Get Mystery Box with random crypto!

AddisWalta - AW

የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth — AddisWalta - AW A
የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth — AddisWalta - AW
የሰርጥ አድራሻ: @waltatveth
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 44.14K
የሰርጥ መግለጫ

This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.
For more updates please visit https://shorturl.at/ehosX https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-07-24 19:51:10
በዓለም አቀፍ ደረጃ ፍትሃዊና ዘላቂ የምግብ ሥርዓት ለመፍጠር አዲስና ጠንካራ የግብርና ፋይናንስ ሞዴል ያስፈልጋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

ሐምሌ 17/2015(ዋልታ) በዓለም አቀፍ ደረጃ ፍትሃዊና ዘላቂ የምግብ ሥርዓት ለመፍጠር አዲስና ጠንካራ የግብርና ፋይናንስ ሞዴል ያስፈልጋል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጣሊያን ርዕሰ መዲና ሮም እየተካሄደ ባለው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምግብ ሥርዓት ጉባኤ ላይ ንግግር አድርገዋል።

በንግግራቸውም የአየር ንብረት ለውጥ በዓለም ላይ በተለይም በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በምግብ አቅርቦት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድሯል ብለዋል።
https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/683508483815484?ref=embed_post
2.2K viewsedited  16:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 19:17:12
አል ሂላል ለኪሊያን ምባፔ ያቀረበዉን ከፍተኛ ዋጋ የዝዉዉር ጥያቄ ፒኤስጂ መቀበሉ ተገለጸ

ሐምሌ 17/2015 (ዋልታ) የሳውዲዉ ቡድን አል ሂላል የፓሪስ ሴንት ዠርሜይን ፈረንሳዊ ኮከብ ኪሊያን ምባፔን ለማስፈረም ያቀረበውን ክብረወሰን የሆነ 300 ሚሊዮን ዩሮ የዝውውር ዋጋ ፒኤስጂ መቀበሉ ተገልጿል፡፡

በእግር ኳስ ታሪክ ዉዱን የ300 ሚሊዮን ዩሮ ክፍያ ለመፈፀም ጥያቄ አቅርበዉ በፒኤስጂ ተቀባይነት አግኝቷልም ተብሏል።

እስካሁን በምባፔ እና በአል-ሂላል መካከል ምንም አይነት ድርድር ያልተደረገ ሲሆን ባለቤት ክለቡ ግን ተጫዋቹ ኮንትራቱን ካላራዘመ ለመሸጥ መወሰኑም ነው የተነገረው፡፡

በሀብታሙ ገደቤ
2.5K viewsedited  16:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 19:00:59
ዋልታ #ምሽት - ሐምሌ 17/2015 https://fb.watch/l_mrrmKLte/
2.3K views16:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 18:23:33
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አዲስ እና ጠንካራ ዓለም አቀፍ የግብርና የፋይናንስ ሞዴል እንደሚያስፈልግ ገለጹ

ሐምሌ 17/2015 (ዋልታ)አዲስ እና ጠንካራ ዓለም አቀፍ የግብርና የፋይናንስ ሞዴል መኖር አስፈላጊ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ።

በሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት የምግብ ስርዓት ጉባኤ ወቅት ባደረጉት ንግግር ለምግብ ዋስትና፣ ለስራ እድል ፈጠራ ብሎም ለአጠቃላይ የኢኮኖሚ እድገት አዲስ እና ጠንካራ ዓለም አቀፍ የግብርና የፋይናንስ ሞዴል አስፈላጊ መሆኑን በአፅኖት ተናግረዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ የትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት “ኢትዮጵያ ውስጥ ከፖሊሲ እና ስትራቴጂዎች ባለፈ የግብርና ልማትን ለማጎልበት አቅምን ማሳደግ፣ በምግብ ራስን መቻልን ማረጋገጥ ብሎም የአየር ንብረት ለውጥን ለመዋጋት ዋና ዋና ግቦችን ይዘን በርካታ ጅምር ስራዎችን እየሰራን ነው” ብለዋል።

ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት የምግብ ስርዓት ጉባኤ ከሐምሌ 17-19 በጣሊያን አዘጋጅነት እየተካሄደ ነው፡፡
2.7K views15:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 18:11:19
በበጀት ዓመቱ ከ6ሺሕ በላይ የሳይበር ጥቃት ሙከራዎች መደረጋቸው  ተገለጸ

ሐምሌ 17/2015 (ዋልታ) በበጀት ዓመቱ 6ሺሕ 959 የሳይበር ጥቃቶች መደረጋቸውን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር አስታወቋል፡፡

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የ2015 በጀት አመት አፈጻጸምን አስመልክቶ መግለጫ ሠጥቷል።

የአስተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር ሠለሞን ሶካ በ2015 የበጀት ዓመት በኢትዮጵያ 6ሺሕ 959 የሣይበር ጥቃት መመዝገቡንና ከዚህ ውስጥ 6ሺሕ 768ቱ የጥቃት ሙከራዎች መሆናቸውን ገልፀው የተቀሩት 191 ግን የተሣኩ የሳይበር ጥቃት መሆናቸውን ተናግረዋል።
https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/683457737153892?ref=embed_post
2.5K viewsedited  15:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 18:02:25
ዋልታ #አመሻሽ - ሐምሌ 17/2015 https://fb.watch/l_iY2rd5CR/
2.4K views15:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 17:38:39

2.6K views14:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 17:14:20
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ የጣሊያን፣ የጅቡቲ፣ የሶማሊያ እና የኬንያ የመሪዎች ስብሰባን ተሳተፉ

ሐምሌ 17/2015(ዋልታ)ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ኢትዮጵያን ጨምሮ የጣሊያን፣ የጅቡቲ፣ የሶማሊያ እና የኬንያ የመሪዎች ስብሰባ ላይ ተሳትፈዋል።

ስብሰባው በሀገራቱ መካከል የተቀናጀ ትብብር እንዲኖር የጋራ በሆኑ ጉዳዮች እና ፍላጎቶች ላይ ለመማከር የተዘጋጀ መሆኑን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
2.9K viewsedited  14:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 16:35:40
"የሩሲያ - አፍሪካ አጋርነትና ግንኙነት ጠንካራ ጥልቅ እና ፅኑ በመተማመን እና በበጎ ፈቃደኝነት ላይ መመስረቱ መለያው ነው፡፡" የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን

ሐምሌ 17/2015 (ዋልታ) "የሩሲያ- አፍሪካ አጋርነትና ግንኙነት ጠንካራ ጥልቅ እና ፅኑ በመተማመን እና በበጎ ፈቃደኝነት ላይ መመስረቱ መለያው ነው፡፡" ሲሉ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ገልጸዋል፡፡

በሩሲያዋ ቅዱስ ፒተርስበርግ ከተማ ሐምሌ 20 እና 21 ሁለተኛው የሩሲያ -አፍሪካ የኢኮኖሚና የሰብዓዊ ፎረም ይካሄዳል፡፡ፎረሙን አስመልተው የሩሲያው ፕሬዝንት ቭላድሚር ፑቲን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በላኩት ፅሁፍ በርካታ ርዕሰ ጉዳዮችን የዳሰሱ ሲሆን በዋናነት አገሮች እና አህጉራዊ ተቋማት ከሩሲ ጋር ስለሚኖራቸው ኢኮኖሚያዊ ማህበራዊ የሰው ኃይል ልማት በዓለም አቀፍ መድረክ ስለሚኖራቸው ትብብር እና መደጋገፍ ሰፊ ፅሁፍ አቅርበዋል፡፡

የሩሲያ እና አፍሪካ ወዳጃዊ ግንኑነትን አስመልክተው ፕሬዝዳነቱ እንደገለጹት "በሩሲያና በአፍሪካ መካከል ያለው የአጋርነትና ግንኙነት ጠንካራ ጥልቅ እና ፅኑ በመተማመን እና በበጎ ፈቃደኝነት ላይ መመስረቱ መለያው ነው " ብለዋል፡፡
https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/683408460492153?ref=embed_post
3.2K views13:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 16:04:33
400 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር በቁጥጥር ስር ዋለ

ሐምሌ 17/2015 (ዋልታ) መነሻውን ከጅቡቲ ወደብ አድርጎ መዳረሻውን ወረታ ከተማ ለማድረግ የተንቀሳቀሰው 400 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ የጫነ ተሳቢ ተሽከርካሪ ከታሰበው ቦታ ሳይደርስ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጸ።

ህገ ወጥ ድርጊቱ የተፈፀመው በባህርዳር ከተማ ሰባታሚት ቀበሌ ሐምሌ 16 ቀን 2015 ዓ.ም ሲሆን ከሌሊቱ 6 ሰዓት የአፈር ማዳበሪያ በህገ ወጥ መንገድ ለግለሰቦች ሲያከፋፍል በህብረተሰቡ ጥቆማ መያዙን የሰባታሚት ቀበሌ ፖሊስ ኦፊሰር ኮንስታብል ዮሐንስ ጥላሁን ተናግረዋል።

አብዛኛው ማዳበሪያ ሳይራገፍ ከነተሽከርካሪው መያዝ ቢቻልም ከ140 ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ለግለሰቦች በህገ ወጥ መንገድ መሰራጨቱን ፖሊስ ባደረገው ክትትል ደርሶበታል።

ፖሊስ ባደረገው ቤተ ለቤት ፍተሻ ከተሽከርካሪው ተራግፎ በግለሰቦች ቤት የተከማቸ በርካታ የአፈር ማዳበሪያ አግኝቷል።

89 ኩንታል ማዳበሪያ በአንድ ግለሰብ ቤት ተከማችቶ የተገኘ ሲሆን 24 ኩንታል ማዳበሪያ ደግሞ በአንድ ግለሰብ ቤት በአልጋ ስር እና በኩሽና ተከዝኖ መገኘቱን ከክልሉ ግብርና ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

አሽከርካሪው ግለሰብ በህግ ቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራ መሆኑን ፖሊስ የገለፀ ሲሆን ህብረተሰቡ እንደዚህ አይነት ህገ ወጥ ተግባርን እንዲያወግዝም ጠይቋል።
3.2K views13:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ