Get Mystery Box with random crypto!

AddisWalta - AW

የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth — AddisWalta - AW A
የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth — AddisWalta - AW
የሰርጥ አድራሻ: @waltatveth
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 45.03K
የሰርጥ መግለጫ

This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.
For more updates please visit https://shorturl.at/ehosX https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-06-12 16:12:03

2.8K views13:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 15:18:02
በዱር እንስሳትና ውጤቶቻቸው ላይ የሚካሄድ ህገ ወጥ ንግድን መከላከል ላይ ያተኮረ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተጀመረ

ሰኔ 5/2015 (ዋልታ) የምስራቅ አፍሪካ አገራት የሚሳተፉበት በዱር እንስሳት እና የዱር እንስሳት ውጤቶቻቸው ላይ የሚካሄድ የወንጀል እና ህገ ወጥ ንግድን መከላከል ላይ ያተኮረ የአቅም ግንባታ ስልጠና በአዲስ አበባ ተጀመረ።

በዓለም አቀፍ የዱር እንስሳት ደህንነት ፈንድ እና በኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን አዘጋጅነት የሚካሄደውን ስልጠና በንግግር የከፈቱት የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኩመራ ዋቅጅራ የዱር እንስሳት ወንጀል ድንበር ዘለል እንደሆነና ከአጎራባች አገራት ጋር መተባበር እና መቀናጀት ወሳኝነት እንዳለው ገልጸዋል፡፡

በዚህም ከዓለም አቀፉ የዱር እንስሳት ደህንነት ፈንድ ጋር በመተባበር ከሰባት አገራት ለተውጣጡ ባለሙያዎች እና ኃላፊዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/pfbid02XFBy14EtkgidUMmwrtCXuhiK6j8LVCoVH6F97ZxcBeKMF7rKcwF997ib4nKMTUSRl
3.0K views12:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 13:46:07
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል 25 ሚሊዮን ብር የሚገመቱ የተለያዩ ድጋፎችን ለትግራይ ክልል አስረከበ

ሰኔ 5/2015 (ዋልታ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጥሬ ገንዘብን ጨምሮ 25 ሚሊዮን ብር የሚገመቱ ምርጥ ዘርና የምግብ እህል ድጋፎችን ለትግራይ ክልል አስረከበ።

ድጋፉን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ ፀጋዬ ማሞና የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና ግብርና ቢሮ ኃላፊ ማስረሻ በላቸው አስረክበዋል።

ድጋፉ 10 ሚሊዮን ብር ጥሬ ገንዘብና 15 ሚሊዮን ብር ግምት ያለው 2 ሺሕ ኩንታል ምርጥ ዘር፣ ዱቄትና ቦቆሎ መሆኑን የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ ፀጋዬ ማሞ ገልጸዋል።

የክልሉ ሕዝብና መንግስት ለትግራይ ክልል ያደረገው ድጋፍ የመጀመሪያ እንጂ የመጨረሻ አለመሆኑን ገልጸው በቀጣይ ክልሉን መልሶ ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት ድጋፍ እንደሚያደርጉም ተናግረዋል።

ድጋፉን የተረከቡት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች የተረከቡትን ድጋፍ በፍጥነትና በፍትሃዊነት ለተጠቃሚው እንደሚያደርሱ መግለጻቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ እያሱ አብረሃ (ዶ/ር) ለደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የተደረገው ድጋፍም የክልሉ ህዝብና መንግስት የትግራይ ህዝብ አለኝታ መሆኑን ያሳየበት እንደሆነ ገልጸዋል።
3.3K views10:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 13:16:21
ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ተሾሙ

ሰኔ 5/2015 (ዋልታ) ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ተሾሙ፡፡

ሌተናል ጄነራል ይልማ የቀድሞ የአየር መንገድ ቦርድ ሰብሳቢ ግርማ ዋቄን በመተካት የአየር መንገዱ ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው መሾማቸው ነው የተገለጸው፡፡

ሌተናል ጄነራል ይልማ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የስራ አመራር ቦርድ አባል ሆነው ሲያገለግሉ መቆየታቸው ተገልጿል፡፡

ግርማ ዋቄ ከፈረንጆቹ 2022 ጀምሮ የአየር መንገዱ ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ሲያገለግሉ መቆየታቸውን የአየር መንገዱ መረጃ አመላክቷል፡፡
3.2K views10:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 12:53:15
ጠ/ሚ ዐቢይ ከሶማሊያ እና ከኬንያ ፕሬዝዳንቶች ጋር ተወያዩ

ሰኔ 5/2015 (ዋልታ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ መሐሙድ እና ከኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ጋር ተወያዩ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር  ገጻቸው ዛሬ ጠዋት ከኢጋድ የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን ከሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ መሐሙድ እና ከኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ጋር ተገናኝቻለሁ ብለዋል።

ብዙ የጋራ ጥቅሞቻችንን እና ሥጋቶቻችንን ከግምት ውስጥ በማስገባት የጋራ ተግዳሮቶቻችንን በድል ለመወጣት ኢትዮጵያ ከእያንዳንዱ ሀገር ጋር ተቀራርባ ትሠራለች ሲሉም አመልክተዋል።
3.2K viewsedited  09:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 12:17:34
የቀድሞው የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ህይወታቸው አለፈ

ሰኔ 5/2015 (ዋልታ) የቀድሞው የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ሲልቪዮ ቤርሉስኮኒ በ86 ዓመታቸው ህይወታቸው አለፈ፡፡

ሲልቪዮ በርሉስኮኒ ጣሊያንን ከፈረንጆቹ 1994 እስከ 2011 በጠቅላይ ሚኒስትርነት አገልግለዋል፡፡

የጣሊያን ትልቁን የሚዲያ ኩባንያ የፈጠሩ ቢሊየነር ነጋዴ የነበሩት የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ሲልቪዮ ቤርሉስኮኒ ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለዩ ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

ቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ከኢንፌክሽን ጋር በተያያዘ በሚላን በሚገኝ ራፋኢል ሆስፒታል ህክምናቸውን ሲከታተሉ ቢቆዩም ዛሬ ህልፈታቸው ተሰምቷል፡፡
3.2K views09:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 12:07:40
የቀን 6፡00 ዜና ከ #ዋልታ_ቴቪ በቀጥታ ሰኔ 5/2015

https://fb.watch/l6CjVMbAH5/
3.1K views09:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 11:33:36
በቻይና በተካሄደ የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ድል ቀናቸው

ሰኔ 5/2015 (ዋልታ) በቻይና የላንዡ ከተማ በተካሄደ የወንዶች ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከአንደኛ እስከ ሰባተኛ ተከታትለው በመግባት አሸነፉ።

በሳምንቱ መጨረሻ በተለያዩ የዓለም አገራት በተደረጉ ዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ውድድሮች ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል።

ከእነዚህ የአትሌቲክስ ውድድሮች መካከል በ2023 የላንዡ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ በበላይነት የጨረሱ ሲሆን በተለይ በወንዶች መካከል በተደረገው ውድድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከ1ኛ እስከ 7ኛ ተከታትለው በመግባት ማሸነፍ ችለዋል።

በውድድሩ አትሌት ኃይለማርያም ኪሮስ በአንደኝነት ያጠናቀቀ ሲሆን አፈወርቅ መስፍን፣ ሃይማኖት አለው፣ ሃይሌ ለሚ፣ አባይነህ ደጉ፣ ዮሐንስ መካሻ፣ ዱበር አብዲሻ እንደየቅደም ተከተላቸው ከሁለተኛ እስከ ሰባተኛ ያለውን ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል።

በሴቶች ደግሞ አትሌት ለተብርሃን ሃይላይ በአንደኝነት ስታጠናቅቅ አትሌት ታደለች በቀለ ሁለተኛ ሆና ጨርሳለች።

በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ የማራቶን ውድድር የተካሄደ ሲሆን በሴቶች አትሌት ዝናሽ ደበበ በአንደኝነት ማጠናቀቋ ተመላክቷል።

በኔዘርላንድ በተካሄደ ግማሽ ማራቶን ውድድር ንግስቲ ሃፍቱ በአንደኝነት ስትጨርስ በዚህ ውድድር በወንዶቹ አትሌት ሃፍቱ ተክሉና አሸናፊ ኪሮስ ሁለተኛና ሦስተኛ ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል።

በአሜሪካ ኒዮርክ በተካሄደ የ10 ኪሎ ሜትር ውድድር ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሰንበሬ ተፈሪ የቦታውን ሰዓት በማሻሻል ጭምር አሸንፋለች።

በፈረንሳይ በተካሄደ 5 ሺሕ ሜትር ውድድር ደግሞ አትሌት መዲና ኢሳ የቦታውን ክብረ ወሰን ሰዓት በማሻሻል ጭምር ማሸነፉ ተገልጿል።
3.1K views08:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 11:16:21
በቻይና የሚማሩ ኢትዮጵያዊያን የሀገራቸውን የቱሪዝም ሃብቶች አስተዋወቁ

ሰኔ 5/2015 (ዋልታ) በቻይና ጂሊን ዩኒቨርሲቲ የሚማሩ ኢትዮጵያዊያን የሀገራቸውን የባሕልና የቱሪዝም ሐብቶች ለዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ማስተዋወቃቸው ተገለጸ።

ተማሪዎቹ የሀገራቸውን የባሕልና ቱሪዝም ሐብቶች ያስተዋወቁት በአካባቢው ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ጋር በመተባባር መሆኑም ተገልጿል፡፡

ዝግጅታቸውን ያቀረቡት በዩኒቨርሲቲው ዓመታዊ ፌስቲቫል ላይ መሆኑን በቻይና የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመላክታል፡፡

በማስተዋወቂያ ዝግጅቱ ላይም የኢትዮጵያን ባሕላዊ ምግቦች፣ የቱሪዝም መስኅቦችና አጠቃላይ የኢትዮጵያን ታሪክ በተለያየ ዘዴ ማቅረብ ተችሏል፡፡
3.1K views08:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 10:20:30
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ በኢጋድ አባል ሀገራት መደበኛ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ጅቡቲ ገቡ

ሰኔ 5/2015 (ዋልታ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ልዑካን ቡድናቸው በኢጋድ አባል ሀገራት መደበኛ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ጅቡቲ ገቡ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ14ኛው የምሥራቅ አፍሪካ በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) አባል ሀገራት ርዕሰ ብሔራት እና መንግሥታት መደበኛ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ጅቡቲ መግባቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መረጃ አመላክቷል።
3.3K viewsedited  07:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ