንረት የኢትዮጵያን የውጭ ንግድ እየተፈታተነው መሆኑን ዋዜማ ካገኘቻቸው መረጃዎች መረዳት ችላለች። በተለይ የስጋ የወጪ ንግድ በውጭ ምንዛሬ እጥረት ሳቢያ በተያዘው ዓመት በከፍተኛ ደረጃ ያሽቆለቆለ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ወደ ዱባይ የምትልከው የስጋ ምርት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኬንያዊያን ስጋ ላኪዎች እንደተበለጠ ምንጮች ተናግረዋል። ስጋ ላኪዎች በተለይ የፍየል ስጋ ከአገር ውስጥ ገበያ የሚገዙበት ዋጋ በከፍተኛ ደረጃ መወደዱ፣ ኪሳራ ላይ እንደጣላቸው ጨምረው ገልጸዋል። ባለፈው ዓመት በሰባት ወራት ውስጥ ለውጭ ገበያ የቀረበው 13 ሺህ 800 ቶን ስጋ ሲሆን፣ ዘንድሮ በተመሳሳይ ወራት የቀረበው ግን 9 ሺህ 600 ቶን ስጋ ብቻ እንደሆነ ተገልጧል።

4፤ የኡጋንዳው ፋይንቴክ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ከኢትዮጵያው አዋሽ ባንክ ጋር የሥራ ትብብር መፍጠሩን የኡጋንዳው ዘ ሞኒተር ጋዜጣ ዘግቧል። ኩባንያው ከባንኩ ጋር የፈጠረው የሥራ ትብብር ስምምነት፣ ባንኩ በንግድ፣ በዕርዳታ ሥርጭት እና በኢንሹራንስ ዘርፎች አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እንዲተገበ እንደሚያስችለው የኩባንያው ሃላፊዎች መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ፋይንቴክ ኩባንያ በኡጋንዳ በሞባይል የገንዘብ ብድር መስጠት አገልግሎት፣ በባንክ እና ኢንሹራንስ ዘርፎች ሰፊ ልምድ ያለው ነው።

5፤ በአሜሪካ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፍሎሪዳ ግዛት ተወካይ ማት ገዓዝ አሜሪካ ወታደሮቿን ከሱማሊያ እንድታስወጣ የሚጠይቅ ረቂቅ የውሳኔ ሃሳብ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል። የገዓዝ ረቂቅ የውሳኔ ሃሳብ፣ የአሜሪካ ወታደራዊ አመራሮች አሜሪካ ከምታሰለጥናቸው የሱማሊያ ወታደሮች መካከል ነገ የትኞቹ በመፈንቅለ መንግሥት እንደሚሳተፍ በማይገምቱበት ሁኔታ፣ የአሜሪካ ወታደሮች በሱማሊያ መገኘታቸው አሳማኝ አይደለም ይላል። ረቂቅ የውሳኔ ሃሳቡ፣ የፔንታጎን ባለሥልጣናት የአሜሪካ ወታደሮች ሱማሊያ ውስጥ መስፈራቸው የአሜሪካን ሕዝብ ምን ያህል እንደሚጠቅም ማብራራት አልቻሉም የሚል መከራከሪያም አቅርቧል። በምክር ቤቱ ሕግ መሠረት፣ በረቂቅ የውሳኔ ሃሳቡ ላይ በ18 ቀናት ውስጥ ውይይት ይደረግበታል። "ዳናብ" የተሰኘውን የሱማሊያ ልዩ ኮማንዶ ብርጌድ የሚያሰለጥኑት የአሜሪካ ወታደሮች ናቸው።

6፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 53 ብር ከ8887 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 54 ብር ከ9695 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 63 ብር ከ3673 ሳንቲም እና መሸጫው 64 ብር ከ6346 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ58 ብር ከ3453 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ59 ብር ከ5122 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩኝ


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
253 views17:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-29 07:37:42 ረቡዕ ማለዳ! መጋቢት 20/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባለፈው የአውሮፓዊያን ዓመት በዓለም ላይ ከተከሰቱት ግጭቶች ሁሉ እጅግ አውዳሚው የትግራዩ ጦርነት እንደነበር ትናንት ባወጣው ሪፖርቱ ገልጧል። ድርጅቱ፣ በኢትዮጵያው ጦርነት ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች የተፈጸሙት ከዓለማቀፉ ኅብረተሰብ ትኩረት ውጭ በኾነ ሁኔታ እንደኾነ በሪፖርቱ ጠቅሷል። ዓለማቀፍ ድርጅቶች፣ በኢትዮጵያ፣ የመን፣ በርማ እና አፍጋኒስታን ለነበሩ ግጭቶችና ሰብዓዊ ቀውሶች በቂ ምላሽ አልሰጡም በማለትም አምነስቲ ወቅሷል።

2፤ የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ፣ የሰላምና ጸጥታ ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ በትግራይ ወቅታዊ ፖለቲካዊ እና የጸጥታ ሁኔታዎች ዙሪያ ከኅብረቱ የዓለማቀፍ አጋሮች ቡድን ጋር መወያየታቸውን ትናንት ምሽት በትዊተር ገጻቸው ላይ ባሠፈሩት መልዕክት አስታውቀዋል። አምባሳደር ባንኮሌ፣ የኅብረቱ አጋሮች ቡድን ኅብረቱ-መር ለኾነው የኢትዮጵያ መንግሥት እና ሕወሃት ለደረሱበት የሰላም ስምምነት ተግባራዊነት ድጋፍ ማድረጋቸውን እንዲቀጥሉ መጠየቃቸውን ጨምረው ገልጸዋል።

3፤ ከትናንት ወዲያ በ99 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት የፒያኖና ቫዮሊን ሙዚቃ አቀናባሪ የእማሆይ ጽጌማርያም ገብሩ ሥርዓተ ቀብር በመጭው ዕሁድ እየሩሳሌም ውስጥ እንደሚፈጸም መስማቱን ጠቅሶ ቪኦኤ ዘግቧል። እማሆይ ጽጌማርያም ለረጅም ዓመታት የተጫወቱበት የግል ፒያኗቸው፣ ለቅዱስ ያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት እንዲሰጥላቸው እንደተናዘዙ ዘገባው ጠቅሷል። እማሆይ ጽጌማርያም በሕይወት ዘመናቸው ከ300 በላይ ረቂቅ ሙዚቃዎችን ማቀናበራቸው የሚነገርላቸው ሲሆን፣ ከወጣትነት ዘመናቸው ጀምሮ እስከ ሕልፈታቸው ድረስ የኖሩት በምንኩስና ሕይወት ነው።

4፤ ኢጋድ በአፍሪካ ቀንድ የተከሰተው ድርቅ አሰቃቂ ሰብዓዊ ቀውስ እንዳያስከትል ለመከላከል ዓለማቀፍ ለጋሾች እጃቸውን እንዲዘረጉ የድርጅቱ ዋና ጸሃፊ ወርቅነህ ገበየሁ ጥሪ ማድረጋቸውን ዘ ኢስት አፍሪካን አስነብቧል። በቀጠናው 47 ሚሊዮን ሕዝብ ለከፍተኛ የምግብ እጥረት መጋለጡን የጠቀሱት ወርቅነህ፣ 70 በመቶዎቹ ተጋላጮች በኢትዮጵያ፣ ኬንያና ሱማሊያ እንደሚገኙ መናገራቸው ተገልጧል። ወርቅነህ፣ በቅርቡ ቀናት በቀጠናው አንዳንድ አካባቢዎች የዘነበው ከፍተኛ ዝናብ፣ የዝናብ ወቅቱን ትክክለኛ ገጽታ ላያሳይ እንደሚችል መናገራቸውንም ዘገባው ጠቅሷል። በኢትዮጵያ ድርቁ መጠነ ሰፊ ጉዳት እንዳያደርስ በቀጣዮቹ አራት ወራት 710 ሚሊዮን ዶላር፣ በሱማሊያ 1.6 ቢሊዮን ዶላር እንዲሁም በኬንያ 378 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ ወርቅነህ አውስተዋል ተብሏል።

5፤ በአፍሪካ ቀንድ የአውሮፓ ኅብረት ልዩ ልዑክ አኒታ ዌበር በተመድ ጸጥታው ምክር ቤት ዝግ ስብሰባ ላይ ስለ ሱማሊያ ገለጻ ማድረጋቸውን የሱማሊያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ዌበር በገለጻቸው፣ ጸጥታው ምክር ቤት በሱማሌላንድ ራስ ገዝ ላስ አኖድ ከተማ ለቀጠለው ደም አፋሳሽ ግጭት መፍትሄ እንዲፈልግ መጠየቃቸውን ዘገባዎቹ አመልክተዋል። የግጭቱ ተሳታፊ አካላት፣ ቀደም ሲል ታውጆ ለነበረው ተኩስ አቁም ተገዥ እንዲኾኑ፣ ለግጭቱ ዘላቂ መፍትሄ ለማስገኘት እንዲደራደሩና ለግጭቱ ተጎጂዎች ሰብዓዊ ዕርዳታ እንዲቀርብ እንዲፈቅዱ ዌበር ጠይቀዋል ተብሏል። #ሼር በማድረግ ተባበሩኝ


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
64 views04:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 22:43:45 ጠሚ/ሩ የአማራ ተወላጆች ወደአዲስ አበባ እንዳይገቡ የተደረገውን ክልከላ በቀጥታ እሳቸው ማዘዛቸውን ዛሬ ገልጸዋል። እስከአሁን ጉዳዩ ከኦሮሚያ ክልል አመራሮች ጋር በተያያዘ ነበር ሲነሳ የሰነበተው። በዛሬው የፓርላማ ውሎአቸው የጉዳዩ ባለቤት እሳቸው መሆናቸውን በግልጽ አሳውቀዋል። ታዲያ የፌደራሉ መንግስት ውሳኔ ከሆነ ለምን በኦሮሚያ ልዩ ሃይልና ፖሊስ ፍተሻና ብርበራው እንዲሁም ክልከላው እንዲከናወን እንዳስፈለገ ሊገልጹልን ግን አልቻሉም። ጠሚ/ሩ በቀጣይም ክልከላው ተጠናክሮ እንደሚካሄድ ገልጸዋል። ''ሰላማዊ ዜጎችን ለይተን ሌላውን አናስገባም'' ሲሉም ፈርጠም ብለው ተናግረዋል። መቼም ከሰውዬው የሚሰማው ሁሉ ጉድ የሚያሰኝ ነው። እሳቸው አእምሮ ውስጥ እየመጣ የሚያስበረግጋቸውና ስልጣናቸውን ሊነጥቅ የሚያስፈራራቸው ሃይል አዲስ አበባ እስኪመጣ ለምን ይጠብቁታል? ጎንደርም ካለ አሳይታ፡ ጂግጂጋም ይሁን ወላይታ በየትኛውም የኢትዮጵያ መሬት ላይ የእሳቸውን ስልጣን ለመቀማት የተዘጋጀ ሃይል ካለ እርምጃ መውሰድ ሲችሉ አራት ኪሎ ቤተመንግስት እስኪደርስ ለምን ይጠብቁታል? እንደዛ በማድረግስ ከግልበጣ መትረፍ ይቻላልን? እንዲህ እየበረገጉና እየደነበሩ እስከመቼ ይዘልቁታል?

በእርግጥ ይህ አባባላቸው እሳቸው ቤተመንግስታቸውንና ዙሪያቸውን ነው የሚጠብቁት፡ የአዲስ አበባው ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ቀርተዋል እያሉ ነቃፊዎቻቸው የሚናገሩት ሁሉ እውነት ለመሆኑ የሚያረጋግጥ ንግግር አድርጌ ውስጄዋለሁ። ለዚህ ነው ለካ በወለጋ ሰው ሲታረድ መታደግ ያልቻሉት? በዙሪያቸው የሚነደው እሳት መጥፋት ያቃተው እሳቱ አራት ኪሎ የሚደርስ አይደለም፡ እኔን አይነካኝም በሚል ተማምነው መሆኑን ዛሬ ከምንም ጊዜውም በላይ ማረጋገጫ ሰጥተዋል። አንድን ህዝብ በጅምላ መንግስቴን ሊገለብጥ ነው በሚል ፍራቻ የመንቀሳቀስ መብቱን ለመገደብ መወሰናቸው ዘመናዊ ባርነትን መንግስታቸው በይፋ አውጇል ማለት ይቻላል። ''ሰላማዊ ዜጎችን'' ለይቶ የሚያሳልፍ፡ መንግስታቸውን ለመፈንቀል የሚያሴረውን ደግሞ ነጥሎ የሚከለክል ዘመናዊ ማሽን ታጥቀው ከሆነ ቢያሳውቁን መልካም ነው። የዓይንህ ቀለም አላማረኝም በሚል ፍርሃት በወለደው ማን አለብኝነት የሚደረግ መሆኑ ነው እጅግ አደገኛውና አስፈሪው ነገር።#share Godhii
mesay

ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
106 views19:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 20:47:10 ማክሰኞ ምሽት! መጋቢት 19/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ የዓለም ገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) አንድ የባለሥልጣናት ቡድን ድርጅቱ ለኢትዮጵያ ሊሰጥ ለሚችለው የገንዘብ ድጋፍ የቴክኒክ ዝግጅቶችን ለማድረግ አገሪቱ ውስጥ እንደሚገኝ ሮይተርስ ዘግቧል። መንግሥት ለአገር በቀል የኢኮኖሚ መርሃ ግብሩ ማስፈጸሚያ ድርጅቱ የገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርግለት በይፋ ጥያቄ ማቅረቡን የድርጅቱ ቃል አቀባይ መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ድርጅቱ የድጋፍ ጥያቄውን ካጸደቀ፣ ድጋፉ የመንግሥትን የኢኮኖሚ ማሻሻያ ዕቅድ ለመተግበርና የአገሪቱን ኢኮኖሚ በማረጋጋት ሥራ ለመፍጠር፣ ለሰብዓዊ ዕርዳታና ድህነትን ለመቀነስ ይውላል ሲሉ ቃል አቀባዩ መግለጻቸውን ዜና ምንጩ አመልክቷል። መንግሥት በአገሪቱ ሰሜናዊ ክፍሎች ሰላም ለማስፈን እያደረገ ያለውን ጥረትና ከትግራይ ኃይሎች ጋር የደረሰበት የሰላም ስምምነት አተገባበርን አይ ኤም ኤፍ በአዎንታ ይመለከተዋል መባሉን በዘገባው ላይ ተመልክቷል።

2፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ዛሬ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ስለ ሰላም፣ ስለ ክልልነት ጥያቄ፣ ስለ ምጣኔ ሃብት፣ ስለ መፈናቀል እና በሌሎች በርካታ ጉዳዮች ዙሪያ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ዐቢይ፣ ከሥልጣን የመልቀቅ ዕቅድ ይኖራቸው እንደኾነ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ ሥልጣን መልቀቅ አለመልቀቅ በምርጫ ብቻ የሚወሰን እንደኾነ ምላሽ ሰጥተዋል። ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ መንገደኞች እንዳይገቡ ኦሮሚያ ክልል ላይ ስለሚገጥማቸው ክልከላ ደሞ፣ በከተማዋ ሁከት የመቀስቀስና መንግሥትን በኃይል የመገልበጥ ተልዕኮ ተሰጥቷቸው የሚገቡ አካላት እንዳሉ ዐቢይ ተናግረዋል። ከክልሎች ወደ አዲስ አበባ የሚደረገው ፍልሰት፣ በተያዘው ዓመት ከፍተኛ መሆኑንም ዐቢይ ጠቁመዋል። መንግሥታቸው አገር ለማፍረስ እየሠራ ነው ተብሎ ለበቀረበላቸው ጥያቄም፣ ጉዳዩን እንደ ቀልድ እንደሚወስዱትና የአገር መፍረስና መገነጣጠል አደጋ መቆሙን ገልጸዋል።

3፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ መንግሥታቸው ከኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ሰላም ለማውረድ እንቅስቃሴ መጀመሩን ዛሬ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ላይ ተናግረዋል። መንግሥት ለበርካታ ዜጎች ሞትና መፈናቀል ምክንያት የሆነው በክልሉ የሚካሄደው ግጭት እንዲቆም ፍላጎት ያለው መኾኑን ዐቢይ ገልጸዋል። መንግሥት ለግጭቱ ሰላማዊ መፍትሄ ለማፈላለግ ሲል የገዥው ብልጽግና ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር የሚመሩት ኮሚቴ ማቋቋሙን የጠቀሱት ዐቢይ፣ እስካሁን 10 ያህል የሰላም ጥረቶችን እንደተሞከሩ ጠቁመዋል። ኾኖም ቡድኑ ማዕከላዊ አመራር ስለሌለው የሰላም ፍለጋ ሂደቱ መጓተቱን ጠቅላይ ሚንስትሩ ጨምረው ገልጸዋል።

4፤ የቤንሻንጉል ጉሙዝ መንግሥት ወደ ሰላማዊ ኑሮ ለተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች በኢኮኖሚ ተጠቃሚ የሚያደርጉ አንዳንድ ጥቅማጥቅሞችን ለመስጠት መወሰኑን የክልሉ ብዙኀን መገናኛ ዘግቧል። የክልሉ መንግሥት ያሳለፈው ውሳኔ፣ ትጥቃቸውን የፈቱ የቀድሞ አማጺያን በማዕድን፣ ግብርና እና ንግድ እንዲሠማሩ የሚያስችሉ እንደኾኑ ዜና ምንጩ ጠቅሷል። ይህንኑ ውሳኔ ተግባራዊ ለማድረግም፣ የክልሉ መንግሥት የእርሻ ትራክተሮችን፣ የማዕድን ማውጫ መሳሪያዎችን እና የልማት ሥራ ማስጀመሪያ መነሻ ካፒታል እሰጣለሁ ማለቱን ዘገባው ጨምሮ ገልጧል። ክልሉ ለዚሁ ሥራ ምን ያህል በጀት እንደመደበ ግን ዘገባው አልገለጠም።

5፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በኦሮሚያ ክልል ወሊሶ ከተማ አካባቢ በተካሄደው "በሕገወጥ የቀኖና ቤተክርስቲያን ጥሰት" ተግባር ውስጥ የተሳተፉና "በሕገወጥ ሲመት ኤጲስ ጳጳስነት" የተፈጸመላቸው 17 ግለሰቦች ለቤተክርስቲያኗ ቅዱስ ሲኖዶስ የይቅርታ ደብዳቤ ማስገባታቸውን የቤተክርስቲያኗ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። 17ቱ ግለሰቦች የይቅርታ ደብዳቤያቸውን ያቀረቡት፣ ዛሬ በጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት ከሲኖዶሱ ከፍተኛ ኃላፊዎች ከአቡነ አብርሃም እና ከአቡነ ጴጥሮስ ጋር ከተነጋገሩ በኋላ መኾኑን ዜና ምንጮቹ ጠቅሰዋል። አቡነ አብርሃም እና አቡነ ጴጥሮስም፣ የይቅርታ ደብዳቤውን ለቅዱስ ሲኖዶሱ ለማቅረብ ቃል መግባታቸው ተገልጧል። ቀሪዎቹ ግለሰቦች በቅርብ ቀናት ተመሳሳይ የይቅርታ ደብዳቤ ያስገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ዜና ምንጮቹ ጨምረው ጠቅሰዋል።

6፤ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ሰሞኑን በኬንያ የተቀሰቀሰእ ጸረ-መንግሥት ሁከት እንዳሳሰባቸው ዛሬ ባወጡት መግለጫ አስታውቀዋል። ፋኪ፣ ሁሉም ወገኖች ሁከትን አስወግደው የአገር አንድነትን መሠረት ባደረገ መልኩ ልዩነቶቻቸውን በንግግር እንዲፈቱ ጥሪ አድርገዋል። ፋኪ በዚሁ መግለጫቸው፣ ባለፈው ነሐሴ በአገሪቱ በተደረገው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ዊሊያም ሩቶ ማሸነፋቸውን የአገሪቱ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያረጋገጠው ሃቅ መሆኑን ጠቅሰዋል። ታዋቂው የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ራይላ ኦዲንጋ ትናንት በጠሩት የተቃውሞ ሰልፍ፣ በተቃዋሚዎች እና ፖሊስ መካከል ግጭትና ከፍተኛ የንብረት ውድመት መድረሱን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ከተቃውሞ ሰልፉ ዓላማዎች መካከል፣ መንግሥት የኑሮ ውድነቱን እንዲፈታና ተቃዋሚዎች "ተጭበርብሯል" ለሚሉት ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ፍትህ መጠየቅ ይገኙበታል።

7፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 53 ብር ከ8833 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 54 ብር ከ9610 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 63 ብር ከ0933 ሳንቲም እና መሸጫው 64 ብር ከ3552 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ58 ብር ከ0269 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ59 ብር ከ1874 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩኝ


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
121 views17:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 12:52:41 ያው አዲስ ነገር የለም። እንደተለመደው እሳቸው ሌላ ዓለም ላይ መሆናቸውን ዛሬም ከዚያው ቦታቸው ንቅንቅ ያላሉ እንደሆኑ ከማሳየት ያለፈ ፍሬ የሚቋጥር፡ እውነት የሆነ፡ ሀገርን ከመጣባት አደጋ የሚያድናትን መፍትሄ የሚናገሩ መሪ ሆነው አላገኘኋቸውም። በኢኮኖሚ የደቀቀች፡ በግጭቶች አቅሏን የሳተች፡ በዘርፈ ብዙ ችግሮች ጎሮሮዋ የታነቀ፡ ዘረኝነት የሚያምሳት፡ የዜጎቿ ሲዖል የሆነች ሀገር መሪ አይመስሉም። አሁንም ሌላ ቦታ ናቸው። ሀቅን ሊኖሯት አልቻሉም። መሬት ላይ ያለውን እውነታ መምሰል ተስኗቸዋል። የእሳቸውን ጉድፍ ለማየት ወኔ ያጠራቸው፡ በአብዛኛው ንግግራቸው የራሳቸውን ድክመትና ክፍተት ''የተቀደሰ'' የሌላውን ችግር ''ውእግዝ ከማዕሪዮስ'' የሆነ አድርገው ለማሳየት እዚህም እዚያም ሲረግጡ እንጂ ያየኋቸው ወገብ የሚቆርጥ ምጥ ይዟት የምትሰቃይን ሀገር የሚያስተዳድሩ መሪ ፈጽሞ አይመስሉም። እየራበው ያለን ህዝብ ነገ ስለምትበለጽግ ረሃቡን እንደበረከት ቁጠረው የሚሉ ደፋር ሰው ናቸው። ኢትዮጵያ እናንተ ጭንቅላት ውስጥ ነው የፈረሰችው ብለው ሲናገሩ ኢትዮጵያ በእሳቸው የአእምሮ ጓዳ ብቻ በልጽጋ እየታየች ስለመሆኗ ይዘነጉታል። ፍየል ወዲያ ቅዝምዝም ወዲህ። እሳቸው ወዲያ፡ ሀገሪቱ ወዲህ። አልተገናኝቶም።

አቶ ክርስቲያን ታደለ ''ስልጣንዎን ለመልቀቅ አያስቡምን?'' ብለው በትህትና ለጠየቋቸው ጥያቄ ለምን እንደዚያ እንደተገረሙ አልገባኝም። ስልጣን መልቀቅ እኮ ታላቅነት ነው። ለዚያውም ሀገሪቱን እንደዚህ ዓይነት መጠነ ሰፊ አደጋ ላይ የጣላትን መሪ ይቅርና ''ሴትን ልጅ ጎነተልክ'' ተብሎ የስልጣን መልቀቅ ጥያቄ የሚቀርብባት ዓለም ላይ መኖራቸውን ዘንግተውታል። እውነት ለመናገር ለእሳቸው ስልጣን ልቀቁ የሚለው ጥያቄ ሀቀኝነት ያለው፡ ምንም እንከን የማይወጣለት ተገቢ ጥያቄ ነው። በዚህ መልኩ በክብር መጠየቃቸውን ማመስገን ሲገባቸው ለመሳለቅና በተረት ዙሪያ ጥምጥም በመሄድ ጠያቂውን ለማበሻቀጥ መሞከር ትዝብት ላይ የሚጥላቸው ነው። ቀርበው የኢትዮጵያን ህዝብ ቢያዳምጡትና ስለእሳቸው ምን እያለ እንዳለ ቢያውቁ አቶ ክርስቲያን ያቀረቡላቸው ጥያቄ አያስደነግጣቸውም ነበር። የመለሱበት መንገድ ቅንነት የጎደለው ብቻ አይደለም። ለስልጣን ያላቸውን ጥልቅ ጥማት ያጋለጠባቸውም ጭምር ነው። ሀገሪቱን በዚህ በኩል እለውጣታለሁ ብለው ሞከሩ። አልተሳካም። ስለዚህ ለሌላው እድል ልስጥ የሚል ታላቅነትን የሚያንጸባርቅ፡ ከእኔነትነት ይልቅ ህዝቤንና ሀገሬን ላስቀድም ከሚል በሳልና አስተዋይ መሪ የሚጠበቅ ትንሹ እርምጃ መሆኑን ጭራሽ አያውቁትም። የኢትዮጵያ የብርሃን መንገድ የእኔ ብቻ ነው የሚል ክፉ ደዌ ደማቸው ውስጥ የተቀበረ መሆኑ እሳቸውንም ሀገሪቱንም መላቅጥ እንዲያጡ አድርጓቸዋል።

ስለዛሬው ውሎአቸው አንድ በአንድ፡ መስመር በመስመር መሞገት ትርጉም የለውም። እሳቸው አሁንም ሌላ ዓለም ላይ የጀመሩትን ኑሮ መቀጠል መፈለጋቸውን ነግረውናል። ወደእኛ ሊመጡ አልፈቀዱም። ወይም ወደእሳቸው ዓለም ሊወስዱን አልፈለጉም። እሳቸው እዚያ ህዝባቸው እዚህ እየኖሩ እንዴት መግባባት ይቻል ይሆን? #ሼር በማድረግ ተባበሩኝ


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
መሳይ መኮንን
162 views09:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 12:52:41
ምንም ለውጥ የለም
151 views09:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 11:29:29 ክርስቲያን ታደለ ለጠቅላይ ሚንስትሩ ያቀረቡት ጥያቄ
ዛሬ መጋቢት 19 ቀን 2015 ዓ.ም እየተካሄደ ባለው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ  የቀረበ ጥያቄ፤
**
አመሰግናለሁ የተከበሩ አፈጉባዔ፤

አመሰግናለሁ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር፤

ጥያቄዬን ከማቅረቤ በፊት ስለጥያቄዬ ትንሽ ማለት እፈልጋለሁ። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር በዚህ ምክር ቤት እና በተለያዩ መድረኮች ስለእርስዎና ስለሚመሩት የአስፈፃሚ መንግስት ተጠየቅ ሲቀርብብዎ ለተጠየቁ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ጠያቂዎችን የሚያጥላላ አስተያየት ሲያራምዱ፤ አለፍ ሲልም ተጠየቅ የቀረበብዎት የወጡበት ብሔርን በመጥላት እንደሆነ አድርገው ምላሽ መስጠትዎ የቅርብ ትዝታ ነው። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር ቀጥዬ የማቀርብልዎ ጥያቄ ራስዎንና መንግስትዎን የሚመለከት እንጂ ሌላ ማንንም የማይመለከት መሆኑን ማረጋገጥ እፈልጋለሁ። እኔም ጥያቄውን የማቀርብልዎት በብሔር አይደለም። ምላሽ ሲሰጡም የመንግስት ግልበጣ ለማድረግ የተሼረበ ሴራ ነው የሚል እንደማይሆን ተስፋ አደርጋለሁ። ጥያቄዬ የሚከተለው ነው።

የዜጎችን ደኅንነት እና የአገርን ሉዓላዊነት መጠበቅ ዝቅተኛ የመንግስት ኃላፊነት ሆኖ ሳለ ዜጎች በማንነታቸው ምክንያት በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ይገደላሉ፤ ይፈናቀላሉ፤ ቤታቸው ይፈርሳል፤ ንብረታቸውም ይወድማል። የአገር ሉዓላዊነትን በሚዳፈር መልኩ የጎረቤት አገራት ሰራዊቶች በኢትዮጵያ ሰሜን ምዕራብና ደቡብ ምዕራብ ወሰኖች በርካታ ኪሎሜትሮችን ዘልቀው በመግባት ወረራ ፈጽመዋል። አሁን ላይ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ የዜጎች ደኅንነትና የአገር ሉዓላዊነት ዋነኛ የስጋት ምንጭ ሆኖ የምናየው ራሱ መንግስትን ነው። እርስዎ  በአፍዎ «ኢትዮጵያ አትፈርስም» ቢሉንም በተግባር ግን ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነት በመንግስትዎ እየተናዱ ነው። የበርካታ አገራት መሪዎቸ መሰል ኃላፊነትን በወጉ ያለመወጣት ጉድለት ሲያሳዩ ሕዝብን ይቅርታ ጠይቀው ሥልጣናቸውን ሲለቁ ይታያል። በአገራችንም የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ኃይለማርያም ደሳለኝ ተመሳሳይ ሕዝባዊ ተጠየቅ ሲቀርብባቸው ሥልጣን መልቀቃቸው ይታወሳል።

እርስዎስ ሥልጣንዎን በመልቀቅ የመፍትሔው አካል ለመሆን አላሰቡም ወይ?  በሰብአዊነት ላይ በተፈፀሙ እንዲሁም የማንነት ተኮር የዘር ማጥፋት፣ የዘር ማጽዳትና የማንነት ማሳሳት ወንጀሎች ተጠያቂ ለመሆን ምን ያህል ዝግጁ ነዎት?

አመሰግናለሁ! #ሼርርር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
164 views08:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ