Get Mystery Box with random crypto!

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ) Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkun_zemede — Zemedkun Bekele (ዘመዴ)
የሰርጥ አድራሻ: @zemedkun_zemede
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.26K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-05-10 07:17:16 ረቡዕ ጠዋት! ግንቦት 2/2015 ዓ.ም የEMS ዋናዋና ዜናዎች

1፤ ሕገመንንግሥታዊ ሥርዓቱን ለመገልበጥ አሲረዋል ተብለው በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ 6 ግለሰቦች ላይ ትናንት መርማሪ ፓሊስ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 14 ተጨማሪ ቀናት እንዲሰጠው መጠየቁን የአገር ውስጥ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች በበኩላቸው፣ መርማሪ ፖሊስ ለመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ያቀረበውን ምክንያት ደግሞ አቅርቦታል በማለት፣ ችሎቱ ጥያቄውን እንዳይቀበል እንዲኹም የጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ክስ በመገናኛ ብዙኀን አዋጅ መሠረት እንዲታይ እንደጠየቁ ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ችሎቱ ግራ ቀኙን መርምሮ ዛሬ ውሳኔ ይሰጣል ተብሏል። ትናንት ችሎት ከቀረቡት መካከል፣ ጅቡቲ ላይ ተያዘ የተባለው የበይነ መረብ ጋዜጠኛው ጎበዜ ሲሳይ እና ረዳት ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቸው ይገኙበታል።

2፤ ዓለማቀፉ የፍልሰት ድርጅት እስካለፈው ሰኞ 15 ሺህ ከሱዳኑ ግጭት የሸሹ ሰዎች በመተማ በኩል ኢትዮጵያ መግባታቸውን በትዊተር ገጹ አስታውቋል። ድርጅቱ ወደ ኢትዮጵያ ለሚገቡ ሰዎች የተለያዩ ድጋፎችን እየሰጠ መኾኑን ገልጦ፣ ድጋፉን አጠናክሮ ለመቀጠል ግን ተጨማሪ የገንዘብ ዕርዳታ እንደሚፈልግ ገልጧል። ከሱዳን በመተማ በኩል የሚገቡት፣ ኢትዮጵያዊያን ተመላሾች፣ ሱዳናዊያን ስደተኞችና የሌሎች አገራት ዜጎች እንደኾኑ ድርጅቱ ቀደም ሲል ማስታወቁ ይታወሳል።

3፤ የሳፋሪኮም ኩባንያ የሞባይል መገበያያ ዘዴ "ኤምፔሳ" ገንዘብ ላኪዎች ስማቸውንና ስልክ ቁጥራቸውን ከገንዘብ ተቀባዩ እንዲደብቁ የሚያስችል አሠራር ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩን የኬንያው ቢዝነስ ደይሊ ድረገጽ ዘግቧል። ኩባንያው አዲሱን አሠራር የጀመረው፣ በ"ኤምፔሳ" ላይ የሚፈጸሙ የዲጂታል ማጨበርበርና የግል መረጃ ሥርቆት ወንጀሎችን ለመከላከል እንደኾነ መግለጡን ዘገባው አመልክቷል። ኾኖም የአዲሱ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ተጨማሪ የገንዘብ መላኪያ ታሪፍ እንደሚከፍሉ ተገልጧል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምኅረቱ፣ "ኤምፔሳ" ኢትዮጵያ ውስጥ አገልግሎቱን እንዲጀምር በቅርቡ ፍቃድ እንደሚሰጥ ባለፈው ሳምንት መናገራቸው ይታወሳል።

4፤ ዓለማቀፉ የፍልሰት ድርጅት ሱማሊያ ውስጥ በአስቸጋሪ ኹኔታ ውስጥ ለሚያልፉ በሺዎች ለሚቆጠሩ አፍሪካዊያን ፍልሰተኞች ከሰኔ በፊት 3 ሚሊዮን ዶላር ዕርዳታ እንደሚያስፈልገው ከትናንት በስቲያ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ድርጅቱ የገንዘብ ድጋፉን ካላገኘ፣ በሱማሊያ በኩል ወደ ባሕረ ሰላጤው አገራት ለሚሻገሩ በዓመት 50 ሺህ ያህል ፍልሰተኞች የምግብ፣ ሕክምናና ሕይወት አድን ድጋፎችን መስጠት እንደማይችልና ቦሳሶ እና ሐርጌሳ የሚገኙ ማዕከሎቹንም ለመዝጋት እንደሚገደድ ገልጧል። በሱማሊያ በኩል ወደ ባሕረ ሰላጤው አገራት የሚሻገሩት ሕገወጥ ፍልሰተኞች አብዛኞቹ ኢትዮጵያዊያን ናቸው።

5፤ የሱማሊያዋ ፑንትላንድ ወታደሮች "ደመወዝ አልከፈለንም" በማለት በራስ ገዟ መንግሥት ላይ ማደማቸውን ጋሮዌ ድረገጽ ዘግቧል። አድመኞቹ ወታደሮች የፑንትላንድ ዋና ከተማ ጋሮዌን መውጫና መግቢያ ከፊል መንገዶችንና ጋሮዌን ከቦሳሶ ወደብ ጋር የሚያገናኘውን አውራ ጎዳና መዝጋታቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ወታደሮቹ አድማ የመቱት፣ የሥልጣን ጊዜያቸውን ያጠናቀቁት የራስ ገዟ ፕሬዝዳንት አብዱላሂ ደኒ ከአካባቢ ምርጫና ከሕገመንግሥታዊ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ከተቃዋሚ ፖለቲከኞችና ከፌደራል መንግሥቱ ጋር ከፍተኛ ውጥረት በገቡበት ወቅት ላይ ነው። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
282 views04:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 20:22:31 ማክሰኞ ምሽት! ግንቦት 1/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በክልሉ የሚካሄደውን ግጭት በድርድርና በሰላማዊ አማራጭ ለመፍታት ዝግጁ መኾኑን ዛሬ የክልሉ ኮምንኬሽን ቢሮ ኃላፊ ኃይሉ አዱኛ ለአገር ውስጥ ጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ላይ መናገራቸውን ዶይቸቨለ ዘግቧል። ኾኖም የቢሮ ኃላፊው፣ ታንዛኒያ ውስጥ በፌደራል መንግሥቱ እና በአማጺው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት መካከል በቅርቡ ስለተካሄደው የመጀመሪያ ዙር የፊት ለፊት ድርድር ሂደትና ውጤቱ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ ቀጥተኛ መልስ ሳይሰጡ እንደቀሩ ዘገባው ጠቅሷል። ኹለቱ ወገኖች ቀጣይ ድርድር በማድረግ አስፈላጊነት ላይ እንደተስማሙ መግለጣቸው ይታወሳል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት የመንግሥት ጦር ትናንት በምዕራብ እና ምሥራቅ ሸዋ በኩል አዲስ ጥቃት ከፍቶብኛል ሲል ዛሬ ማለዳ ላይ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

2፤ ኢትዮጵያ የኬንያን የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት በመሳብ ከምሥራቅ አፍሪካ ቀጠና ኡጋንዳንና ታንዛኒያን በመብለጥ ቀዳሚውን ደረጃ መያዟን ደይሊ ኔሽን አስነብቧል። ከአንድ ዓመት በፊት በነበረው መረጃ፣ የኬንያ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ገበያ ያፈሰሱት ሙዓለ ንዋይ ከ600 ሚሊየን ዶላር በላይ ደርሶ እንደነበር ዘገባው ጠቅሷል። እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጠና የኬንያ ኩባንያዎች ቀጥተኛ የውጭ ኢንቨስትመንት መዳረሻ በመኾን ታንዛኒያ ቀዳሚዋ እንደነበረች ዘገባው አመልክቷል። ኢትዮጵያ የኬንያ ኩባንያዎች ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት መዳረሻ በመኾን የቀዳሚነቱን ደረጃ የያዘችው፣ የኬንያው ሳፋሪኮም የቴሌኮም ኩባንያ በኢትዮጵያ ሙዓለ ንዋዩን ማፍሰስ ከጀመረ ወዲህ ነው።

3፤ የግብጽ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሳሜ ሽኩሪ ዛሬ ጁባ መግባታቸውን የደቡብ ሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል። ሽኩሪ ጁባ የገቡት፣ የሱዳኑን ግጭት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት በሚቻልበት ኹኔታ ዙሪያ ከሱዳን ጎረቤት አገራት የሰላም ጥረቶችን ለማስተባበር እንደኾነ ሚንስቴሩ ገልጧል። ሽኩሪ ለሱዳኑ ግጭት መፍትሄ በማፈላለግ ዙሪያ፣ ከደቡብ ሱዳኑ አቻቸው እንዲኹም ከአገሪቱ ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ጋር ይወያያሉ ተብሏል።

4፤ በሱዳኑ ግጭት ሳቢያ ከመኖሪያቸው የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር ወደ 700 ሺህ ማሻቀቡን ዓለማቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት ዛሬ ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል። እስካለፈው ሳምንት ድረስ በግጭቱ የተፈናቀሉ ተፈናቃዮች ብዛት 334 ሺህ ገደማ የነበረ ሲኾን፣ ባለፉት ጥቂት ቀናት ግን ውጊያው ጋብ ማለቱን ተከትሎ በርካቶች የውጊያ ቀጠና ከኾኑ ቀየዎቻቸው እንደለቀቁ ተገልጧል። ከ100 ሺህ በላይ ሱዳናዊያን ደሞ ወደ ጎረቤት አገራት በተለይም ወደ ደቡብ ሱዳን፣ ቻድና ግብጽ እንደተሰደዱ ድርጅቱ በሪፖርቱ ጠቅሷል። ተፋላሚዎቹ የሰብዓዊ ዕርዳታ መተላለፊያ መስመሮችን ለመክፈት ጅዳ ውስጥ ቅዳሜ'ለት የጀመሩት ንግግር እንደቀጠለ ሲኾን፣ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ ንግግሩ ምን ውጤት እንዳስገኘ የታወቀ ነገር የለም።

5፤ በደቡባዊ ኬንያ ፖል ማካንዚ የተባለ የፕሮቴስታንት ሰባኪ "እየሱስ ክርስቶስን ለመገናኘት ራሳቸውን አስርበው እንዲሞቱ" ካደረጋቸው ከመቶ በላይ ተከታዮቹ የተወሰኑ አስከሬኖች ላይ አንዳንድ የሰውነት ክፍሎች እንደተወሰዱ በምርመራ መረጋገጡን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚንስትሩ ኪቱሪ ኩንዲኪ ድርጊቱን "በከፍተኛ ደረጃ የተደራጀ ወንጀል" በማለት እንደፈረጁት የጠቀሱት ዘገባዎቹ፣ ዛሬን ጨምሮ የሰባኪው ቤተክርስቲያን በሚገኝበት ጫካ በተደረገ አሰሳ 133 አስከሬኖች በጅምላ መቃብሮች ውስጥ እንደተገኙ አመልክተዋል። መርማሪ ፖሊስ፣ ድርጊቱ ከሰውነት ክፍሎች ንግድ ጋር የተያያዘና በርካታ ተዋናዮች የተሳተፉበት ወንጀል ሳይኾን እንደማይቀር መግለጡና፣ በሰባኪው ላይ የ"ሽብር ወንጀል" ክስ እመሠርታለኹ ማለቱ ተገልጧል። መንግሥት ወንጀሉን የሚመረምር ገለልተኛ ኮሚሽን አቋቁሟል።

6፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ2048 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ2889 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 65 ብር ከ5404 ሳንቲም እና መሸጫው 66 ብር ከ8512 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ59 ብር ከ8855 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ61 ብር ከ0832 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
285 views17:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 00:29:52
ሀሰት ነው ተባለ

#ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
66 views21:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 10:20:23
ተቀበሩ

የቤት ሰራተኛዋ አልተያዘችም እንድትያዝ ሼር አድርጉ እባካችሁ ተባበሩ



በቤት ሰራተኛ በጭካኔ ታርደው እና በእሳት ተቃጥለው ህይወታቸው አለፈ!!

በቡራዩ ቄራ አካባቢ የተሰማው መርዶ ለጆሮ ሰቅጣጭ ነበር

በፎቶው ላይ የምታይዋቸው የ12 አመቱ

* ናሖል ጌቱ እና
* የ5 አመቷ ታናሽ እህቱ ናኑ ጌቱ

ወላጅ እናታቸውን በሞት ያጡት የዛሬ ሁለት አመት ገደማ ነበር

አባታቸው ጌቱ የቡራዩ ቄራ ሰራተኛ በመሆኑ የስራው ባህሪይ ሌሊት ሌሊት ነው እንደተለመደው ትናንትም ልጆቹን ለቤት ሰራተኛዋ ትቶ ስራ ያነጋል

ይህቺ ሰራተኛ ግን ልጆቹን በጭካኔ አርዳ እና በእሳት ጭምር አቃጥላ ህይወታቸው እንዲያልፍ አድርጋለች

የቤት ስራተኛ ስሟ :- ነጋሴ ከበደ ነው

አልተያዘችም

እባካችሁ እንድትያዝ በሼር ተባበሩ እባካችሁ

ልጅ ያለው የልጁ፣ወንድምና እህት ያለው፣ የወንድሙና እህትን ነገር መቼም ትረዳላችሁና በእባካችሁ ገዳይ እንድትያዝ ለጓደኞቻችሁም ቢሆን #ሼር ብቻ እንድታደርጉልን ተብላቹሃል አደራ

ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
202 views07:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 22:26:45
ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ በፌዴራል ፖሊስ በቁጥጥር ስር ዋለ
ጋዜጠኛው ጅቡቲ ከገባ በኋላ ወደሌላ አገር ሊሻገር ሲል ከዓለም አቀፉ ፖሊስ እና ከጅቡቲ ብሔራዊ ፖሊስ ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር እንዲውልና ተላልፎ ለኢትዮጵያ እንዲሰጥ ተደርጎ ዛሬ ምሽት አዲስ አበባ መግባቱን የፌደራል ፖሊስ በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ አስነብቧል።

#ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
251 views19:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 19:37:34 የዲቪ 2024 እድለኛ አሸናፊዎች ይፋ ሆኑ!

አሜሪካ ኢትዮጵያ በሚገኘው ኢምባሲዋ በኩል ከሰሞኑ አመልካቾች ከአጭበርባሪዎች እንዲጠነቀቁ ማሳሰቧ ይታወሳል
የዲቪ 2024 እድለኛ አሸናፊዎች ይፋ ሆኑ።
ባሳለፍነው ጥቅምት እና ህዳር ወራት ላይ በበይነ መረብ አማካኝነት የተሞላው የ2024 ዲቪ ሎተሪ አሸናፊዎች መታወቃቸው ተገልጿል።
በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኢምባሲ የዲቪ 2024 ማመልከቻ የሞሉ ዜጎችም መመረጣቸውን እና አለመመረጣቸውን የፊታችን ቅዳሜ ማለትም ከሚያዚያ 28 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ማወቅ እንደሚችሉ ከሰሞኑ ማሳሰቡ ይታወሳል።
በዚህ መሰረትም አመልካቾች https://dvprogram.state.gov/ESC/ በዚህ ሊንክ በመግባት የዲቪ 2024 እድለኛ መሆን አለመሆናቸውን ማረጋገጥ እንደሚችሉ ተገልጿል።
ይህ በዚህ እንዳለም የድቪ ሎተሪ አሸንፋችኋል፣ ከአሜሪካ ኢምባሲ ነው እምንደውለው በሚል የሚያጭበረብሩ አካላት ስለሚኖሩ አመልካቾች እንዲጠነቀቁ ኢምባሲው ማሳሰቡ ይታወሳል።
አመልካቾች ዲቪ ሎተሪ ስለማሸነፋቸው በራሳቸው እና እጃቸው ላይ ባለው ሚስጢራዊ ቁጥር ብቻ ማረጋገጥ እንደሚችሉም ተገልጿል።
የ2023 ዲቪ ሎተሪ አሸናፊዎች እስከ ቀጣዩ መስከረም 2016 ዓ.ም ድረስ ብቻ ባሉት ቀናት ውስጥ እንደሚስተናገዱም ኢምባሲው በመግለጫው ላይ ጠቁሟል።
የ2022 ዲቪ ሎተሪ አሸናፊዎች በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት መከሰቱን ተከትሎ የአሜሪካ እና ኢትዮጵያ ግንኙነት በመሻከሩ ተጎድተናል ማለታቸው ይታወሳል።
ዲቪ ከደረሳቸው ኢትዮጵያዊያን መካከል አስተያየታቸውን ለአልዐይን የሰጡ የድቪ 2022 አሸናፊዎች በሁለቱ ሀገራት ግንኙነት መሻከር ምክንያት እድሉን ተጠቅመን ወደ አሜሪካ እንዳንሄድ ተደርገናል ብለውም ነበር።
በኢትዮጵያ ያለው የአሜሪካ ኢምባሲ በበኩሉ " የዲቪ ሎተሪ እድለኛ ተሆነ ማለት ቪዛ ይገኛል፣ ለቪዛ ቃለ መጠይቅም ይጠራል ወይም ቪዛ ይሰጣል ማለት አይደለም" ሲል በወቅቱ ምላሽ ሰጥቷል።
ነገር ግን የዲቪ ሎተሪ እድለኛ መሆን የቪዛ ጥያቄ ለማቅረብ የመጀመሪያው መስፈርት ነው ያለው ኢምባሲው እድለኞቹ አሁን ላይ የቪዛ አገልግሎት ሂደት ውስጥ ሳይገቡ ከቀረ በቀጣይ በሚደረጉ ተመሳሳይ የቪዛ አገልግሎት ውስጥ ሊካተቱ ይችላሉ ሲልም አክሎ ነበር።
አሜሪካ በየዓመቱ ከአፍሪካ፣ እስያ፣ አውሮፓ፣ ሰሜን አሜሪካ፣ ደቡብ አሜሪካ እና አውስትራሊያ 50 ሺህ ሰዎችን በድቪ ሎተሪ ወደ ሀገሯ ታስገባለች።
አፍሪካ የዚህ እድል ትልቁን ኮታ የምትሸፍን ሲሆን በዲቪ 2022 ፕሮግራም ግብጽ፣ አልጀሪያ እና ሱዳን እያንዳንዳቸው 6 ሺህ ሰዎች እድለኞች ሲሆኑ ሞሮኮ 4 ሺህ 138 ፣ ዲሞክራቲክ ኮንጎ 3 ሺህ 347 ፣ጋና 3 ሺህ 145 ፣ ኢትዮጵያ ደግሞ 2 ሺህ 988 ሰዎች የዲቪ እድለኛ እንደሆኑ ከተቋሙ ድረገጽ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል። መረጃውን #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
262 views16:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 19:27:12 የቅዳሜ ምሽት!ሚያዝያ 28/2015 ዓ.ም የEMS አጫጭር ዜናዎች

1፤ ኢዜማ ከመንግሥት ጋር ባለው ግንኙነት ላይ ጥናት እንዲያደርግ ያቋቋመው ግብረ ኃይል ሪፖርቱን ዛሬ ይፋ እንደሚያደርግ ዋዜማ ከምንጮቿ ሰምታለች። ሪፖርቱ፣ ፓርቲው ከመንግሥት ጋር የፈጠረው ትብብር ለአገሪቱ ምን ፋይዳ እንዳስገኘ ጭምር የሚዳስስ ሲኾን፣ የእስካኹኑን የፓርቲውን አካሄድ የሚያስቀጥል ወይም ሥር ነቀል የትግል መስመር ለውጥ እንዲደረግ ምክረ ሃሳብ እንደሚያቀርብ ይጠበቃል። ፓርቲው ጉዳዩን ለማስጠናት የወሰነው፣ ከመንግሥት ጋር የፈጠረው ቅርርቦሽ ለውስጣዊ አንድነቱና ኅልውናው ስጋት መፍጠሩን ተከትሎ ነበር። የኢዜማ መሪ ብርሃኑ ነጋ በመንግሥት በተሰጣቸው ሹመት ትምህርት ሚንስትር ኾነው እያገለገሉ ይገኛሉ።

2፤ የአማራ ክልል መንግሥት በክልሉ የሚገኙ አንዳንድ ኢመደበኛ አደረጃጀቶች "በመንግሥት ጸጥታ አካላት ላይ ትንኮሳ" በመፈጸም "የውጭና የውስጥ ኃይሎች መጠቀሚያ" ኾነዋል ሲል ዛሬ ባወጣው መግለጫ ከሷል። ፌደራል መንግሥቱ በአማራ ክልል ባኹኑ ወቅት እያካሄደው የሚገኘው የሕግ ማስከበር ርምጃ "በጣም ውስን" በኾኑ አካባቢዎች የሚካሄድ መኾኑን የጠቀሰው የክልሉ መንግሥት መግለጫ፣ ክልሉ "ሕዝባዊ እምቢተኝነት" ውስጥ አለመኾኑ ሊታወቅ ይገባል ብሏል። "የተሳሳተ ዓላማ ውስጥ" የገቡ "ጽንፈኛ ግለሰቦችና ቡድኖች" ከድርጊታቸው እንድትቆጠቡና "መንግሥት ያስቀመጣቸው የሰላም አማራጮች" ተጠቃሚ እንዲኾኑ የክልሉ መንግሥት አሳስቧል። መግለጫው አያይዞም፣ የሕግ ማስከበር ርምጃው በክልሉ ሰላም፣ ፍትሃዊ ልማትና ተጠቃሚነትን" ለማረጋገጥ ያለመ መኾኑን አውስቷል።

3፤ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ሸገር ከተማ ውስጥ የሚካሄደውን የመስጅዶች ማፍረስ ድርጊት እንዲያስቆም ለክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ደብዳቤ መጻፉን አስታውቋል። ምክር ቤቱ፣ የሸገር ከተማ አስተዳደር "የፈረሱ መስጅዶች በፍጥነት እንዲሰሩ" እንዲያደርግና የሙስሊሙን ኅብረተሰብ "በይፋ ይቅርታ መጠይቅ እንዳለበት" በደብዳቤው ላይ ማሳሰቡን ገልጧል። ምክር ቤቱ አስተዳደሩ አፈረሳቸው ያላቸውን አራት መስጅዶች በስም ዘርዝሯል።

4፤ ኢትዮጵያ በጀኔቫ በመካሄድ ላይ ላለው የተመድ ጸረ-ሥቅየት ኮሚቴ 76ኛ ጉባኤ ትናንትና ከትናንት ወዲያ ሪፖርቷን አቅርባለች። ኾኖም ኮሚቴው፣ በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት አያያዝ በተለይም የጸረ-ሥቅየት ሪፖርት ላይ ከሰሜኑ ጦርነት ጋር የተያያዙ በርካታ ትችቶችንና ጥያቄዎችን ማቅረቡን ኮሚቴው ካሰራጨው መረጃ ተመልክተናል። የጸረ-ሥቅየት ኮሚቴው አባላት፣ ኢትዮጵያ በምዕራብ ትግራይ ክልል ተፈጸሙ የተባሉ "የብሄር ማጽዳት" ወንጀሎችን"፣ "ከሕግ ውጭ የተፈጸሙ ግድያዎችን" እና "ሕገወጥ እስራቶችን" አስተባብላለች በማለት ከሰዋል። ኮሚቴው፣ ኢትዮጵያ በጦርነቱ ተፈጸሙ ለተባሉት ወንጀሎች "ተጠያቂነትን አላሰፈነችም"፤ "የኤርትራ ወታደሮች በጦርነቱ ስለመሳተፋቸው መረጃ አልሰጠችም"፤ ዓለማቀፍ ገለልተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት መርማሪዎች ወደ ጦርነቱ ቀጠና እንዳይገቡ ከልክላለች" በማለት ወቅሷል። የኢትዮጵያን ሪፖርት ያቀርበው የፍትህ ሚንስትር ደኤታ አለማንተ አግደው የመሩት ልዑካን ቡድንም ለኮሚቴው ጥያቄዎችና ትችቶች ምላሽ ሰጥቷል።

5፤ የሱዳን ጦር ሠራዊት እና ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት ጅዳ ውስጥ "ለሰብዓዊነት ዓላማ ተኩስ አቁም" ማድረግ በሚችልበት ኹኔታ ዙሪያ ዛሬ ፊት ለፊት ንግግር ይጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል። የሁለቱም ወገኖች ተወካዮች ጅዳ መግባታቸውን የውጭ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የፊት ለፊት ንግግሩን የሚያስተባብሩት ሳዑዲ ዓረቢያና አሜሪካ፣ ሁለቱ ወገኖች ወደተኩስ አቁም የሚያመራ ንግግር እንዲያደርጉና ግጭቱ በዘላቂነት እንዲቆም ከወዲኹ ባወጡት መግለጫ ተማጽነዋል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
236 views16:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 09:59:26 የቅዳሜ ዕረፋድ! ሚያዝያ 28/2015 ዓ.ም የEMS አጫጭር ዜናዎች

1፤ በጎንደር ከተማ በፋኖ ታጣቂዎችና መከላከያ ሠራዊት መካከል የተፈጠረውን ውጥረት ለማርገብ ያለመ ውይይት እንደተጀመረ መስማቱን ጠቅሶ ቪኦኤ ዘግቧል። ውጥረቱን ለማርገብ፣ በአካባቢው ሽማግሌዎች አመቻችነት በኹለቱ ወገኖች መካከል ትናንት ውይይት እንደተደረገ ዘገባው ጠቅሷል። በውይይቱ ከተነሱ ነጥቦች መካከል፣ ሰሞኑን ወደ ጎንደር የገባው መከላከያ ሠራዊት ከአካባቢው እንዲወጣና የፋኖ ታጣቂዎች አደረጃጀት እንዲቀጥል የሚሉት እንደሚገኙበት በውይይቱ የተሳተፉ የፋኖ አባላት መናገራቸው ተገልጧል። የክልሉ መንግሥትም ኾነ መከላከያ ሠራዊት ጎንደር ላይ ተደረገ ስለተባለው ውይይት፣ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ ያሉት ነገር የለም።

2፤ ሲዳማ ክልል ልዩ ኃይሉን ትናንት በይፋ ማፍረሱን ዶይቸቨለ ዘግቧል። የክልሉ ጸጥታ ቢሮ፣ የልዩ ኃይሉ አባላት ወደ ፌደራል እና ሌሎች የክልል ጸጥታ ተቋማት ተቀላቅለዋል ማለቱን ዘገባው አመልክቷል። የክልሉ መንግሥት በተንኳቸው ያላቸውን የክልሉ ልዩ ኃይል አባላት ብዛት ዘገባው አልጠቀሰም።

3፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ሦስት ሳምንታት ከ8 ሺህ በላይ ከፊል ሥልጠና የወሰዱ ሥራ ተቀጣሪ ዜጎችን ወደ ውጭ አገራት መላኳን የሥራ ፈጠራና ክህሎት ሚንስትር ሙፈሪያት ከሚል በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል። መንግሥት የውጭ አገር የሥራ ሥምሪት ዘርፉን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማዘመኑን ሚንስትሯ ገልጸዋል። ሰልጣኞቹ ተቀጣሪዎች ወደየትኞቹ አገሮች እንደተላኩ ግን ሙፈሪያት አልገለጡም። መንግሥት ለ500 ሺህ ተቀጣሪዎች ሥልጠና ሰጥቶ ወደውጭ አገራት በተለይም ወደ መካከለኛው ምሥራቅ አገራት ለመላክ እየተንቀሳቀሰ ስለመኾኑ በቅርቡ ተዘግቦ ነበር።

4፤ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ካርዲናል ብርሃነየሱስ ሱራፊኤል በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ፍትህ እና ካሳ እንዲሰጣቸው ጥሪ ማድረጋቸውን የቫቲካን ዜና ምንጭ ዘግቧል። ካርዲናል ብርሃነየሱስ እውነተኛ ሰላም ለማምጣት በጦርነቱ ተጎጂዎች መካከል ይቅርታ እንዲሰፍን መጠየቃቸውን ዘገባው ጨምሮ አመልክቷል። ካርዲናል ብርሃነየሱስ፣ ለተመላሽ ፍልሰተኞች፣ ለውስጥ ተፈናቃዮችና ኢትዮጵያ ውስጥ ለተጠለሉ ስደተኞች የክህሎት ሥልጠና ለመስጠት የተቋቋመው ዓለማቀፍ ፈንድ እያደረገ ስላለው እንቅስቃሴም ለዜና ምንጩ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ፈንዱን ከኹለት ዓመት በፊት ያቋቋሙት፣ የተለያዩ የሐይማኖት ተቋማት፣ የግል ኩባንያዎችና ዓለማቀፍ ድርጅቶች በጋራ በመኾን ነበር።

5፤ የሱዳን ጦር ሠራዊት በአገሪቱ የሰባዓዊ ዕርዳታ መስመሮችን ማስክፈት በሚቻልበት ኹኔታ ዙሪያ ከፈጥኖ ደራሹ ሠራዊት ጋር ለመነጋገር ተወካዮቹን ወደ ጅዳ ሳዑዲ ዓረቢያ እንደሚልክ አስታውቋል። በተያያዘ፣ የጦር ሠራዊቱ አዛዥ ጀኔራል ቡርሃን፣ ልዩ መልዕክተኛቸውን በቀጣዩ ሰኞ ወደ ደቡብ ሱዳን እንደሚልኩ ለፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ቃል እንደገቡላቸው የደቡብ ሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ገልጧል።
ፕሬዝዳንት ኪር ለግጭቱ ሰላም ለማፈላለግ ኢጋድ ያቋቋመው የመሪዎች ቡድን ሰብሳቢ ናቸው። ተፋላሚ ወገኖች ከሐሙስ ጀምሮ ለሰባት ቀናት ቃል የገቡትን ተኩስ አቁም እስከ ትናንት ሌሊት ድረስ አላከበሩም። #ሼር በማድረግ ተባበሩን
ሰናይ ቅዴ


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
250 views06:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 09:53:50 ከ258 ሚሊዮን በላይ ዓለም ሕዝብ ለአስከፊ የምግብ እጥረት መጋለጡ ተሰማ

ባለፈው የፈረንጆች ዓመት 2022 ከዓለም ሕዝብ አንድ አራተኛ የሚሆነው በአስከፊ የምግብ እጥረት ውስጥ ማለፉን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና በአውሮፓ ሕብረት በጋራ የተቋቋመው የዓለም አቀፍ የምግብ ቀውስ ሪፖርትና የሰብዓዊ ድርጅቶች ጥምረት አስታወቀ፡፡

በዚህም 258 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ ባለፈው ዓመት በአስከፊ የምግብ እጥረት መጋለጡን የገለጸው ተቋሙ፤ ይህ ቁጥር ከዓለም ሕዝብ ብዛት ሦስት በመቶ ይሸፍናል ብሏል፡፡

ለዚህም እንደ ምክንያት የተጠቀሰው የእርስ በርስ ግጭቶች፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሲሆን፤ በ58 አገራት የሚገኙ ከ258 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ ሰዎች አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል ነው የተባለው፡፡

በተለይ በሰባት አገራት ማለትም በሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ የመን፣ ቡርኪናፋሶ፣ ናይጄሪያ፣ አፍጋኒስታን እና ሄይቲ የተከሰተው የምግብ ቀውስ ከኹሉም የከፋ በመሆኑ ሰዎች በረሃብ ምክንያት መሞታቸው ተጠቅሷል፡፡

እንዲሁም በአፍሪካ ቀንድ የተከሰተው አስከፊ ድርቅ በቀጠናው ከፍተኛ የምግብ ቀውስ እንዲፈጠር አድርጓል ተብሏል፡፡

በተባበሩት መንግሥታት የዓለም የምግብ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ሲንዲ ማኬይን በምግብ ዋስትና እጦት የበርካታ ሰዎች ሕይወት ማለፉን ጠቅሰው፤ አሁንም አፋጣኝ እርዳታ ካላገኙ የበርካታ ሰዎች ሕይወት አደጋ ውስጥ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

ዳይሬክተሯ ችግሩ በተለይም ድሃ በሆኑ አገራት በእጅጉ አስከፊ የሆነ ደረጃ ላይ መድረሱን የገለጹ ሲሆን፤ የከፋ የምግብ እጥረት ችግር ባለባቸው ሰባቱ አገራት አጣዳፊ የምግብ ዋስትና እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል፡፡
#ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
235 views06:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 09:30:30
...ባል ና ሚስት በመሀላቸው ግጭት ተፈጥሮ አይነጋገሩም፡፡ ሁለቱም በረጅም ትዝታ ተውጠዋል፡፡ መጀመሪያ
ማውራት ሽንፈት መስሎ ስለታያቸው ሳይነጋገሩ መተኛ ሰአታቸው ደረሰ፡፡
ድንገት ግን ባል አንድ ነገር ትዝ አለው፡፡ ነገ በጠዋት የስራ ስብሰባ ለመታደም ወደ ሌላ ሀገር ለመሄድ በረራ አለው፡፡
ሁሌ ደሞ ወደ ስራ ሲሄድ እንቅልፋም በመሆኑ የምትቀሰቅሰው ሚስቱ ናት፡፡ የነገው ስብሰባ እንዳያመልጠው"
11 ሰአት ቀስቅሺኝ " ብሎ በአፉ መናገር ሞት መስሎ ታየው እና ወረቀት ላይ " ነገ የስራስብሰባ ስላለብኝ ወደ ሌላ ሀገር እበራለሁ፡፡
አደራ 11 ሰአት ላይ ቀስቂሺኝ" ብሎ በወረቀት ላይ ፅፎ እሷ የምታይበት ቦታ አስቀምጦላት ምንም ቃል ሳይተነፍስ ተኛ፡፡
ጠዋት ሰውየው ከእንቅልፉ ሲነቃ ከጠዋቱ 3 ሰአት ሆኖ በረራውም ስብሰባውም አምልጦታል፡፡ እንዴት እንደዛ አስጠንቅቄ ነግሪያት አትቀሰቅሰኝም?" ብሎ በጣም ተበሳጨ፡፡ ከአልጋ ለመነሳት ሲሞክር አንድ ወረቀት ኮመዲኖ ላይ ተቀምጦ አየ፡፡ " 11 ሰአት ሞልቷል ተነስ ስብሰባው እንዳያመልጥህ " የሚል ፅሁፍ ተፅፎበታል፡፡
➧ማነው ስተት የሰራው? ማነውስ ልክ?
➧ወዳጄ ሴትን ልጅ በተንኮልም ሆነ በፍቅር ልትበልጣት አትችልም፡፡ ዝምታ ደሞ መቼም መፍትሄ ሆኖ አያውቅም፡፡
ወዳጆቼ ነገሮችን በንግግር ለመፍታት ሞክሩ።
መቻቻልን ይስጠን

#በቅንነት share ያድርጉት

ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
253 views06:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ