Get Mystery Box with random crypto!

AddisWalta - AW

የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth — AddisWalta - AW A
የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth — AddisWalta - AW
የሰርጥ አድራሻ: @waltatveth
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 45.03K
የሰርጥ መግለጫ

This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.
For more updates please visit https://shorturl.at/ehosX https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-07-24 15:44:41
ሀገሬ

የሀገር በቀል ዕውቀት በየሞች መንደር---

በሠራዊት ሸሎ

ሐምሌ 17/2015(ዋልታ) አገር በቀል ዕውቀት ለማህበረሰብ ዕድገትና ለውጥ እንዲሁም ለሳይንስና ቴክኖሎጂ ምጥቀት መነሻ ወይም መሠረት መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ።

ለአንድ አገር ዕድገት ባህላዊ ወይም አገር በቀል ዕውቀት ያለው ሚና ቀዳሚ ሰለመሆኑም ይወሳል።

የአገር በቀል ዕውቀት ማህበረሰቡ የዕለት ተዕለት ኑሮን ለመምራት በሚያደርገው የእንቅስቃሴ ሂደት የሚገኝ ልምድ ወይም ክህሎት ሲሆን ሰዎች በኑሮ ዘየአቸው የሚለማመዱትና ወጤት የተመዘገበበት የለውጥ ምንጭ ነው።

የአገር በቀል ዕውቀተ በግብርና ፣በህክምና፣በዕደ ጥበብ፣ በሥነ ህንፃና በሌሎች ሳይንሳዊ ግኝቶች እንደመነሻ ሆኖ እንዳገለገለም ይጠቀሳል።

የአገር በቀል ዕውቀት በሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር ሲታገዝና ገቢራዊ ሲደረግ ለፈጣን ዕድገትና ለውጥ መንገድ ስለመሆኑም አብዛኛዎቹ የሚስማሙበት ሀቅ ነው።https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/683385503827782?ref=embed_post
3.2K views12:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 13:16:37
የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች ቀይ ጨረቃ ማህበር በጎርፍ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች የአይነት ድጋፍ አደረገ

ሐምሌ 17/2015(ዋልታ) የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች ቀይ ጨረቃ ማህበር በጎርፍ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች ከ100 ሺህ ዶላር በላይ የሚገመት የአይነት ድጋፍ አደረገ።

ድጋፉን በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች ኢምባሲ ምክትል አምባሳደር ሚስተር ሱዑድ አልቱናይጁና ለአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አይደሩስ ሀሰን አስረክበዋል።

ማህበሩ ድጋፉን ያደረገው በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኢሜሬትስ ኢምባሲ በኩል ነው።

የተደረገው ድጋፍ ዱቄት፣ ሩዝ፣ የህፃናት አልሚ ምግብ እና ዘይት ሲሆን፤ ይህ በገንዘብ ሲተመን ከ100 ሺህ ዶላር በላይ እንደሚሆን መገለጹን ኢዜአ ዘግቧል።
3.9K views10:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 12:03:43
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከእስራኤል ግብረ-ሰናይ ድርጀት ጋር የመግባቢያ ስምምነት አደሱ

ሐምሌ 17/2015 (ዋልታ) የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሴቭ ዘ ችልድረንስ ኸርት (save the children’s heart) ከተባለ የእስራኤል ግብረ-ሰናይ ድርጀት ጋር የመግባቢያ ስምምነት አድሰዋል፡፡

የመግባቢያ ስምምነቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በፈረንጆቹ 2014 የተፈረመ ሲሆን ለ28 ዓመታት የሚቆይ እንደሆነም ተገልጿል፡፡

ስምምነቱ በልብ ህመም የሚሰቃዩ ህፃናትን ለመታደግ የሚውል የህክምና ድጋፍ እንዲሁም ለባለሙያዎች ልምድ ለማካፈል የሚያስችል እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ህፃናት ወደ እስራኤል ሀገር በመጓዝ ዎልፍሰን ሜዲካል ሴንተር በተሰኘ ማዕከል ውስጥ የልብ ህክምና የሚያገኙበትን ሂደት ለማመቻቸት የሚያግዝ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

እስካሁንም 1000 የሚሆኑ ህፃናት በዚሁ ማዕከል ውስጥ የልብ ህክምና ማግኘታቸው በመድረኩ ተመላክቷል፡፡

ዩኒቨርስቲው ለሚያደርገው የህፃናት የልብ ህክምና ሆስፒታሉ ያሉበትን ችግሮች ለማሻሻል እና ለመፍታት እንደሚያግዝም ነው የተገለፀው፡፡

በመቅደስ የኔሁን
4.0K views09:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 12:02:46
የቀን 6፡00 ዜና ከ #ዋልታ_ቴቪ በቀጥታ ሐምሌ 17/2015 https://fb.watch/lZZWGdRnj6/
3.6K views09:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 10:46:20 WALTA TV pinned a photo
07:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 10:45:09
ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ!

ዋልታ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኮርፖሬት ከዚህ በታች ለተመለከቱት ክፍት የሥራ መደቦች አመልካቾችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡
4.2K views07:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 10:34:20
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ

ሐምሌ 17/2015(ዋልታ) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት 16ኛ መደበኛ ጉባኤውን ዛሬ በአሶሳ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።

የክልሉ ርዕሰ-መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን የጽህፈት ቤታቸውን የ2015 በጀት የስራ አፈጻጸም ዝርዝር ሪፖርት ለምክር ቤቱ ያቀርባሉ።

የክልሉ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት በበጀት ዓመቱ ያከናወኗቸው ስራዎች ሪፖርት በምክር ቤቱ ለውይይት የሚቀርቡ አጀንዳዎች ናቸው።

የክልሉ የ2016 በጀት ዓመት አጠቃላይ የመደበኛ እና ካፒታል በጀት ረቂቅ አዋጅም በምክር ቤቱ ቀርቦ ይፀድቃል ተብሎም ይጠበቃል።

በተጨማሪም የክልሉ የአስፈጻሚ አካላት አደረጃጀት ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ በክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና በርዕሰ መስተዳድሩ የሚቀርቡ የዳኞች እና ሌሎች ሹመቶችን ምክር ቤቱ መርምሮ እንደሚያጸድቅ ለጉባኤው ከተዘጋጀው መርሐ-ግብር ማወቅ ተችሏል። መረጃ የክልሉ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ነው።
3.9K views07:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 10:10:04
በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ፈተና የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የሚያስችል ዝግጅት ተደርጓል-የሀረሪ ትምህርት ቢሮ

ሐምሌ 17/2015 (ዋልታ) በክልሉ በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ፈተና የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን የሀረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቋል፡፡

የክልሉ የትምህርት ቢሮው ኃላፊ ሙክታር ሳሊህ ባለፈው ዓመት በክልሉ ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 10 ነጥብ 5 በመቶ የሚሆኑት ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የሚያስገባቸውን ውጤት ማስመዝገባቸውን ጠቅሰው በዘንድሮው አመትም ከባለፈው አመት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በትኩረት ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል።

የቢሮ ኃላፊው ተማሪዎች ሰፊ ሰዓታቸውን ለትምህርታቸው እንዲሰጡ በማድረግ የማብቃትና የመደገፍ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል።

በተለይም ከመደበኛ የትምህርት ጊዜ ባሻገር በተቃራኒ ፈረቃ እና በእረፍት ቀናት የማጠናከሪያ ትምህርት ሲሰጥ መቆየቱን ጠቁመው ሞዲል ፈተናዎችን በመስጠትና የቤተመፅሐፍት ጊዜን በማሳደግ እንዲሁም ሌሎች ድጋፎች ሲደረገ መቆየቱን ተናግረዋል።

ከዚህ ባሻገር ከወላጆች ጋር ውይይት የማድረግና ተማሪዎችን በስነምግባር የማዘጋጀት ስራ ሌላው ትኩረት ተሰጥቶት ሲሰራ የቆየ ተግባር መሆኑን አብራርተዋል።

በክልሉ በሚገኙ 14 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 2510 ተማሪዎች የዘንድሮውን የ12 ክፍል ብሔራዊ ፈተና እንደሚወስዱ ነው ኃላፊው የተናገሩት።
https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/683259340507065?ref=embed_post
4.1K views07:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-05 11:14:47
ኢትዮጵያ እና ጅቡቲ ምሳሌ የሚሆን ወዳጅነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸው ተጠቆመ

ሰኔ 28/2015 (ዋልታ) ኢትዮጵያ እና ጅቡቲ ለቀጣናው ሀገራት ምሳሌ የሚሆን ታሪካዊ ወዳጅነት ያላቸው ሀገራት ናቸው ሲሉ የኢፌዲሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ብርቱካን አያኖ ተናገሩ።

የኢትዮ ጅቡቲ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ ፎረም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ሲሆን በመድረኩ ሚኒስትር ዴኤታዋ ሁለቱ ሀገራት በንግድ፣ ትራንስፖርት፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮች የተሳሰሩ ሀገራት ናቸው ብለዋል።

የሁለቱ ሀገራት የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ታሪካዊ እና በጠንካራ ወዳጅነት ላይ የተመሰረተ መሆኑንም አንስተዋል፡፡

የጅቡቲ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ልዑክ የኢትዮጵያ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ ተሻለ ምዕራፍ ያሸጋገረ እንደሆነም አመልክተዋል።

የምስራቅ አፍሪካ በይነ መንግስታት ድርጅት (ኢጋድ) ተወካይ የምስራች ብናልፈው በበኩላቸው ኢጋድ በህብረቱ አባል ሀገራት መካከል ያለ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ውህደትን ያበረታታል ሲሉ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ እና ጅቡቲ ዘርፈ ብዙ የሚያስተሳስራቸው ነገር እንዳለ ጠቅሰው ኢትዮ ጅቡቱ የባቡር ትራንስፖርት ቀዳሚው መሆኑን አንስተዋል።

112 አባላትን የያዘ የጅቡቲ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ ልዑክ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል።

በመስከረም ቸርነት
157 viewsedited  08:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-05 10:40:52
አዲሱ የኢቢሲ ሚዲያ ኮምፕሌክስ ዛሬ በይፋ ይመረቃል

ሰኔ 28/2015 (ዋልታ) አዲሱ የኢቢሲ ሚዲያ ኮምፕሌክስ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ዛሬ በይፋ ይመረቃል።

በአዲስ አበባ ሸጎሌ አካባቢ የተገነባው ዘመናዊ የሚዲያ ኮምፕሌክስ ተቋሙ በአፍሪካ ብሎም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስችለዋል ተብሏል።

በተራራ የተከበበው እና በእፅዋት ያጌጠው አዲሱ የሚዲያ ኮምፕሌክስ ዓለም በደረሰበት የሚዲያ ቴክኖሎጂ የተደራጁ ስቱዲዮዎችም ያሉት መሆኑ ተመላክቷል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ለሚዲያው ሠራተኞች ምቹ የሥራ ከባቢን በመፍጠር ተቋማዊ አፈፃፀም እንዲያድግ ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

ኢቢሲ "ለኢትዮጵያ ልዕልና" በሚል መሪ ቃል በአዲሱ የሚዲያ ኮምፕሌክሱ በሁሉም ሚዲየሞቹ አዳዲስ ይዘቶችን እና አቀራረቦችን አካቶ ወደ አድማጭ ተመልካች ለመድረስ ዝግጅቱን ማጠናቀቁም ከኢቢሲ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
637 views07:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ