Get Mystery Box with random crypto!

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ) Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ)
የሰርጥ አድራሻ: @zemedkun_zemede
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.26K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-06-19 20:34:12 ኢትዮ ቴሌኮም የ994 የጥሪ ማዕከል አገልግሎቱን ለውስን ደንበኞች ብቻ ክፍት እንዲሆን አደረገ
ኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞቹ ከጥሪ ማዕከል ሰራተኞች ጋር የሚገናኙበትን አገልግሎት፤ በከፊል የሚያስቀር አሰራር ተግባራዊ ማድረግ ጀመረ። በአዲሱ አሰራር መሰረት ከድርጅቱ የጥሪ ማዕከል ሰራተኞች ጋር የሚገናኙ ተገልጋዮች፤ “የፕሪሚየም እና የተለዩ አገልግሎቶችን የሚፈልጉ” ተብለው የተለዩ ደንበኞች ብቻ እንደሚሆኑ ኢትዮ ቴሌኮም አስታውቋል።

መንግስታዊው የቴሌኮሚዩኒኬሽን አቅራቢ ድርጅት ከደንበኞቹ ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ከሚሰጥባቸው አማራጮች ውስጥ አንዱ፤ ወደ ተቋሙ የጥሪ ማዕከል በ994 አጭር ቁጥር መወደል ነው። በዚህ ቁጥር ላይ የሚደውል ደንበኛ፤ በስልኩ ላይ በድምጽ የሚቀርብለትን አማራጮች በመከተል የሚፈልገውን የአገልግሎት አይነት እንዲያገኝ ይደረጋል። ደንበኞቹ ከተቋሙ አገልግሎቶች ጋር በተያያዘ ለሚያነሷቸው ጥያቄዎችም፤ በመስመር ላይ የሚጠብቁ የጥሪ ማዕከሉ ሰራተኞች ምላሽ ይሰጣሉ።

የኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ለጥሪ ማዕከሉ ከሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች ውስጥ አብዛኛዎቹ “የፒን ቁጥርን ከመርሳት፣ የጥሪ ዝርዝርን ከመጠየቅ እንዲሁም ስልክ ቁጥር ከማስከፈት እና ከማዘጋት” ጋር የተያያዙ መሆናቸውን የተቋሙ ቺፍ ኮሚዩኒኬሽን ኦፊሰር አቶ መሳይ ውብሸት ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። እነዚህ ጥያቄዎች እንዲመለሱላቸው የሚፈልጉ ደንበኞች መስመሩን ለረጅም ጊዜ ይዘው የሚቆዩ መሆናቸው እና ቁጥራቸውም በርካታ መሆኑ፤ ሌሎች “መሰረታዊ ጥያቄዎች የሚጠይቁ ሰዎች” ከጥሪ ማዕከሉ ሰራተኞች ጋር እንዳይገናኙ ማድረጉን አስረድተዋል።
መረጃ ህይወት ነው፣ ይህንንም መረጃ ለጓደኞቻችሁ#Share በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ


t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
234 views17:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-19 20:24:08 ሰኞ ምሽት! ሰኔ 12/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ ምርጫ ቦርድ ዛሬ በደቡብ ክልል ወላይታ ዞን በድጋሚ ሲያካሂድ የዋለውን የክልልነት ሕዝበ ውሳኔ ድምጽ አሰጣጥ የሰዓት ገደብ ከምሽቱ 12 ሰዓት ወደ 1 ሰዓት ማራዘሙን አስታውቋል። የዞኑ ድምጽ ሰጭዎች ድምጽ ሲሰጡ የዋሉት፣ ወላይታ ዞን ባለፈው ጥር 29 ቀን ሕዝበ ውሳኔ ካካሄዱት ሌሎች አምስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ጋር በጋራ አንድ ራሱን ያቻለ ክልል እንዲያቋቁም "እደግፋለኹ" ወይም "አልደግፍም" በሚሉ አማራጮች ላይ ነው። ቦርዱ ዛሬ በዞኑ በድጋሚ ሕዝበ ውሳኔ ያካሄደው፣ ጥር 29 በዞኑ የተካሄደው ሕዝበ ውሳኔ "መጠነ ሰፊ የሕግ ጥሰት" ታይቶበታል በማለት ውጤቱን በመሰረዙ ነው። ሌሎች አምስት ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ግን ከደቡብ ክልል ተነጥለው ራሱን የቻለ አዲስ ክልል ለማቋቋም በአብላጫ ድምጽ መወሰናቸው ይታወሳል።

2፤ ምርጫ ቦርድ ዛሬ በደቡብ ክልል ወላይታ ዞን በድጋሚ ሲያካሂድ በዋለው የክልልነት ሕዝበ ውሳኔ ዙሪያ ምሽት 2:00 ሰዓት ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጥ አስታውቋል። ቦርዱ ከአዲስ አበባ 5 ሺህ 215 እንዲኹም ከወላይታ ዞን 3 ሺህ 845 የምርጫ አስፈጻሚዎችን ለሕዝበ ውሳኔው ማሠማራቱንና በዞኑ በጠቅላላው በ1 ሺህ 812 ጣቢያዎች ድምጽ ሰጪዎች ድምጽ ሲሰጡ እንደዋሉ በሌላ መግለጫው ገልጧል። ሦስት የአገር ውስጥ ሲቪክ ተቋማት 214 ታዛቢዎችን በዞኑ ማሠማራታቸውንም ቦርዱ ጠቅሷል። በርካታ ድምጽ ሰጪዎች ስድስት ወር ያልሞላው መታወቂያ ይዘው መገኘታቸውን የጠቀሰው ቦርዱ፣ መራጮቹ ሦስት የሰው ምስክሮችን አቅርበው ድምጽ እንዲሰጡ ተደርጓል ብሏል።

3፤ በአማራ ክልል ስር ራሱን "የወልቃይት ጠገዴ ዞን" በማለት ያዋቀረው አስተዳደር ምክትል ሊቀመንበር ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ከግጭት ማቆም ስምምነቱ በኋላ አስተዳደሩ ከወልቃይት ጠገዴ አካባቢ የትግራይ ተወላጆችን አላፈናቀለም በማለት ማስተባበላቸውን ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል። ከአካባቢው ለቀው የሚሄዱ የትግራይ ተወላጆች "በራሳቸው ፍቃድ ብቻ" ለቀው የሚሄዱ መኾናቸውን ደመቀ ጠቅሰው፣ በአካባቢው በርካታ የትግራይ ተወላጆች አኹንም እየኖሩ መኾኑን ማንም አካል በአካል መጥቶ ማረጋገጥ ይችላል ማለታቸውን ዘገባው አመልክቷል። ሂውማን ራይትስ ዎችና አምነስቲ ኢንተርናሽናል ኮሎኔል ደመቀ አኹንም የትግራይ ተወላጆችን ከአካባቢው በግዳጅ ያፈናቅላሉ በማለት በቅርቡ ላቀረቡባቸው ውንጀላ፣ ድርጅቶቹ በወልቃይት ጉዳይ ላይ "የሕወሃት ቃል አቀባይ እንጂ የመብት ተሟጋቾች" አልኾኑም በማለት መክሰሳቸውን ዘገባው ጨምሮ ጠቅሷል። የወልቃይት ጥያቄ ከሕዝበ ውሳኔ ይልቅ፣ ታሪክንና ሕግን መሠረት ያደረገ ሕጋዊ ምላሽ እንዲሰጠው እንደሚፈልጉ ደመቀ ተናግረዋል ተብሏል።

4፤ በኢትዮጵያ ለዘንድሮው የምርት ዘመን ከፍተኛ የአፈር ማዳበሪያ እጥረት በመከሰቱ በተለይ በአማራ ክልል አርሶ አደሮች የማዳበሪያ ጥያቄያቸውን በሰላማዊ ሰልፍ እስከማቅረብ ደርሰዋል። በአገሪቱ የአፈር ማዳበሪያ እጥረት መከሰቱን ያመነው ግብርና ሚንስቴር፣ ሰሞኑን ጅቡቲ ወደብ የደረሰ 7 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል ማዳበሪያ ወደ አገር ውስጥ እየተጓጓዘ መኾኑን መናገሩን መንግሥታዊ ዜና አውታሮች ዘግበዋል። ሰሞኑን ጅቡቲ የገባው የአፈር ማዳበሪያ፣ መንግሥት ዘንድሮው የምርት ዘመን ከውጭ ገበያ የገዛው 12 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ማዳበሪያ አካል እንደኾነ ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።

5፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ4852 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ5749 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 66 ብር ከ6651 ሳንቲምና መሸጫው 67 ብር ከ9984 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ59 ከ6449 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ60 ብር ከ8378 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል።
መረጃ ህይወት ነው፣ ይህንንም መረጃ ለጓደኞቻችሁ#Share በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ


t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
226 views17:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-19 10:33:47
12 ቅዱስ ሚካኤል
መልካም ነገር የምንሰማበት ይሁንልን

የአደይ ድራማዎችን ማገኘት ከፈለጋችሁ ይህንን ይጫኑ t.me/adey121
253 views07:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-19 07:19:15 ሰኞ ጠዋት! ሰኔ 12/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ ምርጫ ቦርድ ዛሬ በደቡብ ክልል ወላይታ ዞን በድጋሚ የክልልነት ሕዝበ ውሳኔ ያካሂዳል። ቦርዱ ሕዝበ ውሳኔውን ዛሬ በድጋሚ የሚያካሂደው፣ ቦርዱ ባለፈው ጥር 29 በስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች የክልልነት ሕዝበ ውሳኔ ማካሄዱ ይታወሳል። ኾኖም ቦርዱ የወላይታ ዞን ሕዝበ ውሳኔ ሂደት የሕግ ጥሰት ተገኝቶበታል በማለት ውጤቱን ሙሉ በሙሉ በመሰረዙ ነው ሕዝበ ውሳኔው በድጋሚ የሚካሄደው። ቦርዱ በዞኑ ለሚካሄደው ሕዝበ ውሳኔው 1 ሺህ 812 ድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ማዘጋጀቱን ገልጧል።

2፤ የኢትዮጵያ የስደተኞች ጉዳዮች ቢሮ የዓለም ምግብ ፕሮግራምና የአሜሪካ ተራድዖ ድርጅት የምግብ ዕርዳታ በማቋረጣቸው በአገሪቱ የተጠለሉ ስደተኞች ከፍተኛ ችግር ላይ መውደቃቸውን መናገሩን ሪፖርተር ዘግቧል። በተለያዩ የስደተኛ መጠለያ ካምፖች የተጠለሉ 1 ሚሊዮን ስደተኞች የምግብ እርዳታ እንደተቋረጠባቸው የቢሮው ዋና ዳይሬክተር ተስፋሁን ጎበዛይ መግለጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ከሱማላላንዱ ግጭት የተሰደዱ ከ91 ሺህ በላይ ስደተኞች በሱማሌ ክልል የተጠለሉ ሲኾን፣ ከሱዳን ግጭት የሸሹ ከ10 ሺህ በላይ ሱዳናዊያንና ኤርትራዊያን ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ ውስጥ እንደገቡ የተመድ መረጃዎች ያመለክታሉ።

3፤ የሱማሊያ መንግሥት በተያዘው ወር አፍሪካ ኅብረት ከአገሪቱ በከፊል የሚያስወጣቸውን ሰላም አስከባሪ ወታደሮች ለመተካት 20 ሺህ ወታደሮችን ማዘጋጀቱን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። አፍሪካ ኅብረት ከተያዘው ወር ጀምሮ በጥቂት ወራት ውስጥ ኹለት ሺህ ወታደሮችን ከሱማሊያ ለማስወጣት አቅዷል። ሱማሊያ የኅብረቱ ወታደሮች ሲወጡ የጸጥታ ክፍተቱን የሚሞሉት 20 ሺህ ወታደሮች፣ ኤርትራ፣ ኢትዮጵያ እና ኡጋንዳ ያሰለጠኗቸው እንደኾኑ ጠቅላይ ሚንስትር ሐምዛ ባሬ መናገራቸውን ዘገባዎች ጠቅሰዋል። ኅብረቱ በአውሮፓዊያን አቆጣጠር በ2024 ዓ፣ም ኹሉንም ሰላም አስከባሪ ወታደሮቹን ከአገሪቱ የማስወጣት እቅድ አለው።

4፤ ኹለቱ የሱዳን ተፋላሚ ወገኖች ሌላ የ72 ተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ደርሰዋል። አዲሱ የተኩስ አቁም ስምምነት ከዛሬ ንጋት 12 ሰዓት ጀምሮ ተግባራዊ ይኾናል። እንደካኹን ቀደሙ ኹሉ ተፋላሚዎቹ ወገኖች ከአኹኑ ተኩስ አቁም ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ያስቻሉት፣ የሳዑዲ ዓረቢያና አሜሪካ አደራዳሪዎች ናቸው።
መረጃ ህይወት ነው፣ ይህንንም መረጃ ለጓደኞቻችሁ#Share በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ


t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
252 views04:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-18 11:49:53
አባቴ ደፈረኝ!
#ሼር አድርጉት

የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ
@adey121
288 views08:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-18 11:45:55 የ“ኦነግ” ሸኔ ታጣቂዎች ከአዲስ አበባ 75 ኪሎ ሜትር እርቀት ላይ በምትገኝ ወረዳ አንድ ቀበሌ መቆጣጠራቸው ተገለጸ

ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው እና በመንግሥት ኦነግ ሸኔ ተብሎ በአሸባሪነት የተፈረጀው ታጣቂ ቡድን አባላት በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ዋጫሌ ወረዳ፣ አርብ ሰኔ 9/2015 ተኩስ ከፍተው አንድ ቀበሌ መሉ በሙሉ መቆጣጠራቸውን አዲስ ማለዳ ከአካባቢው ነዋሪዎች ሰምታለች። 

በዚህም ታጣቂዎቹ በወረዳው ሥር ካሉ የገጠር ቀበሌዎች አንዷ የሆነችውን ጉምቢቹ ቀበሌ አርብ ዕለት ሙሉ ለሙሉ በቁጥጥራቸው ሥር ማድረጋቸውን የተገለጸ ሲሆን፤ የቀበሌው ነዋሪም በከፍተኛ ስጋት ውስጥ ናቸው ተብሏል።

በተጨማሪም በዕለቱ ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ገደማ ከአዲስ አበባ በስተሰሜን 75 ኪሎሜትር እርቀት ላይ ከምትገኘዋ የወረዳው ከተማ ሙከጡሪ በመግባት ኹለት ሰዎችን አፍነው ሲወስዱ አንድ ሰው ላይ ደግሞ ከፍተኛ ጉዳት አድርሰው መሰወራቸው ተገልጿል።

በአካባቢውም ከሰላሳ ደቂቃ በላይ ከፍተኛ የተሰኩስ ድምጽ ይሰማ እንደነበር ነዋሪዎች ጨምረው ገልጸዋል።

የታጣቂ ቡድን አባላት በአካባቢው በተለይም ከአንድ ዓመት ወዲህ በስፋት እንደሚንቀሳቀሱና በፈለጉት ሰዓት በመምጣት ነዋሪዎችን አፍነው እንደሚወስዱ ነው የተገለጸው፡፡

ነዋሪዎቹን በተለያዩ ጊዜያት አፍነው ከወሰዱ በኋላም "ከ200 ሺሕ እስከ 1 ሚሊዮን ብር ክፈሉ" እያሉ እንደሚደራደሩ ነው የተገለጸው፡፡

ከአንድ ሳምንት በፊት የወረዳው የባህል እና ቱሪዝም ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሌሊት ላይ በታጣቂዎች በመሳሪያ ተመትተው መገደላቸው የተጠቀሰ ሲሆን፤ የአካባቢው ነዋሪዎችም ከሚኖሩበት ቀዬ በየዕለቱ እንደሚፈናቀሉ ተመላክቷል።

በወረዳው የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በስፋት ያሉ ቢሆንም፤ ታጣቂ ቡድኑ በፈለገው ሰዓት እየገባ ሰላማዊ ሰዎችን አፍኖ እንደሚወስድም ነው የተገለጸው፡፡

አዲስ ማለዳ በጉዳዩ ዙሪያ ከዋጫሌ ወረዳ ሰላም እና ጸጥታ ዘርፍ ጽህፈት ቤት ምላሽ ለማግኘት ተደጋጋሚ ሙከራ ብታደርግም ሳይሳካ ቀርቷል።
መረጃ ህይወት ነው፣ ይህንንም መረጃ ለጓደኞቻችሁ#Share በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ


t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
256 views08:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-18 11:01:50 የቀጠለ
10) የሕወሓት ታጣቂዎች በአንድ ሳምንት ውስጥ በጠለምት አምስት ንጹሃን ሰዎችን መግደላቸው ተገለጸ፡፡  በአማራ እና ትግራይ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች በሚንቀሳቀሱ የሕወሓት ታጣቂዎች ከባለፈው ግንቦት ወር መጨረሻ ጀምሮ እስከ ትናንት ሰኔ 08/2015 ድረስ ባሉት ቀናት አምስት ንጹኃን ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ፡፡

በሰሜን ጎንደር ዞን የምዕራብ ጠለምት ወረዳ ሰላም እና ደህንነት ኃላፊ አለባቸው አለሙ፤ በጠለምትና ተከዜ ዙሪያ በሚንቀሳቀሱ በርካታ የሕወሓት ታጣቂዎች ንጽሃን መገደላቸውን እና ብዙዎችም መፈናቀላቸውን ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል። ስለሆነም የሕወሓት ታጣቂዎች በአካባቢው ማህበረሰብ ላይ እያደረሱት ያለውን ማንነት ተኮር በደል ለማውገዝ በጠለምት እና አካባቢው ዛሬ እሁድ ሰኔ 11/2015 ሰላማዊ ሰልፍ ሊያደርጉ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

11) በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ ስምንት ዞኖች ሥር ባሉ 41 ወረዳዎች በተከሰተው የኮሌራ በሽታ ወረርሽኝ፤ 6 ሺሕ 159 ሰዎች በበሽታው መያዛቸውን እና ከእዚህም ውስጥ ከ70 በላይ ሰዎች ሕይወታቸው ማለፉን የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ለአዲስ ማለዳ ገልጿል።

በኦሮሚያ ጤና ቢሮ የድንገተኛ የሕብረተሰብ ጤና ቁጥጥር እና ምርመር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ገመቹ ሹሚ፤ በበሽታው ከሞቱት ከ70 በላይ ሰዎች መካከል አብዛኞቹ በሽታው የቆየባቸውና በፍጥነት ወደ ሕክምና ተቋም ያልመጡ ብሎም ተጓዳኝ በሽታ ያለባቸው መሆናቸውን ጠቁመዋል። 

12) በትግራይ ክልል ከሚገኙ 93 ወረዳዎች 26 ያህሉ ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ውጭ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ መቀሌ ቅርንጭፍ ለአዲስ ማለዳ ገልጿል።

የቅርንጫፉ ጊዜያዊ ኃላፊ ጸሐዬ እምባዬ፤ "ክልሉ ከኤርትራ እና አማራ ክልል ጋር በሚዋሰንባቸው አካባቢዎች ያሉ 26 ወረዳዎች በኤርትራና አማራ ኃይሎች ቁጥጥር ሥር ናቸው።" ሲሉ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል። 

13) በአፋር ክልል አዋሽ አርባ ዞን አሚበራ ወረዳ የአፋር ክልል ፖሊስ አባል በመከላከያ ሠራዊት አባል መገደሉን ተከትሎ በተፈጠረ ግጭት ከመተሃራ ወደ አዋሽ አርባ፣ ወደ ድሬዳዋና፣ ሃረር የሚወስደው ዋና መንገድ መዘጋቱ ተገለጸ።

ለመንገዱ መዘጋት ምክንያት የሆነው አርብ ሰኔ 9/2015 ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ የአፋር ክልል ፖሊስ አባል የነበረ አንድ ግለሰብ በመከላከያ ሠራዊት አባል በጥይት ተመቶ መሞቱን ተከትሎ በተፈጠረ አለመግባበት መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ለEMS Mereja ተናግረዋል፡፡
መረጃ ህይወት ነው፣ ይህንንም መረጃ ለጓደኞቻችሁ#Share በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ


t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
214 views08:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-18 11:01:50 የሳምንቱ አንኳር ዜናዎች 

እሁድ ሰኔ 11 ቀን 2015 (EMS Mereja)

1) በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ባቱ (ዝዋይ) ከተማ እሁድ ሰኔ 4/2015 ዕለት ከሌሊቱ አምስት ሰዓት አካባቢ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እና ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ብሎ የሚጠራውና በመንግሥት ኦነግ ሸኔ ተብሎ በአሸባሪነት በተፈረጀው ታጣቂ ቡድን መካከል በተደረገ ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ የአራት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የአካባቢው ነዋሪዎች ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል፡፡

ከሟቾቹ መካከል አንዲት ሴትን ጨምሮ ሦስቱ የመንግሥት የጸጥታ አካላት መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን፤ አንዱ ደግሞ ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን አባል ነው ተብሏል። ለተከታታይ ኹለት ሰዓታት በላይ ሲደረግ ነበር የተባለው የተኩስ ልውውጥ፤ ዓላማው እስረኛ ለማስፈታት እንደሆነ ተገልጿል።

እስር ቤቱ በተለምዶ ሀይቅ ዳር ወይም የቀድሞ ጤና ጣቢያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ እንደሚገኝ እና ታጣቂዎቹ ከዚህ ቀደምም በእስር ቤቱ የታሰረባቸውን አባል ለማስፈታት ጥረት ሲያደረጉ የሰዎች ሕይወት ማለፉን ነዋሪዎቹ አውስተዋል።

2) ከሶማሊያ ግጭት በመሸሽ ወደ ኢትዮጵያ ከገቡ ስደተኞች ውስጥ 70 በመቶ ገደማ የሚሆኑት መጠለያ ባለማግኘታቸው ሜዳ ላይ እንደሚያድሩ ተገልጿል። ይህ የሆነው በገንዘብ እጥረት መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ለስደተኞች ያስፈልጋል ከተባለው 116 ሚሊዮን ዶላር ውስጥ የተገኘው ኹለት በመቶ ብቻ መሆኑ ተጠቅሷል። ይህን ተከትሎም ለስደተኞች ከሚያስፈልገው መጠለያ 30 በመቶ ብቻ በመሟላቱ ሌሎቹ በአንድ ቦታ ተጨናንቀው በዛፎች ሥርና ሜዳ ላይ እንደሚኖሩ ተመላክቷል። ከሶማሊያ ወደ ኢትዮጵያ ከገቡ ከ100 ሺሕ በላይ ስደተኞች መካከል፤ 20 ሺሕ ያህሉ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ዶሎ ዞን ቦኦ ወረዳ ሚርቃን ቀበሌ በሚገኝ መጠለያ ጣቢያ እንዲገቡ መደረጋቸው ነው የተገለጸው። 

3) ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ባለፉት አስር ወራት 1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ለአዲስ ማለዳ ገልጿል።

በዚህም ከሃምሌ 01/2014 እስከ መጋቢት 30/2015 ድረስ ከአገር ዉስጥ ቦንድና ስጦታ 897 ሚሊዮን በላይ መሰብሰብ መቻሉ የተገለጸ ሲሆን፤ ከዲያስፖራ ቦንድና ስጦታ ከ13 ሚሊዮን በላይ እንዲሁም ከአጭር የሞባይል መልእክት አገልግሎት ከ110 ሚሊዮን ብር በላይ እና በኢትዮጵያ ኤሌትሪክ ኃይል የስጦታ አካውንት ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ እንደተሰበሰብ ተጠቁሟል።

4) በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ኮንሶ ዞን የተከሰተው ድርቅ ባስከተለው ሰብዓዊ ቀውስ ምክንያት ከ190 ሺሕ በላይ ሰዎች አስቸኳይ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው የዞኑ አደጋ ስጋትና መከላከል መምሪያ ለአዲስ ማለዳ ገልጿል።

የኮንሶ ዞን አደጋ ስጋት እና መከላከል መምሪያ ኃላፊ ገደኖ ካዋይታ፤ በዞኑ አሁንም 190 ሺሕ 822 ሰዎች አስቸኳይ ድጋፍ የሚፈልጉ መሆናቸውን ነው የተናገሩት። ኃላፊው አክለውም፤ ለተከታታይ አራት የመኸር ዘመን ተቋራጦ የነበረው ዝናብ በዘንድሮ የበልግ ዘመን መዝነቡን ተከትሎ ቀድሞ ከተለያዩ አካላት ሲደረግ የነበረው ሰብዓዊ ድጋፍ መቀዛቀዙን ተናግረዋል፡፡

5) በበጀት መቋረጥ ምክንያት በጣና ሀይቅ ላይ የተከሰተውን የእንቦጭ አረም የማስወገዱ ሥራ ከአምስት ወራት በፊት መቆሙን የጣና ሐይቅና ሌሎች ዉሃ አካላት ጥበቃና ልማት ኤጀንሲ ለአዲስ ማለዳ ገለጸ።

በዚህም ከባለፈው የካቲት ወር ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ምንም አይነት የእንቦጭ አረም የማስወገድ ሥራ እየተሰራ አለመሆኑን የኤጀንሲው ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶክተር አያሌው ወንዴ ተናግረዋል። በዘንድሮው በጀት ዓመት ሙሉ ለሙሉ የእንቦጭ አረምን ለማስወገድ ታቅዶ እንደነበር የገለጹት ኃላፊው፤ አረሙን ለማስወገድ ለገቡት ማሽኖች የነዳጅ ወጪ እንዲሁም ለኤክስካቫተር ኪራይ ወጪ መሸፈን ባለመቻሉ ሥራው ተቋርጧል ነው ያሉት።

በሀይቁ ላይ የተከሰተውን ከአረም ለማጥፋት በጀት የሚመድበውም በዋናነት በአማራ ክልል እና በፌደራል መንግሥታት መሆኑን አመላክተዋል።

6) በሰሜን ኢትዮጵያ በፌደራል መንግሥት እና በሕወሓት መካከል በተካሄደው ጦርነት በኹለቱም ወገኖች የታሰሩት ተዋጊዎች የት እንዳሉ እስካሁን እንደማይታወቅ ተገለጸ።

ከተኩስ አቁም ስምምነት ጀምሮ እስካሁን ድረስ በጦርነቱ ወቅት ስለታሰሩት በሺዎች የሚቆጠሩ የጦርነት ተሳታፊዎች እና ስለተማረኩት ተዋጊዎች እጣ ፈንታ ከፌደራል መንግሥትና ከሕወሓት በኩል የተሰጠ ምላሽ አለመኖሩ ቅሬታን መፍጠሩ ተገልጿል፡፡ የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የሕግ አማካሪ ፍስሃ ተክሌ፤ በእስር ላይ የሚገኙ የፌደራል መንግሥቱ እና የሕወሓት ወታደሮች እንዲሁም በየአካባቢው በጦርነቱ ተሳትፋችዋል ተብለው ያለክስ የታሰሩ የሚሊሻ አባላት የት እንዳሉ አይታወቅም ማለታቸውን አልጀዚራ ዘግቧል።

7) በኢትዮጵያ 4.8 ሚሊዮን ሕጻናት በተመጣጣኝ ምግብ እጥረት የተነሳ የመቀንጨር አደጋ አጋጥሟቸዋል ተባለ።

የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የአየር ንብረት ትንበያ እና መተግበሪያ ማዕከል፤ የምግብ ቀውሶችን አስመልክቶ ያጠናው ጥናት "ዓለም አቀፍ ሪፖርት 2023" ይፋ ተደርጓል። ጥናቱ በኢጋድ አባል አገራት ላይ ያተኮረ ሲሆን፤ በዚህም በ2022 በኢትዮጵያ 4.8 ሚሊዮን ሕጻናት በተመጣጣኝ ምግብ እጥረት የተነሳ ቀንጭረው እንደነበር ተመላክቷል። ይህም ቁጥር ኢትዮጵያን በምስራቅ አፍሪካ በሕጻናት መቀንጨር ቀዳሚ አገር እንደሚያደርጋትም ተነግሯል።

8) ከትግራይ ክልል እንዳይወጡ የታገዱ ነዋሪዎች የትራንስፖርት አገልግሎት ለማግኘት ጉቦ እየከፈሉ መሆኑን ገለጹ፡፡  በትግራይ ክልል ከ15 እስከ 60 ዕድሜ ያላቸው ሰዎች ከክልሉ በአየርና የየብስ ትራንስፖርት ወደ አዲስ አበባ መሄድ እንዳይችሉ ክልከላ ከመደረጉ ጋር ተያይዞ፤ ለትራንስፖርት ሰጭ ተቋማት ሠራተኞች ጉቦ እየከፈሉ እንደሚወጡ ተናግረዋል።

ነዋሪዎቹ ከትግራይ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በዋናነት ወደ አዲስ አበባ ለመጓዝ የአውሮፕላንም ሆነ የመኪና ትኬት ለማግኘት፤ ለአየር መንገድ ሠራተኞች እና ጥበቃዎች እንዲሁም ለአውቶብስ ሠራተኞች ጎቦ በመክፈል ትኬት እንደሚያገኙ ነው ለአዲስ ማለዳ የገለጹት። ከጦርነቱ ማብቃት በኋላ የትግራይ ክልል ወጣቶች በአውሮፕላንም ይሁን በመኪና ከክልሉ እንዳይወጡ እየተደረገ ነውም ብለዋል።

9) በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን በተከሰተው ድርቅ ለተጎዱ ዜጎች ሲቀርብ የነበረው ሰብዓዊ ድጋፍ መሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ መቋረጡን የቦረና ዞን ቡሳ ጎኖፋ መምሪያ ለአዲስ ማለዳ ገልጿል። 

የመምሪያው ኃላፊ ሊበን ሳራ፤ የድርቁ አስከፊነት በተለያዩ መገናኛ ዘዴዎች ከተሰማ በኋላ፣ ሲደረግ የነበረው ሰብዓዊ ድጋፍ መልካም እንደነበረ የገለጹ ሲሆን፤ ነገር ግን ለአምስት ተከታታይ የዝናብ ወቅቶች ተቋርጦ የነበረው ዝናብ፣ መዝነብ ከጀመረ በኋላ ሲደረግ የነበረው ድጋፍ መቋረጡን አስረድተዋል፡፡

አሁን ላይ መጠነኛ ድጋፍ እያደረገ ያለው “ጆፕ” የተሰኘ መንግሥታዊ ያልሆን ግብረ ሰናይ ድርጅት ብቻ መሆኑን ገልጸው፤ በሌሎች አካላት ሲደረግ የነበረው ሰብዓዊ ድጋፍ ግን ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ መቆሙን ተናግረዋል፡፡
መረጃ ህይወት ነው፣ ይህንንም መረጃ ለጓደኞቻችሁ#Share በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ
http://t.me/emsmereja
213 views08:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-17 20:39:13
ገነት በትኬት
የገነት መግቢያ ትኬት በ 500$ እየሸጠ የነበረ የዝንባብዌ ፓስተር ታሰረ። እየሱስ ክርስቶስ በአካል መጥቶ አግኝቶኝ ነው ትኬቶቹን የሰጠኝ ብሏል።
መረጃ ህይወት ነው፣ ይህንንም መረጃ ለጓደኞቻችሁ#Share በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ


t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
236 views17:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-17 20:30:08 ቅዳሜ ምሽት! ሰኔ 10/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ለኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን በጻፈው ደብዳቤ በጦርነቱ ለተጎዱ የክልሉ ኢንቨስትመንቶች የካሳ ክፍያ፣ የዕዳና የታክስ ስረዛ እንዲደረግላቸው መጠየቁን ሪፖርተር ዘግቧል። ኮሚሽኑ የጥያቄዎቹን አፈጻጸም የሚገመግም የጋራ ኮሚቴ እንዲቋቋም ጭምር ጠይቋል ተብሏል። ኮሚሽኑ የውጭ ኢንቨስትመንት ኩባንያዎች በክልሉ ሙዓለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ፌደራል መንግሥቱ እንዲጋብዝ መጠየቁንም ዜና ምንጩ አመልክቷል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ በበኩላቸው፣ የክልሉ ኢንቨስትመንት ኩባንያዎች ብድር እንዲሰረዝላቸው ወይም የዕዳ መክፈያ ጊዜ እንዲራዘምላቸው ብሄራዊ ባንክን መጠየቃቸውን በዘገባው ተመልክቷል።

2፤ ምርጫ ቦርድ በቀጣዩ ሰኞ በደቡብ ክልል ወላይታ ዞን በድጋሚ የክልልነት ሕዝበ ውሳኔ ያካሂዳል። በዞኑ የሚንቀሳቀሱት ተቃዋሚዎቹ የዎላይታ ብሄራዊ ንቅናቄ እና የዎላይታ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ግንባር ግን ቦርዱ ለሚያካሂደው የክልልነት ሕዝበ ውሳኔ እውቅና አንሰጥም ማለታቸውን ዶይቸቨለ ዘግቧል። ሁለቱ ፓርቲዎች ሕዝበ ውሳኔውን የተቃወሙት፣ ሕዝበ ውሳኔው የዎላይታን ሕዝብ ራሱን የቻለ ክልል የመመስረት መብት የነፈገና ሕገ መንግሥታዊ ጥሰት ያለበት ሂደት ነው በማለት እንደኾነ ዘገባው አመልክቷል። ሁለቱ ፓርቲዎች ፌደሬሽን ምክር ቤት የዞኑን ሕዝብ ሕጋመንግሥታዊ መብት ጥሷል በማለት ቀደም ሲል በፍርድ ቤት ክስ መስርተዋል። የሰኞው ሕዝበ ውሳኔ፣ ጥር ላይ ወላይታን ጨምሮ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ያካሄዱት ሕዝበ ውሳኔ አካል ነው። ቦርዱ በወቅቱ የወላይታ ዞን ሕዝበ ውሳኔ ላይ የሕግ ጥሰት አግኝቼበታለኹ በማለት በድጋሚ እንዲካሄድ መወሰኑ ይታወሳል።

3፤ የሱማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሐመድ የተመድ ጸጥታው ምክር ቤት በአገራቸው ላይ የጣለውን የጦር መሳሪያ ማዕቀብ ሙሉ በሙሉ እንዲያነሳ በአካል እንዲጠይቁ በተያዘው ወር የምክር ቤቱ ሰብሳቢ የኾነችው ወዳጃቸው የተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች ጋብዛቸዋለች። ፕሬዝዳንቱ የጦር መሳሪያ ማዕቀቡ እንዲነሳ ለጸጥታው ምክር ቤት በሚያደርጉት ንግግር የሚጠይቁት፣ ምክር ቤት በሱማሊያ ወቅታዊ ጸጥታ ላይ በተያዘው ወር በሚያዘጋጀው ልዩ ስብሰባ ላይ እንደኾነ የሱማሊያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ጸጥታው ምክር ቤት በአገሪቱ ላይ የጦር መሳሪያ ማዕቀብ የጣለው ከ30 ዓመት በፊት ቢኾንም፣ በተለያዩ ጊዜያት ማዕቀቡን በከፊል አንስቷል።

4፤ የአሜሪካው ፔንታጎን ትናንት ሌሊት በአንድ የአልሸባብ አመራሮች ስብሰባ ላይ በፈጸመው የድሮን ጥቃት በርካቶች መገደላቸውን የሱማሊያ መንግሥታዊ ዜና አውታሮች ዘግበዋል። የድሮን ጥቃቱ የተፈጸመው፣ ከኪሲማዩ ወደብ ወጣ ብሎ በጁባላንድ ራስ ገዝ በታችኛው ጁባ ግዛት እንደኾነ ዘገባዎቹ ገልጠዋል። አልሸባብ የፔንታጎን የድሮን ጥቃት ዒላማ የኾነው፣ በአፍሪካ የአሜሪካ ወታደራዊ ዕዝ (አፍሪኮም) ዋና አዛዥ ከሞቃዲሾና ከጁባላንድ ራስ ገዝ ባለሥልጣናት ጋር በአካል ተወያይተው በተመለሱና የሱማሊያ ጦር ከኢትዮጵያ፣ ኬንያና ጅቡቲ ጦር ጋር ጁባላንድ በሚንቀሳቀሰው አልሸባብ ላይ የተቀናጀ ዘመቻ ለማድረግ በዝግጅት ላይ ባሉበት ወቅት ላይ ነው።

5፤ አንድ የሱዳን ጦር ሠራዊት ከፍተኛ አዛዥ የባርቱም ነዋሪዎች የፈጥኖ ደራሹ ኃይሎች ከመሸጉባቸው ሠፈሮች እንዲወጡ መጠየቃቸውን ሱዳን ትሪቡን ዘግቧል። የጦሩ ከፍተኛ አዛዥና የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት ኣባል የኾኑት ጀኔራሉ ይህን ትዕዛዝ ያስተላለፉት፣ ጦር ሠራዊቱ በየሠፈሩና መኖሪያ ቤቶች የመሸጉትን የፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት ኃይሎች በምድር ውጊያ ሊገጥም በመኾኑ እንደኾነ መግለጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ጦር ሠራዊቱ እስካሁን ካርቱም ላይ ሲዋጋ የቆየው፣ በዋናነት በአውሮፕላና ድብደባና በከባድ መሳሪያ ነው። ጀኔራሉ፣ ውጊያው በአኹኑ ወቅት ከወታደሮች አልፎ ሲቪሉን ሕዝብና የፖለቲካ ኃይሎችን ጭምር ያካተተ ኾኗል ማለታቸውን ዘገባው ጠቅሷል።

6፤ የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሴሪል ራማፎዛ የመሩት ለሩሲያና ዩክሬን ግጭት ሰላማዊ መፍትሄ አፈላላጊ የአፍሪካ መሪዎች ልዑካን ቡድን ዛሬ በሩሲያዋ ፒተርስበርግ ከተማ ገብቷል። ልዐካን ቡድኑ ወደ ሩሲያ ያቀናው፣ ከዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ዘለንስኪ ጋር ከተወያየ በኋላ ነው። የአፍሪካዊያኑ የመሪዎች ልዐካን ቡድን በሩሲያ ቆይታው፣ ግጭቱን በንግግር መፍታት በሚቻልበት ኹኔታ ዙሪያ ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ይወያያል። ልዑካን ቡድኑ፣ የሴኔጋል፣ የዲሞክራሲያዊት ኮንጎ፣ የኮሞሮስ፣ የዛምቢያና የግብጽ መሪዎችን ያካተተ ነው።
መረጃ ህይወት ነው፣ ይህንንም መረጃ ለጓደኞቻችሁ#Share በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ


t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
t.me/emsmereja
233 views17:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ