Get Mystery Box with random crypto!

ልሂቃንና የፖለቲካ ፓርቲዎች በአገራዊ ምክክር ሂደት በንቃት ሊሳተፉ እንደሚገባ የፖለቲካ ፓርቲዎች | AddisWalta - AW

ልሂቃንና የፖለቲካ ፓርቲዎች በአገራዊ ምክክር ሂደት በንቃት ሊሳተፉ እንደሚገባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ

ሰኔ 5/2015 (ዋልታ) በአገራዊ ምክክሩ ሂደት ልሂቃን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሁሉም ባለድርሻ አካላት በንቃት ሊሳተፉ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስታወቀ።

የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ መብራቱ አለሙ (ዶ/ር) የአገራዊ ምክክሩ አላማ በማያግባቡ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ተመካክሮ ችግሮችን መፍታትና ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥ መሆኑን ገልጸዋል።

አገራዊ ምክክሩ ስኬታማ እንዲሆን ደግሞ ልሂቃን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ሲቪል ማኅበረሰቦች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ መንግሥት፣ የተለያዩ ማህበራትና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት በንቃት ሊሳተፉ እንደሚገባ አስረድተዋል።

አገሪቱ በተለያዩ ግጭቶች እንደማለፏ የምክክሩ ፋይዳ የጎላ ነው ያሉት ሰብሳቢው ዕውነተኛ ምክክር ለማድረግ ሁሉን አሳታፊና እና ተጨባጭ ውጤት ላይ ያተኮረ ሊሆን ይገባል ብለዋል።

https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/pfbid02gj4ZzFh3FjKghXf1dJchL2bybbWjPKdLf7b4RSwFHwYCvAEq2CEk4tLq7i74MzUTl