Get Mystery Box with random crypto!

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ) Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ)
የሰርጥ አድራሻ: @zemedkun_zemede
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.26K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-05-13 07:17:50 ቅዳሜ ጠዋት! ግንቦት 5/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ የትግራይ ክልል የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ዓለማቀፍ ረድዔት ድርጅቶች ያቋረጡት የምግብ ዕርዳታ እንዲቀጥል ጥሪ ማድረጉን ቪኦኤ ዘግቧል። በክልሉ የምግብ ዕርዳታ ሥርጭቱ ባለፈው ወር ከተቋረጠ ወዲህ፣ ወደ ክልሉ እየገቡ ያሉት መጠነኛ የሕጻናት አልሚ ምግቦችና የግብርና ግብዓቶች ብቻ መኾናቸውን ኮሚሽኑ መግለጡን ዘገባው ጠቅሷል። የዓለም ምግብ ፕሮግራም ከሽሬ ከተማ የዕርዳታ መጋዘኔ ከፍተኛ መጠን ያለው የዕርዳታ እህል ተዘርፏል በማለት፣ የዕርዳታ ሥርጭት ማቋረጡ ይታወሳል። የአሜሪካው ዓለማቀፍ የልማትና ዕርዳታ ድርጅትም በተመሳሳይ ምክንያት የዕርዳታ ሥርጭት ለጊዜው አቋርጫለኹ ብሏል።

2፤ ዓለማቀፉ የፍልሰት ድርጅት የጅቡቲ መንግሥት በሕገወጥ መንገድ ገብታችኋል ብሎ ያስወጣቸው 6 ሺህ ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞች አፋር ክልል ደዋሌ መግባታቸውን አስታውቋል። ድርጅቱ፣ በምሥራቃዊው መስመር ማለትም በፑንትላንድ፣ ሱማሌላንድና ጅቡቲ በኩል ወደ ባሕረ ሰላጤው አገራት ለሚሰደዱ 1 ሚሊዮን ያህል ፍልሰተኞች የ58 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ከለጋሾች ጠይቋል። በምሥራቁ መስመር ባሕር አቋርጠው የሚጓዙት ፍልሰተኞች አብዛኞቹ ኢትዮጵያዊያን መኾናቸውን የጠቀሰው ድርጅቱ፣ ለጋሾች ይህንኑ መስመር ዘንግተውታል በማለት ወቅሷል። ድርጅቱ የገንዘብ ድጋፉን የጠየቀው፣ በስደት ወቅት እንግልት ለሚገጥማቸው ፍልሰተኞችና ለተመላሾች የተለያዩ ድጋፎችን ለመስጠት ነው።

3፤ ኢትዮጵያ፣ ሱማሊያና ኬንያ በጋራ ድንበር ጸጥታ ዙሪያ ለመተባበር የሚያስችላቸውን የጋራ ፕሮጀክት መርቀዋል። ከብሪታኒያ መንግሥት የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኘው የጋራ ፕሮጀክቱ መሠረቱ የተጣለው፣ በሰሜን ምሥራቅ ኬንያ ማንዴራ አውራጃ እንደኾነ የኬንያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የፕሮጀክቱ ዓላማ፣ በአገራቱ የጋራ የድንበር አካባቢ ሰላም፣ ጸጥታ፣ ልማትና ድንበር-ዘለል ትብብሮችን ማረጋገጥ ነው። ሦስቱ አገራት የጋራ ፕሮጀክቱን የጀመሩት፣ በነውጠኛው አልሸባብ ላይ የጋራ ወታደራዊ ዘመቻ ለማድረግ ከተስማሙ ከጥቂት ስምንታት በኋላ ነው።

4፤ የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስቴር የኢትዮጵያው "ቦርከና" ጋዜጣ "በኤርትራና ኢትዮጵያ መካከል ውጥረት እየተፈጠረ ይኾን?" በማለት ያተመውን ሃተታ "በሐሰትና ግምታዊ ድምዳሜ የተሞላ" በማለት ተችቷል። ሚንስቴሩ በመግለጫው፣ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ በቅርቡ ስለ ሱዳኑ ግጭት በሰጡት ቃለ ምልልስ ኢትዮጵያን ጎሸም ያደረጉ አስመስሎ አቅርቧል በማለት ወቅሷል። ጋዜጣው "ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሥመራ መሄድ ፈልገው፣ የኤርትራ መንግሥት ሁለት ጊዜ ፍቃድ ነፍጓቸዋል" እንዲኹም "ኤርትራ ለአማራ ፋኖዎች ወታደራዊ ሥልጠና በመስጠቷ የዐቢይ ካድሬዎች ኢሳያስን እየተቹ ነው" በማለት የጻፋቸው ነገሮች "ሐሰት" መኾናቸውንም ሚንስቴሩ ገልጧል። ሚንስቴሩ፣ ኤርትራ አዲስ ወታደራዊ ዝግጅት እያደረገች እንደኾነ ጋዜጣው ያሰራጨውን ወሬም "የተሳሳተ" በማለት አስተባብሏል።

5፤ ደቡብ ሱዳን የግብጹ ፕሬዝዳንት አል ሲሲ በሱዳን ግጭት ዙሪያ ለመምከር የመሪዎች ስብሰባ እንዲካሄድ ለፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ሃሳብ ማቅረባቸውን በውጭ ጉዳይ ሚንስቴሯ በኩል አረጋግጣለች። ፕሬዝዳንት ሲሲ ይህንኑ ሃሳብ ያቀረቡት፣ ውጭ ጉዳይ ሚንስትራቸውን ሳሜ ሽኩሪን ከአራት ቀናት በፊት ወደ ጁባ በላኩበት ወቅት እንደኾነ ሚንስቴሩ ገልጧል። ፕሬዝዳንት ኪር በበኩላቸው፣ የመሪዎች ጉባዔ ከተካሄደ የሁሉንም የሱዳን ጎረቤቶች መሪዎች ያካተተ ይሁን የሚል መልስ መስጠታቸውንና የፕሬዝዳንት ሲሲን ምላሽ እየተጠባበቁ መኾኑን ሚንስቴሩ ጨምሮ አመልክቷል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
169 views04:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 22:32:09 ኢትዮጵያ የብርን የመግዛት አቅም ማዳከሟ አይቀሬ መሆኑን ኢኮኖሚስቶች ተናገሩ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እንደ ሀገር የገጠመውን የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ለመፍታት በሚል በየጊዜው የተለያዩ እርምጃዎችን ሲወስድ ቆይቷል።
የወጪ ንግድን ለማበረታታት እና የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ለመፍታት እንደ መፍትሔ ሲወሰድ የቆየው የብርን የመግዛት አቅም ማዳከም አንዱ ነው።
ለአብነትም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ወደ ስልጣን በመጡበት ወቅት አንድ የአሜሪካ ዶላር 27 ብር ገደማ የነበረ ሲሆን አሁን ላይ በባንኮች 54 ነጥብ 2 ብር በመመንዘር ላይ ሲሆን በጥቁር ገበያ ደግሞ እስከ110 ብር ድረስ እየተመነዘረ ይገኛል።
መንግስት በጦርነት እና ኮሮና ቫይረስ የተጎዳውን ኢኮኖሚ እንዲያገግም ከዓለም አቀፍ የገንዘብ አበዳሪ ተቋማት ብድር እና እርዳታ ለማግኘት ጥረት ላይ እንደሆኑ ይገለጻል።
በቅርቡም የአይኤምኤፍ ባለሙያዎች በአዲስ አበባ ከመንግስት ከፍተኛ ባለሙያዎች እና አመራሮች ጋር በአዲስ አበባ እና በዋሸንግተን ውይይት ማድረጋቸው ና ጥሩ መግባባቶች ላይ ተደርሷል ማለታቸው ይታወሳል።
ይህን ውይይት ተከትሎም ዓለም ባንክ እና አይኤምኤፍ የኢትዮጵያ መንግስት የውጭ ምንዛሬ ተመንን በጥቁር ገበያ ካለው ምንዛሬ ተመን ጋር እኩል እንዲያደርጉ ምክረ ሀሳብ እንዳቀረቡ ሮይተርስ ዘግቧል።
የኢትዮጵያ መንግስት ከሁለቱ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ጋር ያደረጋቸውን ተከታታይ ውይይቶችን አስመልክቶ የደረሱባቸውን ስምምነቶች እስካሁን ግልጽ አላደረጉም።
አል ዐይን አማርኛ በጉዳዩ ዙሪያ የኢትዮጵያ መንግስት ከውጭ ምንዛሬ ተመን እና እጠረቱ ጋር በተያያዘ የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎችን አነጋግሯል።
ዶክተር ሽመልስ አርአያ በማክሮ ኢኮኖሚክስ ጉዳዮች ዙሪያ አማካሪ እና የጥናት ባለሙያ ናቸው፤ እሳቸው እንደሚሉት ከሆነ የኢትዮጵያ መንግስት ከመቼውም ጊዜ በላይ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ገጥሞታል።
እጥረቱን ተከትሎም መንግስት የብርን የመግዛት አቅም ማዳከሙ አይቀሬ ነው፣ እነ ዓለም ባንክም ብዙ ቅድመ ሁኔታዎችን ያስቀመጡት ኢትዮጵያ ያለባትን እጥረት መጠን ስለሚያውቁ ጭምር መሆኑንም ዶክተር ሽመልስ አክለዋል።
ዓለም ባንክ አሁን ያለው የዓለም ኢኮኖሚ ስርዓት እንዲቀጥል ይፈልጋል ያሉት ዶክተር ሽመልስ ስርዓቱ እንዲቀጥል ደግሞ ሀብታም ሀገራት ሀብታም ሆነው እንዲቀጥሉ የግድ ድሃ ሀገራት ከድህነታቸው እንዲወጡ አይፈለግም ብለዋል።
በብዙ ጉዳዮች እየተፈተነ ያለው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የገጠመውን የውጭ ምንዛሬ ተመን ለመፍታት ሲል መንግስት ብድር እና ሌሎች የገንዘብ ድጋፎችን ለማግኘት የብርን የመግዛት አቅም ያዳክማል፣ ለዚህ ደግሞ የውጪ ንግስትን ለማበረታታት የሚል ስም ይሰጣልም ብለዋል።

ከዚህ በፊት የተደረጉ የብርን የመግዛት አቅም ማዳከም ውሳኔዎች የኑሮ ውድነትን ከማባባስ፣ የሐብት ሽሽትን ከመፍጠር እና የንግድ ሚዛንን ከማዛባት ውጪ ጥቅም አለማስገኘታቸውንም አክለዋል ዶከተር ሽመልስ።
እንደ ዶክተር ሽመልስ ገለጻ የሀገር ውስጥ መገበያያ ገንዘብን ማዳከም የሚሰራው እንደ ጃፓን እና ቻይና ያሉ ሰፊ ወደ ውጪ ሊላኩ የሚችሉ ምርቶች ላሏቸው ሀገራት ብቻ እንጂ እንደ ኢትዮጵያ የግብርና ምርቶችን ወደ ውጪ ለሚልኩ ሀገራት አይደለም።
መንግስት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከሚያመነጨው ገቢ በላይ ብር ማተሙን ካላቆመ የኢኮኖሚ ቀውሱ ይጨምራል ያሉት ደግሞ ሌላኛው ኢኮኖሚስት አቶ መቆያ ከበደ ናቸው።
አቶ መቆያ እንዳሉት “የመንግስት ገቢ እና ወጪ አለመመጣጠን፣ ቅንጡ ፕሮጀክቶች ላይ ከፍተኛ ገንዘብ ማፍሰስ እና መንግስት ራሱ የውጭ ምንዛሬ ከጥቁር ገበያ እየገዛ መሆኑ በኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ እጥረቱን እያባባሱ ናቸው” ብለዋል።
“በኢትዮጵያ ማንኛውም ሰው የየትኛውንም ሀገራት መገበያያ ብር እስካለው ድረስ ከጥቁር ገበያ እየገዛ ነው” የሚሉት አቶ መቆያ ይህ የሚያሳየው የውጭ ምንዛሬ ከገበያው ላይ መኖሩን ነው፣ ኢኮኖሚው የውጭ ምንዛሬ እያመነጨ ነው፣ ችግሩ የአያያዝ እንጂ የአቅርቦት አይደለም ሲሉም አክለዋል።
በውጭ ሀገራት ያሉ ኢትዮጵያዊያን ገንዘባቸውን በባንክ አለመላካቸው፣ የውጭ እዳ ከፍተኛ መሆን፣ በኮሮና ቫይረስ እና በጸጥታ ችግሮች ምክንያት ከውጭ ሀገራት ጎብኚዎች የሚገኘው ገቢ ማሽቆልቆል፣ የማዕድናት እና ሌሎች የንግድ ስራዎች ህገ ወጥነት መስፋፋት መንግስትን ለከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እንደዳረገውም ተገልጿል።
መንግስት የገጠመውን የውጭ ምንዛሬ እጥረት ለመፍታት ኢኮኖሚውን በውድድር ለይ የተመሰረተ ማድረግ እና የውጭ ምንዛሬ ተመኑን በባንኮች እና በጥቁር ገበያ ያለውን እኩል ማድረግ ይኖርበታልም ብለዋል።
በኢኮኖሚው አስገዳጅነትም ሆነ በእነ ዓለም ባንክ ቅድመ ሁኔታ የኢትዮጵያ መንግስት የብርን የመግዛት አቅም ማዳከሙ እንደማይቀርም አቶ መቆያ ግምታቸውን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዋና ገዢ ከሰሞኑ የብርን የመግዛት አቅም ሊዳከም ነው በሚል እየተሰራጨ ያለው መረጃ ሀሰት ነው ሲል ማስተባበሉ ይታወሳል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
189 views19:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 21:02:26
#Eritrea
ኤርትራ ከኢትዮጵያ የተገነጠለችበትን 32ኛ ዓመት በዓል እያከበረች ነው።
======================
#ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
197 views18:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 20:10:42 ዓርብ ምሽት! ግንቦት 4/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ የቀድሞው የኢትዮጵያ ጦር ሠራዊት አባላት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቅርቡ አሻሽሎ ያጸደቀው የመከላከያ ሠራዊት አዋጅ የጥቅማ ጥቅምና ጡረታ መብት ጥያቄያችን አልመለስም በማለት ቅሬታቸውን ለዋዜማ ገልጸዋል። ፓርላማው በረቂቅ አዋጁ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በተወያየበት ወቅት፣ የቀድሞው ጦር ሠራዊት አባላት ከውጊያ ሜዳይ አሰጣጥና የጡረታ መብት አጠባበቅ ዙሪያ የሠራዊቱ አባላት መብት እንዲካተት ጠይቀው ነበር። ኾኖም የጸደቀው አዋጅ፣ የቀድሞው ሠራዊት አባላት ላነሷቸው የጡረታ መብትና ሜዳይ አሰጣጥ ጥያቄዎች ምላሽ ሳይሰጥ በመቅረቱ ቅሬታ እንደፈጠረባቸው የሠራዊቱ የድጋፍና ልማት ማኅበርና አባላቱ ተናግረዋል።

2፤ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በአዲስ አበባ ከተማ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የወረዳ ስምንት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አለባቸው አሞኜ ዛሬ ቢሯቸው ውስጥ "የዕለት ተለት ተግባራቸውን" በማከናወን ላይ እንዳሉ ከጧቱ አራት ሰዓት ላይ በሽጉጥ እንደተገደሉ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ሥራ አስፈጻሚውን ገድሏል ተብሎ በቁጥጥር ስር የዋለው ተጠርጣሪ፣ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የካዛንቺስ አካባቢ የማኅበረሰብ ዓቀፍ ፖሊስ አገልግሎት አባል እንደኾነ ኮሚሽኑ ገልጧል። ኮሚሽኑ፣ ተጠርጣሪው በዋና ሥራ አስፈጻሚው ላይ ግድያውን የፈጸመው፣ ለወረዳው አስተዳደር ያመለከትኩት የግል ጉዳዬ "እንዳይፈጸም የከለከልከው አንተ ነህ" በማለት ሟቹን ተጠያቂ በማድረግ ነው ብሏል። ተጠርጣሪው የወረዳው አስተዳደር አልፈጸመልኝም ያለው የግል ጉዳዩ ምን እንደኾነ ግን ኮሚሽኑ አላብራራም።

3፤ ዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት ከኢትዮጵያ መንግሥት የፋይናንስ ድጋፍ ለማድረግ የአገሪቱ ዓለማቀፍ የልማት አጋሮች ግልጽ ቃል ኪዳን በቡድን-20 ማዕቀፍ ውስጥ የአበዳሪዎች የፋይናንስ ድጋፍ ማረጋገጫ ያስፈልጋል በማለት የድርጅቱ ቃል አቀባይ ጁሊ ኮዛክ ትናንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ መናገራቸውን ጠቅሶ ሮይተርስ ዘግቧል። ድርጅቱ ለኢትዮጵያ አገር በቀል የኢኮኖሚ መርሃ ግብር የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ በሚችልበት ኹኔታ ዙሪያ እስካኹንም ከአገሪቱ መንግሥት ባለሥልጣናት ጋር በመነጋገር ላይ መኾኑን ቃል አቀባይዋ መጥቀሳቸውን ዜና ምንጩ አመልክቷል። ኢትዮጵያ በቡድን-20 ማዕቀፍ ስር የውጭ ዕዳ ክፍያ ሽግሽግ እንዲደረግላት የጠየቀችው ከሁለት ዓመት በፊት ነበር። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ኢትዮጵያ የዓለማቀፉ ገንዘብ ድርጅት 2 ቢሊዮን ዶላር ብድር እንዲሰጣት መጠየቋን ሮይተርስ ባለፈው ወር መዘገቡ ይታወሳል።

4፤ አንጋፋዋና ዝነኛዋ ድምጻዊት ኂሩት በቀለ በ83 ዓመቷ ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለየች የአገር ውስጥ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ኂሩት ከ1953 ዓ፣ም ጀምሮ እስከ 1980ዎቹ በርካታ ዘመን ተሻጋሪ ዘፈኖችን የተጫወተች ተወዳጅ ድምጻዊት ነበረች። ድምጻዊት ኂሩት ወደ መጨረሻው የሕይወት ዘመኗ ገደማ ዓለማዊ ሙዚቃዎችን መዝፈን አቁማ፣ ሐይማኖታዊ መዝሙሮችን ስትዘምር እንደነበር ይታወቃል። ዋዜማ ለአንጋፋዋ ድምጻዊት ኂሩት ቤተሰቦችና ለአድናቂዎቿ መጽናናትን ትመኛለች።

5፤ የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በፕሬዝዳንት ዢ ፑንግ ግብዣ በመጭው ዕሁድ ቻይናን እንደሚጎበኙ የቻይናው ሲጂቲኤን ዘግቧል። ፕሬዝዳንት ኢሳያስ እና ፕሬዝዳንት ዢ ፒንግ፣ የኹለቱን አገራት ግንኙነት ወደ "ስትራተጂካዊ አጋርነት" ለማሳደግ ባለፈው የአውሮፓዊያን ዓመት ስምምነት ላይ ደርሰው እንደነበር የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ማስታወሳቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ቻይናባለፈው ዓመት ለመጀመሪያ ጊዜ የሾመቻቸው የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑኳ ኤርትራን መጎብኘታቸው ይታወሳል።

6፤ በደቡብ አፍሪካ የአሜሪካ አምባሳደር ሩበን ብሪጌቲ ደቡብ አፍሪካ ለሩሲያ ጦር መሳሪያዎችንና ተተኳሾችን ሰጥታለች በማለት ትናንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ መክሰሳቸውን የውጭ ዜና ወኪሎች ዘግበዋል። አምባሳደር ብሪጌቲ፣ ባለፈው ታኅሳስ "ሌዲ አር" የተባለች የሩሲያ መርከብ ደቡብ አፍሪካ ለሩሲያ የሰጠችውን ጦር መሳሪያ ከኬፕታውኑ ከደቡብ አፍሪካ ወደብ ጭና ወደ ሩሲያ ስለመጓጓዟ "አሜሪካ ርግጠኛ ናት" ማለታቸውን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። አምባሳደሩ አያይዘውም፣ ደቡብ አፍሪካ በሩሲያና ዩክሬን ጦርነት ላይ ይዠዋለኹ የምትለውን "ገለልተኛ አቋም" አለማክበሯ፣ የአሜሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣናትን "በእጅጉ አሳስቧል" በማለት ተናግረዋል ተብሏል። የአምባሳደሩን ውንጀላ ተከትሎ፣ የፕሬዝዳንት ሴሪል ራማፎዛ ጽሕፈት ቤት በጉዳዩ ላይ ገለልተኛ ምርመራ መጀመሩን አስታውቋል። አምባሳደሩ ውንጀላውን ያቀረቡት፣ ደቡብ አፍሪካ በሩሲያና ዩክሬን ጦርነት ላይ የያዘችውን አቋም ለአሜሪካ ባለሥልጣናት ለማስረዳት ልዐካን ቡድኗን ወደ ዋሽንግተን በላከች ማግስት ነው።

7፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ2211 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ3055 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 65 ብር ከ2287 ሳንቲም እና መሸጫው 66 ብር ከ5333 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ59 ብር ከ2366 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ60 ብር ከ4213 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። አንድ የቻይና ዩዋን ደሞ በ7 ብር ከ0728 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ7 ብር ከ2143 ሳንቲም ተሽጧል ተብሏል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
212 views17:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 07:32:06 ዓርብ ጠዋት! ግንቦት 4/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ ምርጫ ቦርድ ከሦስት ዓመታት በኋላ በመቀሌ የትግራይ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱን ትናንት እንደገና ከፍቶ ሥራ ማስጀመሩን ቪኦኤ ዘግቧል። ቦርዱ ወደ መቀሌ የላካቸው ባለሙያዎችም ከትግራይ ክልል ፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች፣ ከሲቪል ማኅበራት ተወካዮችና መገናኛ ብዙኀን ጋር እንደተወያዩ ዘገባው ጠቅሷል። ምርጫ ቦርድ የትግራይ ክልል ከሦስት ዓመታት በፊት በተናጥል ያካሄደውን ክልላዊ ምርጫ ውድቅ ያደረገ ሲኾን፣ በቀጣዩ ዓመት የክልልና የፌደራል ምክር ቤቶች ምርጫ እንደሚያካሄድ ሰሞኑን እንደተገለጠ ይታወሳል።

2፤ ጅዳ ውስጥ ንግግር ላይ የሰነበቱት ሁለቱ የሱዳን ተፋላሚ ወገኖች የሰብዓዊ ዕርዳታ መስመሮችን ለመክፈት ስምምነት ላይ መድረሳቸውን የውጭ ዜና ወኪሎች ዘግበዋል። ሁለቱ ወገኖች ሲቪሎችን ከጥቃት ለመጠበቅ እና ተዋጊዎቻቸውን ከሆስፒታሎችና ሌሎች ከአገልግሎት ሰጪ ተቋማት አካባቢ ለማስወጣትም እንደተስማሙ ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ኾኖም ተፋላሚዎቹ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ መድረስ አልቻሉም ተብሏል።

3፤ የተመድ ሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት በሱዳን ለተመድ ሰብዓዊ መብት ባለሙያ ተጨማሪ ሃላፊነቶችን ሰጥቷል። ተቆጣጣሪ ባለሙያው ባሁኑ ወቅት በአገሪቱ ጦር ሠራዊት እና ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት መካከል በቀጠለው ግጭት የሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ጭምር እንዱከታተሉና ሪፖርት እንዲያደርጉ ምክር ቤቱ አዟል። ምክር ቤቱ ግጭቱ ባስቸኳይ እንዲቆምና ሰብዓዊ ዕርዳታ ተደራሽ እንዲኾንም ጠይቋል። ምክር ቤቱ የውሳኔ ሃሳቡን ያጸደቀው፣ በ18 ድጋፍ፣ በ15 ተቃውሞ እና በ14 ድምጸ ተዓቅቦ ነው።

4፤ ኬንያ በግዙፎቹ ዳዳብ እና ካኩማ የስደተኛ መጠለያዎች የተጠለሉ ስደተኞች ወደ አገሬው ኅብረተሰብ እንዲቀላቀሉ ወስናለች። አዲሱ ፖሊሲ ስደተኞች ከመንግሥታዊ አገልግሎቶች እንዲያገኙ የሚያስችል ሲኾን፣ ዳዳብ እና ካኩማ መጠለያዎችም ወደ ማዘጋጃ ቤት ደረጃ እንደሚያድጉ የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የኬንያ መንግሥት ከ200 ሺህ በላይ ስደተኞች የሚገኙባቸው ሁለቱ መጠለያዎች የጸጥታ ስጋት እንደደቀኑ በመግለጽ፣ ጨርሶ እንደሚዘጋቸው ላለፉት ዓመታት ሲዝት እንደነበር ይታወሳል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
240 views04:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 20:04:18 ሐሙስ ምሽት! ግንቦት 3/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ ብሄራዊ ባንክ ለሳፋሪኮም ኩባንያ አካል ለኾነው ሳፋሪኮም ኤምፔሳ የሞባይል የፋይናንስ አገልግሎት ንዑስ ኩባንያ የገንዘብ መገበያያና መላላኪያ አገልግሎት "ኤምፔሳ" እንዲጀምር ፍቃድ ሰጥቷል። ሳፋሪኮም ኩባንያ በኢትዮጵያ የሞባይል ገንዘብ መገበያና መላላኪያ አገልግሎት ፍቃድ በማግኘት የመጀመሪያው የውጭ ኩባንያ ኾኗል። ኩባንያው የ"ኤምፔሳ" አገልግሎቱን ከተያዘው የአውሮፓዊያን ዓመት በፊት እንደሚጀምር የኬንያው ቢዝነስ ደይሊ ኩባንያውን ጠቅሶ ዘግቧል። ሳፋሪኮም ኬንያ ውስጥ "ኤምፔሳ" የጀመረው ከ15 ዓመታት በፊት ሲኾን፣ ባሁኑ ወቅት በኬንያና ሌሎች የአፍሪካ አገራት ከ50 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች አሉት።

2፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ለሚያስገነቡት አዲስ ቤተመንግሥት ተጨማሪ ሦስት ተቋራጮች መቅጠራቸውን ዋዜማ ከምንጮቿ ሰምታለች። የ"ጫካ" ፕሮጀክት አጠቃላይ ወጪው 49 ቢሊዮን ብር እንደሚደርስ ሲገለጽ የቆየ ሲኾን፣ የምዕራባዊያን ዲፕሎማቲክ ምንጮች ግን ወጪው 850 ቢሊዮን ብር ሊደርስ እንደሚችል በመናገር ላይ ናቸው። ፕሮጀክቱ በ503 ሔክታር ላይ የቅንጡ መኖሪያና መዝናኛ መንደሮችንና ሦስት ሰው ሠራሽ ሐይቆች ግንባታ ያካተተ ሲኾን፣ ግንባታው የሚካሄደው በየካ ክፍለ ከተማ የካ ተራራ ግርጌ ነው። የአዲስ አበባ መንገዶች ባለሥልጣን እስካኹን የ29 ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥ መንገድ ግንባታ አካሂዷል።

3፤ በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የተወሰኑ የግል ትምህርት ቤቶች በቀጣዩ ዓመት እናደርገዋለን ባሉት የተማሪዎች የትምህርት ክፍያ ዙሪያ ከወላጆች ጋርመግባባት ላይ መድረስ እንዳልቻሉ ሪፖርተር ዘግቧል። የትምህርት ክፍያ ጭማሪ ለማድረግ ከወሰኑት 1 ሺህ 253 ትምህርት ቤቶች መካከል፣ 1 ሺህ 31 ትምህርት ቤቶች ከወላጆች ጋር ባደረጉት ውይይት 20 በመቶ ጭማሪ ብቻ ለማድረግ መግባባት ላይ እንደደረሱ የከተማዋ የትምህርት ሥልጠናና ቁጥጥር ባለሥልጣን ዛሬ በሰጠው መግለጫ መናገሩን ዘገባው አመልክቷል። ባለሥልጣኑ የግል ትምህርት ቤቶች በቀጣዩ ዓመት ከወርሃዊ ክፍያ ውጭ በዓይነትም ኾነ በገንዘብ የክፍያ ጭማሪ ማድረግ አይችሉም ማለቱ ተገልጧል። የግል ትምህርት ቤቶች ከወላጆች ጋር የተወያዩት፣ ከ20 እስከ 100 ፐርሰን የሚደርስ ጭማሪ ለማድረግ መወሰናቸውን ለባለሥልጣኑ ማሳወቃቸውን ተከትሎ ነው።

4፤ የደቡብ ክልል ምክር ቤት የቁጫ ሕዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ተወካዮች የኾኑ ሦስት የክልሉ ምክር ቤት አባላትን ከግንቦት 1 ጀምሮ ከአባልነት መሰረዙን የጋሞ ዞን ኮምንኬሽን ቢሮ አስታውቋል። ሦስቱ የፓርቲው ተወካዮች ከምክር ቤቱ አባልነት የተሰረዙት፣ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ እና ምርጫ ቦርድ በፍርድ ቤት ሲያካሂዱት የቆዩትን ክርክር መሠረት በማድረግ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በቁጫ ምርጫ ክልሎች በድጋሚ ምርጫ እንዲካሄድ በወሰነው መሠረት መኾኑን ቢሮው ገልጧል። ከክልሉ ምክር ቤት አባልነት የተሰናበቱት የፓርቲው ተወካዮች፣ ጌዲዮን ጌታቸው፣ ማሳሞ ማዳልቾ እና ሊዲያ በለጠ ናቸው። በጋሞ ዞን በሁለት ወረዳዎች የሚኖረው የቁጫ ሕዝብ ለዓመታት ሲያነሳው የቆየውን የማንነትና ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄ ለፌደሬሽን ምክር ቤት ያስገባ ሲኾን፣ ምክር ቤቱ ግን እስካኹን በጥያቄው ላይ ውሳኔ አልሰጠም።

5፤ የተመድ ሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ልዩ ስብሰባ የሱዳኑ ግጭት ባስከተለው ሰብዓዊ መብት ተጽዕኖ ዙሪያ መክሯል። የተመድ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽነር ቮልከር ተርክ በምክር ቤቱ ልዩ ስብሰባ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ የታጠቁ ኃይሎች በሰላማዊ ሰዎች ላይ "ጾታዊ ጥቃትና ግድያ" እንደሚፈጽሙ ገልጸው፣ ተፋላሚዎች የጦርነት ሕግጋትን እንዲያከብሩ ጠይቀዋል። ተርክ፣ የሱዳን ጦር ሠራዊት በሰላማዊው ሕዝብ መኖሪያዎች ላይ የአየር ድብደባዎችን መፈጸሙንና ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊቱም በሲቪሎች ሠፈሮች መሸጎ እየተዋጋ መኾኑንም ገልጸዋል። በተፋላሚ ወገኖች ላይ ተጽዕኖ መፍጠር የሚችሉ አገራት ሀሉ ግጭቱ በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ ጥረት እንዲያደርጉ ተርክ ተማጽነዋል።

6፤ ሁለቱ የሱዳን ተፋላሚ ወገኖች ሳዑዲ ዓረቢያ ጅዳ ውስጥ ሲያደርጉት የሰነበቱት የቅድመ-ድርድር ንግግር አበረታች ውጤት ማሳየት መጀመሩን ሮይተርስ አደራዳሪዎችን ጠቅሶ ዘግቧል። ተፋላሚዎቹ ወገኖች በቅርቡ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ይደርሳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ዘገባው አመልክቷል። የጅዳውን ንግግር የሚመሩት፣ ሳዑዲ ዓረቢያ እና አሜሪካ ናቸው።

7፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ2167 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ3010 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 65 ብር ከ3270 ሳንቲም እና መሸጫው 66 ብር ከ6335 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ59 ብር ከ3890 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ60 ብር ከ5768 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
240 views17:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 13:46:48 ጥንቃቄ

የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በገበያ ላይ ባደረገው ቁጥጥር የኢትዮጵያ አስገዳጅ ደረጃንና የገላጭ ጽሑፍ መስፈርቶች ሳያሟሉ ተመርተው እየቀረቡ ያሉ ምርቶችን ህብረተሰቡ እንዳይጠቀም አሳስቧል፡፡

የተከለከሉት በአጠቃላይ 91 የተለያዩ የምግብ ምርት ዓይነቶች መሆናቸውን የባለስልጣኑ የሕዝብ የኮሙንኬሽ ዳሬክቶሬት ዳሬክተር አበራ ደመቀ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡

46 ዓይነት አይኦዳይዝድ ጨው፣ 27 ዓይነት የምግብ ዘይት፣ 10 ዓይነት ከረሜላ ፣5 ዓይነት አቼቶ 2 ዓይነት የለውዝ ቅቤ እና 1 የቫኔላ ፍሌቨር ምርቶችን  እንደሚገኙበትም ገልጸዋል፡፡

ባለስልጣን በገበያ ላይ ባደረገው ቁጥጥር የኢትዮጵያ አስገዳጅ ደረጃንና የገላጭ ጽሑፍ መስፈርቶች ስለማያሟሉ በተጨማሪም በቁጥጥር ወቅት የተገኙ ግኝቶች እንደሚያሳዩት ምርቶቹ በአብዛኛው በሚባል መልኩ የመጠቀሚያ ጊዜ፣ የአምራች ድርጅታቸው ሥም፣ አስገዳጅ ደረጃ ምልክት፣ መለያ ቁጥርም ሆነ አድራሻቸው ምርቱ ላይ ያልተገለጸና የሌላቸው በመሆኑ የተነሳ ነዉ፡፡

ምርቱ ሊይዛቸው የሚገቡ ንጥረ ነገሮች በውል ለማይታወቅ በተጨማሪም ከሚመለከታቸው የጤና  ተቆጣጣሪ አካላት ፍቃድ የሌላቸው በመሆኑ ህብረተሰቡ ጥቅም ላይ እንዳያውላቸው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ አሳስቧል፡፡

ለጥንቃቄ የምርቱ ዓይነትና የተገኙትን ክፍተቶች ይፋ በማድረግ ህብረተሰቡ በትኩረት ተመልክቶ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ባለስልጣን መስሪያቤቱ አሳስቧል፡፡

በዚህም መሠረት፦

የምርት ዓይነቶች እና ብራንድ ሥማቸው

  የምግብ ጨዉ

1.  ሳባ የገበታ ጨው(Saba IODIZED Salt)
2.  ንጋት የገበታ  ጨው(Nigat IODIZED SALT)
3.  አዲስ ብርሃን የገበታ ጨው  ADDIS BERHAN IODIZED SALT
4.  ሙና የገበታ ጨው(MUNA TABLE SALT)
5.  ቤዝ የገበታ ጨው/BASE IODIZED SALT
6.  ጉስቶ የገበታ ጨው/GUSTO IODIZED SALT
7.  ማክ የገበታ ጨው/MAK IODIZED SALT
8.  አባይ የገበታ ጨው/ABAY TABLE SALT
9.  መስቱራ ባለ አዮዲን የተፈጨ ጨው MESTURA REFINED & IODIZED SALT
10.  መነስ ጨው /MENES IODIZED SALT
11.  ሙሉ የገበታ ጨው /Mulu Table Salt
12.  ኢርኮ  አዮዳይዝድ  ጨው ERKO IODIZED SALT
13.  አርዲ የገበታ ጨው/ARDI IODIZED SALT
14.  ዘመን የገበታጨው/ZEMEN IODIZED SALT
15.  ዘመን የገበታጨው/ZEMEN IODIZED SALT
16.  ጨረቃ የገበታ ጨው/IODIZED SALT
17.  ፋና የገበታጨው/Fana Table Salt
18.  ዳናት የገበታጨው
19.  ሶም የገበታጨው/som iodized salt
20.  ጉግሳ በአዮዲን የበለፀገ የገበታጨው/GUGSA Iodised Salt
21.  ሸጋ ጨው/SHEGA Iodized SALT
22.  ፍዳክ የገበታ ጨው/FDAK IODIZED SALT
23.  ኡሚ የገበታ ጨው/UMI IODIZED SALT
24.  ጊዜ አዮዳይዝድ ጨው/GIZE IODIZED SALT
25.  ባማክ የገበታ ጨው/bamak Iodized Salt
26.  ማዚ የገበታ ጨዉ/MAZI IODIZED SALT
27.  አዲስ የገበታ ጨዉ/ADDIS Iodized Salt
28.  የገበታ ጨው/Iodized salt
29.  TANA TABLE SALT/ጣና የገበታ ጨው
30.  ጣና የገበታ ጨው
31.  ማኢዳ የገበታ ጨው/MAEEDA IODIZED SALT
32.  አሚን ጨው/Amin iodized salt
33.  ሆም የገበታ ጨው/HOME IODIZED SALT
34.  ጂኤም የገበታ ጨው/GM IODIZED SALT
35.  ገዳ አዮዳይዝድ የታጠበ የገበታ ጨው/ GEDA IODIZED SALT
36.  ዛማ አዮዳይዝድ የታጠበ ባለ አዮዲን ጨው /ZAMA SALT
37.  ሶሲ የአዮዲን ጨው/Sosi Iodized Salt
38.  ብቁ የገበታ ጨው/Biku iodized salt
39.  H.T.F TABLE SALT /ኤች.ቲ.ኤፍ
40.  AFRAN Iodized Salt
41.  ኤምሬት ጨው/Emirate IODIZED SALT
42.  ስፔሻል የገበታ ጨው/Special Iodized Salt
43.  ሊያ የገበታ ጨው/ LIYA IODIZED SALT
44.  አፊ ጨው/AFI IODIZED SALT
45.  ዩስራ ጨው/ YUSERA  SALT
46.  ቡዜ የገበታጨው/BUZE IODIZED SALT

የምግብ ዘይት

1.  ነጃ ንጹህ የምግብ ዘይት/ NEJA Pure Edible Oil
2.  ረና ንጹህ የምግብ ዘይት/ Rina Edible Pure Food Oil
3.  የኛ ንጹህ የምግብ ዘይት/Yegna Pure Edible Oil
4.  ኑራ  ንጹህ የምግብ ዘይት /Nura Pure Edible oil
5.  ሕይወት ንጹህ የምግብ ዘይት /HIWOT Edible Cooking Oil
6.  ሚድ ንጹህ የምግብ ዘይት /MID Pure Edible Oil
7.  ጉና ንጹህ የኑግ  የምግብ ዘይት/GUNA Pure Niger Edible Oil
8.  አዲስ  ንጹህ የምግብ  ዘይት
9.  ኑር ንጹህ የምግብ ዘይት/Nur Pure Edible Oil
10.  ኑራ ንጹህ የምግብ ዘይት/NuraPure Edible Oil
11.  ሶፊ ንጹህ የምግብ ዘይት/Sofi Pure Edible Oil
12.  ደሴት ንጹህ የምግብ ዘይት/Deset Pure Food Oil
13.  HADI COOKING OIL
14.  Arif cooking oil
15.  ሰነዓ ንፁህ የምግብ ዘይት /Senea pure food oil
16.  ቃል ንፁህ የምግብ ዘይት/Kale Pure Food Oil
17.  ናዲ የተጣራ ንጹህ የምግብ ዘይት/ Nadi pure food oil
18.  ሰላም ንፁህ የምግብ ዘይት/Selam pure food oil
19.  ኑኑ ንፁህ የምግብ ዘይት /Nunu pure food oil
20.  MIFTAH pure food oil
21.  ቤላ የተጣራ የኑግ ዘይት/BELLA Pure Niger Oil
22.  ጣዝማ ንፁህ የምግብ ዘይት
23.  ሚና ንፁህ የምግብ ዘይት
24.  ብሌን ንፁህ የምግብ ዘይት/Blen Pure  Edible Oil
25.  ደስታ የተጣራ የኑግ  ዘይት
26.  ሐዲ የተጣራ የምግብ ዘይት
27.  ሳራ የኑግ የምግብ ዘይት/Sara Niger Oil

የከረሜላ ምርቶች

1.  ማሂ ከረሚላ/Mahi candy
2.  ኢላላ ጣፋጭ  ከረሚላ/Elaala sweet candy
3.  ፋፊ  ሎሊፖፐ/Fafi lolipop
4.  ኢላላ  ሎሊፖፕ  ቢግ  ጃር/Elaala lolypop big jar
5.  ኮከብ ከረሚላ/KOKEB candy
6.  ከረሚላ
7.  ከረሚላ
8.  ኤም ቲ  ሎሊፖፕ/MT Loliipop
9.  ኤ.ኤ ከረሚላ/A.A candy
10.  ምንም ገለጭ ፁሑፍ የሌለው ከረሜላ

የአቼቶ ምርቶች

1.  ሮያል አቼቶ/Royal VINEGAR
2.  ዋልታ አቼቶ
3.  ሮያል  አቼቶ/ROYAL Vinegar
4.  ሌመን  አቼቶ/LEMEN ACETO
5.  ሸገር  አቼቶ/SHEGER ACETO

  የለዉዝ ቅቤ

#ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
249 views10:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 07:28:07 ሐሙስ ጠዋት! ግንቦት 3/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር በአሜሪካ ሎዛንጅለስ ከተማ ከሚኖሩ የኢትዮጵያዊያን አሜሪካዊያን ዲያስፖራ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር እንደሚወያዩ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል። አምባሳደር ሐመር፣ ከትናንት ጀምሮ እስከ ግንቦት 12 በከተማዋ በሚኖራቸው ቆይታ፣ ከአማራ፣ ኦሮሞ፣ ትግሬይና ሱማሊያ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማኅበረሰብ ተወካዮች እና ባጠቃላይ ከኢትዮዊያን አሜሪካዊያን ጋር እንደሚወያዩ መስሪያ ቤቱ ገልጧል። የአምባሳደር ሐመርና የኢትዮጵያዊያን አሜሪካዊያኑ ውይይት፣ በኢትዮጵያ መንግሥት እና ሕወሃት መካከል ፕሪቶሪያ ላይ በተደረሰው ሰላም ስምምነት አፈጻጸ፣ በሌሎች የኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች እንዲኹም የኢትዮጵያዊያን ሴቶችን አቅም በመገንባት ዙሪያ ያተኮረ እንደሚኾን መረጃው አመልክቷል።

2፤ በአዲስ አበባ በርካታ ትምህርት ቤቶች ከ20 እስከ 100 ፐርሰንት የሚደርስ የትምህርት ክፍያ ጭማሪ ለማድረግ የውሳኔ ሃሳብ ማቅረባቸውን "ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ዘግቧል። የከተማዋ የትምህርትና ሥልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን ግን፣ የትኛውም ትምህርት ቤት ከተማሪ ወላጆች ጋር ስምምነት ላይ ሳይደርስ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ እንደማይችል ማስጠንቀቁን ዘገባው ጠቅሷል። በከተማዋ ከሚገኙት 1 ሺህ 558 ትምህርት ቤቶች መካከል፣ በቀጣዩ ዓመት የትምህርት ክፍያ ጭማሪ ለማድረግ መወሰናቸውን ለባለሥልጣኑ ያሳወቁት፣ 1 ሺህ 257 ትምህርት ቤቶች እንደኾኑ ባለሥልጣኑ መናገሩን ዜና ምንጩ አመልክቷል።

3፤ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት በሱዳኑ ግጭት መጀመርያ ቀናት በፕሬዝዳንታዊ ጽሕፈት ቤቱ ላይ በፈጸመው ጥቃት የአገሪቱን ወታደራዊ መሪ ጀኔራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃንን ለመግደል ወይም እጃቸውን ለመያዝ ተቃርቦ እንደነበር ሮይተርስ ዘግቧል። ጀኔራል ቡርሃንም ክላሽንኮቭ አንስተው እንደተዋጉና በጥቂት ቀናቶች ውጊያ ከ30 በላይ የጀኔራል ቡርሃን የግል ጠባቂዎች እንደተገደሉ ከግል ጠባቂዎቻቸው መስማቱን ዜና ምንጩ ጠቅሷል። የፈጥኖ ደራሹ ሠራዊት ተዋጊዎች ባኹኑ ወቅት የአገር ውስጥ ጉዳይ፣ የፖሊስ መስሪያ ቤቱን እና ሌሎች ተቋማትን ሕንጻዎች ተቆጣጥረውና የካርቱም መውጫና መግቢያ መንገዶች ላይ ኬላዎችን አቁመው ቁጥጥር በማድረግ ላይ እንደሚገኙ ሮይተርስ ጨምሮ ዘግቧል።

4፤ የዲሞክራሲያዊት ኮንጎ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ፌሊክስ ቲሽስኬዴ በምሥራቃዊ ኮንጎ የሠፈረውን የምሥራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ ጦር አፈጻጸም ክፉኛ መተቸታቸውን የፈረንሳዩ ዜና ወኪል ዘግቧል። በቀጠናዊው ጦር እና በኮንጎ አማጺያን መካከል "መቻቻል ይታያል" ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ ባሁኑ ወቅት የቀጠናው ጦር እና አማጺው "ኤም-23" ባንድ ላይ እየኖሩ ነው ማለት ይቻላል ማለታቸውን ዘገባው ጠቅሷል። የቀጠናው ጦር በሰኔ ከኮንጎ ሊወጣ እንደሚችልም ፕሬዝዳንቱ ፍንጭ ሰጥተዋል ተብሏል። ካለፈው ኅዳር እስከ መጋቢት፣ ኬንያ፣ ቡሩንዲ፣ ኡጋንዳና ደቡብ ሱዳን ከአገሪቱ መንግሥት ጋር ወግነው አማጺዎችን ለመውጋት በምሥራቅ ኮንጎ ወታደሮቻቸውን ማስፈራቸው ይታወሳል። የደቡባዊ አፍሪካ ቀጠናዊ ማኅበረሰብ መሪዎች የቀጠናውን ጦር ለተመሳሳይ ተልዕኮ በምሥራቅ ኮንጎ ለማስፈር ሰሞኑን መወሰናቸው ይታወሳል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
259 views04:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 22:27:31
ሌብነት ባልጠበቅነው መልኩ ባህሪውን እየቀያየረ ብዙዎችን እያከሰረ ነው
የዛሬውን የአንድ ነጋዴ ገጠመኝ አንብቡት
."ዛሬ ሱቄ ኣንድ ሰው ሞባይል ሊገዛ ይመጣል እናም ሲመጣ የቤት መኪና ፣ ህፃን ልጁንና ለመውለድ የተቃረበች ሚስቱን ይዞ ነበር ....... እናም ሚስቱን መኪናው ውስጥ ኣስቀምጧት ህፃን ልጁን ይዞ ወደ ሱቄ ይገባና #iphone14  ስልክ ኣሳየኝ ብሎኝ ካሳየሁት በኃላ ዋጋውን ሲጠይቀኝ 165ሺ ኣልኩት እሱም እባክህ ሚስቴ ስላማራት ነው ቀንስልኝ ሲለኝ እሺ ብዬ 2ሺ ብር ስቀንስለት ተስማማን..............  ከዛም ባለቤቴን ከለር ላስመርጣት ብሎ ሶስት የተለያዩ ከለር ያላቸውን iphone 14 ስልኮች ልጁን ሱቄ ጥሎ ይዞ ወጣ............. ያው እኔም ልጁን እዛው ስለተውና እርጉዝ ሴት ስላየው ይመለሳል በሚል እሳቤ ሰጥቼው ትኩረቴን ሌሎች ደንበኞች ላይ ኣደረኩኝ............. ከዛም ብጠብቅ ምንም የለም  ወጣ ብዬ ስመለከትም መኪናዋም እነሱም የሉም ..............ከዛ ወደሱቅ ተመልሼ ፈላውን ስጠይቀው ከጎዳና ላይ ጠዋት ኣንስተውት ልብስ ገዝተውለት ፤ ፀጉሩን ኣሰሰተካክለው ፤ ገላውን ምናምን ኣጥበው እንዳመጡት ነገረኝ ማለት ነው" 165K * 3 = 495 ሺ አነደዱኝ ማለት ነው።
ከእኔ ተማሩ ለጥንቃቄ ይህንን መልዕክቴን #ሼር አድርጉ ተብላቹሃል።

ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
251 views19:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 20:08:54 ረቡዕ ምሽት!ግንቦት 2/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌደሬሽን (ኢሠማኮ) በሠራተኞች ጥያቄዎች ዙሪያ ከጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ጋር ለመወያየት ጥያቄ ማቅረቡን ሪፖርተር ዘግቧል። ኢሠማኮ፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ለመጣው የሠራተኛው የኑሮ ኹኔታ መፍትሄ ለመፈለግ "ብቸኛው አማራጭ ጠቅላይ ሚንስትሩን ማነጋገር ነው" ማለቱን ዘገባው ጠቅሷል። ኢሠማኮ፣ የሠራተኞች የደመወዝ ግብር እንዲቀነስ፣ ከታክስ ነጻ የደመወዝ ወለል ከ600 ብር ከፍ እንዲልና አነስተኛ የምግብ ፍጆታዎች ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ እንዲኾኑ ለገንዘብ ሚንስቴር ደብዳቤ መጻፉም በዘገባው ተመልክቷል። ኢሠማኮ በዓለም ወዛደሮች ቀን ላይ የሠራተኞችን ጥያቄ ለማስተጋባት የጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ የአዲስ አበባ አስተዳደር እንዳገደው መግለጡ ይታወሳል።

2፤ ምርጫ ቦርድ በትግራይና ምርጫ ባልተካሄደባቸው የሌሎች ክልሎች አካባቢዎች ለሕዝብ ተወካዮች እና የክልል ምክር ቤቶች ምርጫ ለማካሄድ ለመንግሥት የበጀት ጥያቄ አቅርቤያለሁ ማለቱን ሪፖርተር ዘግቧል። ቦርዱ ከትግራይ በተጨማሪ፣ በኦሮሚያ፣ አማራና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ለክልል እና ፌደራል ምክር ቤቶች ምርጫ ባልተካሄደባቸው የተወሰኑ የምርጫ ክልሎች በቀጣዩ ዓመት ምርጫ ለማካሄድ መወሰኑን መግለጡን ዘገባው ጠቅሷል። ቦርዱ በተጠቀሱት ክልሎች በሚገኙ ምርጫ ክልሎች በአገራዊው ጠቅላላ ምርጫ ወቅት ምርጫ ሳያካሂድ የቀረው፣ በጸጥታ መጓደልና በፖለቲካዊ ምክንያቶች እንደነበር በወቅቱ መግለጡ ይታወሳል።

3፤ መንግሥት "በሽብር ወንጀል" እፈልጋቸዋለኹ ያላቸው አንጋፋው ተቃዋሚ ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው ክስ ከተመሠረተብኝ ክሱን ለመከላከል ከአሜሪካ "ወደ አገር ቤት እመለሳለኹ" ማለታቸውን ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል። ልደቱ እስከ ትናንት ድረስ ክስ እንዳልተመሠረተባቸው ከጠበቃዬ ተረድቻለኹ ማለታቸውን የጠቀሰው ዘገባው፣ ባኹኑ ወቅት አሜሪካ ውስጥ የሕክምና ክትትል ላይ እንደኾኑ መግለጣቸውን ጠቅሷል። ልደቱ፣ መንግሥት የሽብር ክስ ሊመሠርትብኝ የፈለገው በፍራቻ ወደ አገሬ እንዳልመለስ ለማድረግ ነው ማለታቸውንም ዘገባው ጨምሮ አመልክቷል። የጸጥታና ደኅንነት ግብረ ኃይል፣ በውጭ የሚገኙ ተጠርጣሪዎችን ከዓለማቀፉ የፖሊስ ተቋም ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር ለማዋል ጥረት አደርጋለኹ ማለቱ ይታወሳል።

4፤ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከጅቡቲ ተያዘ የተባለውን የበይነ መረብ ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይን ጨምሮ በስድስት የሽብር ወንጀል ተጠርጣሪዎች ላይ 14 ተጨማሪ የምርመራ ቀናት መፍቀዱን "ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ዘግቧል። ችሎቱ የዋስትና ጥያቄውን ውድቅ ያደረገው፣ መርማሪ ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ ባስተባበሩት "የሽብር ድርጊት በርካታ ንጹሃን ዜጎች እንዲሞቱና ንብረት እንዲወድም ኾኗል" በማለት ያቀረበውን አቤቱታ ግምት ውስጥ በማስገባት እንደኾነ ዘገባው ጠቅሷል።

5፤ የሱዳን ጦር ሠራዊት በካርቱም ተከታይ የአየር ድብደባ መፈጸሙንና ውጊያው ተባብሶ መቀጠሉን የውጭ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት፣ የሱዳን አየር ኃይል በፕሬዝዳንታዊ ጽሕፈት ቤቱ ላይ የአየር ድብደባ ፈጽሟል በማለት ከሷል። በከተማዋ ሕግና ሥርዓት መፍረሱንና ዝርፊያ መንሠራፋቱንም የተለያዩ የዜና ምንጮች አመልክተዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የቱርኩ ፕሬዝዳንት ጣይብ ኤርዶጋን አገራቸው በተፋላሚ ወገኖች መካከል የሚካሄድ ኹሉን ዓቀፍ ንግግር ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ለሱዳን ጦር ሠራዊት ዋና አዛዥ ጀኔራል ቡርሃን በስልክ እንደገለጡላቸው ተዘግቧል። ኹለቱ ተፋላሚ ወገኖች የሰብዓዊ ዕርዳታ መስመሮችን ስለመክፈት ቅዳሜ'ለት ጅዳ ውስጥ የጀመሩት ንግግር፣ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ አልተቋጨም።

6፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ2086 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ2928 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 65 ብር ከ3068 ሳንቲም እና መሸጫው 66 ብር ከ6129 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ59 ብር ከ5048 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ60 ብር ከ6949 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
266 views17:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ