Get Mystery Box with random crypto!

AddisWalta - AW

የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth — AddisWalta - AW A
የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth — AddisWalta - AW
የሰርጥ አድራሻ: @waltatveth
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 45.03K
የሰርጥ መግለጫ

This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.
For more updates please visit https://shorturl.at/ehosX https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-06-12 09:44:08
ልሂቃንና የፖለቲካ ፓርቲዎች በአገራዊ ምክክር ሂደት በንቃት ሊሳተፉ እንደሚገባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ

ሰኔ 5/2015 (ዋልታ) በአገራዊ ምክክሩ ሂደት ልሂቃን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሁሉም ባለድርሻ አካላት በንቃት ሊሳተፉ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስታወቀ።

የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ መብራቱ አለሙ (ዶ/ር) የአገራዊ ምክክሩ አላማ በማያግባቡ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ተመካክሮ ችግሮችን መፍታትና ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥ መሆኑን ገልጸዋል።

አገራዊ ምክክሩ ስኬታማ እንዲሆን ደግሞ ልሂቃን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ሲቪል ማኅበረሰቦች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ መንግሥት፣ የተለያዩ ማህበራትና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት በንቃት ሊሳተፉ እንደሚገባ አስረድተዋል።

አገሪቱ በተለያዩ ግጭቶች እንደማለፏ የምክክሩ ፋይዳ የጎላ ነው ያሉት ሰብሳቢው ዕውነተኛ ምክክር ለማድረግ ሁሉን አሳታፊና እና ተጨባጭ ውጤት ላይ ያተኮረ ሊሆን ይገባል ብለዋል።

https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/pfbid02gj4ZzFh3FjKghXf1dJchL2bybbWjPKdLf7b4RSwFHwYCvAEq2CEk4tLq7i74MzUTl
3.7K views06:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 19:37:40

4.3K views16:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 19:34:30

4.1K views16:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 19:46:41

1.9K views16:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 19:04:27
የሰኔ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል

ግንቦት 28/2015 (ዋልታ) የሁሉም ነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከግንቦት 29 ቀን ጀምሮ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ በግንቦት ወር ሲሸጥ በነበረው ዋጋ እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

በዚሁ መሠረት ፡-
1. ቤንዚን ………………………………………ብር 69.52 በሊትር
2. ነጭ ናፍጣ………………………………….ብር 71.15 በሊትር
3. ኬሮሲን ……………………………………...ብር 71.15 በሊትር
4. የአውሮፕላን ነዳጅ ………………………ብር 65.35 በሊትር
5. ቀላል ጥቁር ናፍጣ…………………………ብር 57.97 በሊትር
6. ከባድ ጥቁር ናፍጣ………………………….ብር 56.63 በሊትር የሚሸጥ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡
2.4K views16:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 18:20:22

2.3K views15:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 18:18:01

2.2K views15:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 18:03:09
ዋልታ ከአመሻሽ እስከ ምሽት - ሰኞ 28/9/2015

https://fb.watch/kZIGFq4vIE/
2.1K views15:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 16:54:30
በስፖርት ጉዳት ህክምና ላይ ያተኮረ የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ ነው

ግንቦት 28/2015 (ዋልታ) በባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር አዘጋጅነት ለህክምና ባለሙያዎች በስፖርት ጉዳት ህክምና ላይ ያተኮረ ስልጠና በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ እየተካሄደ መሆኑ ተገለጸ።

ስልጠናው እየተሰጠ ያለው ከስፔን ዩንቨርስቲ እና ስፔን ላሊጋ ከመጡ በዘርፋ ልምድ እና እውቀት ባላቸው የፊዝዮትራፒ እና የህክምና ባለሙያዎች አማካኝነት ነው።

በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የስፖርት ህክምና ዴስክ ኃላፊ ዮናስ አለማየሁ ስልጠናው የባለሙያዎች የስፖርት ህክምና ሳይንስ ንግንዛቤ ለማሳደግ፣ የህክምና ቁሳቁስ ድጋፎችን ማግኘትና የልምድ ልውውጥ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል ።


በስልጠናው የስፖርት ጉዳትን በመከላከል ፣ በስፖርት ጉዳት ህክምና ፣ በአመጋገብ እንዲሁም የህክምና ቁሳቁስን በመጠቀም ስፖርተኞች በፍጥነት ከጉዳት ማገገም በሚችሉበት ዙሪያ ትኩረት ያደርጋል ተብሏል።

በስልጠናው ከተለያዩ ሆስፒታሎች የመጡ የህክምና ባለሙያዎች ፣ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፣ በፕሪሚየር ሊግ ክለቦች የሚሰሩ የህክምና ባለሙያዎች እና ሌሎች ለሙያው ቅርበት ያላቸው ባለሙያዎች እየተሳተፉ መሆናቸውን ባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር በማህበራዊ የትስስር ገጹ አስታውቋል፡፡
2.6K views13:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 16:37:26
ግምቱ ከ355 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃ በቁጥጥር ስር ዋለ

ግንቦት 28/2015 (ዋልታ) ከግንቦት 18 እስከ 24/2015 በተደረገው ክትትል ግምታቸው ከ355 ሚሊዮን ብር በላይ የሆኑ የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

2 መቶ 54 ሚሊዮን የገቢ እና 101 ነጥብ 8 ብር የወጭ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር የዋሉት በኮሚሽኑ የተለያዩ ቅርንጫፍ ጽህፈት አማካኝነት መሆኑም ተገልጿል፡፡

አልባሳት፣ ነዳጅ፣ የቁም እንስሳት፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ቡና፣ መድሀኒት፣ ተሽከርካሪዎች፣ የመዋቢያ እቃዎች የጦር መሳሪያዎች፣ ጫት፣ አደንዛዥ እጾች፣የምግብ ዘይት እና የተለያዩ ሀገር ገንዘቦች በቁጥጥር ስር ከዋሉት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል ናቸው፡፡

የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ በጉምሩክ ኮሚሽን ሰራተኞች፣ በፌደራል ፖሊስ፣ በክልል ፖሊስ አባላትና ህብረተሰቡ ባደረጉት የጋራ ጥረት በፍተሻ፣ በበረራና በጥቆማ መያዙ ነው የተገለጸው፡፡

የኮንትሮባንድ እቃዎቹን ሲያዘዋዉሩ የተገኙ ሶስት ግለሰቦች እና አራት ተሽከርካሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑን ኮሚሽኑ በማህበራዊ የትስስር ገጹ ባወጣው መረጃ አስታውቋል፡፡

የኮንትሮባንድ እና ህገወጥ ንግድ በረቀቀ ሁኔታ የሚፈጸም እና በባህሪው ተለዋዋጭ በመሆኑ ድርጊቱን ለመግታት ሁሉም ባላድርሻ አካላትና ህብረተሰቡ የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል፡፡
2.5K views13:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ