Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-MAGAZINE

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE
ርዕሶች ከሰርጥ:
Update
Silver
Platinum
Golden
Cloudbridge
Traininginstitute
Samitech
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 196.23K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን 251913134524

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 234

2022-06-01 11:10:02 #ጤናረቡዕ (ክፍል 2)

ርዕስ ፦ የአንጀት ማይክሮባዮምና ጤናማ አንጀት

[ ክሮንስ እና ኮላይተስ ኢትዮጵያ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የሚያቀርብ ]

የአንጀት ማይክሮባዮም በትሪሊዮን የሚቆጠሩ በአንጀት ክፍል ውስጥ የሚኖሩ ረቂቅ ተሕዋስያን ናቸው። እነዚህ  ረቂቅ ተሕዋስያን ጠቃሚ ባክቴሪያዎችን ብቻ ሳይሆን ፈንገሶች፣ጥገኛ ነፍሳት እና ቫይረሶችን ያካትታሉ።

በአንጀት ውስጥ የሚገኙ ጠቃሚ ረቂቅ ተሕዋሲያን ለጤናችን ወሳኝ ለሆኑት በርካታ ተግባራት ተጠያቂ ናቸው፡፡

እያንዳንዳችን ከወላጆቻችን፣ ወንድሞቻችን ወይም እህቶቻችን ወይም የባህር ማዶ ጓደኞቻችን ለየት ያለ የአንጀት ማይክሮባዮም መጠን እና የጤና ሁኔታ  አለን ፡፡

ጤናማ የሆነ የማይክሮባዮም መጠንን ለማጠናከር የአንቲባዮቲክ መድሃኒቶችን አወሳሰድ ማስተካከል ( ሀኪም ያዘዘውን መድሀኒት ብቻ መውሰድ) አንዱ መንገድ ነው።

ስለ የአንጀት ማይክሮባዮም፣ ጠቀሜታቸውንና ይበልጥ ለማጠናከር የሚረዱ የጤና ምክሮችን በ #InstantView ያንብቡ https://telegra.ph/Gut-Microbe--Healthy-Gut-05-31 ያንብቡ።

በጉዳዩ ላይ ለሚኖሮት ጥያቄ፣ ምክርና አስተያየት በስልክ +251965662501 ይደውሉልን ወይም በቴሌግራም @IBDETHIOPIA ላይ ይጻፉልን።

#ዕሮብንለአንጀትጤና

@tikvahethmagazine @ibdeth
23.3K views08:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-01 11:08:38
#WeeklyUpdate

ባሳለፍነው ሳምንት 102 ነጥብ 8 ሚሊዮን የገቢ ኮንትሮባንድ እቃዎች እና 26 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የወጭ ኮንትሮባንድ እቃዎች በተለያዩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶቹ መያዙን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

የገቢ ኮንትሮባንድን በመቆጣጠር ረገድ ቀዳሚውን ስፍራ የሚይዙት ሞያሌ፣ አዲስ አበባ ኤር ፖርት ፣ እና አዲስ አበባ ቃሊቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ሲሆኑ በቅደም ተከተላቸው 37 ነጥብ 9 ሚሊዮን ፣ 16 ነጥብ 7 ሚሊዮን እና 14 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የኮንትሮባንድ እቃዎችን መያዝ ተብሏል፡፡

በቁጥጥር ስር ከዋሉት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል አልባሳት፣ነዳጅ፣ የቁም እንስሳት፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ቡና፣ መድሀኒት ፣ተሽከርካሪዎች፣ የመዋቢያ እቃዎች የጦር መሳሪያዎች፣ጫት፣ አደንዛዥ እጾች፣የምግብ ዘይት እና የተለያዩ ሀገር ገንዘቦች ይገኙበታል፡፡

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
19.2K viewsedited  08:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-01 11:08:17
ዱባይ ጎልደን ቪዛ ለኢትዮጵያውያን ባለሀብቶች እና ቤተሰቦቻቸው...

እጅግ ቅንጡ ቤቶችን በመሪነት በመገንባት የሚታወቀው ሾባ ሪአልቲ ለ10 ዓመት የመኖሪያ ፈቃድ ጎልደን ቪዛ የሚያሰጠውን በዱባይ ያለውን ቅንጡ እና አመቺ የሆነውን መኖሪያ ቤት ፖርትፎሊዮ እድትጎበኝ ይጋብዝሃል።

አንተን ለመሰሉ ስኬታማ ሰዎች በልክ የተሰራች የምትመስለው የአለማችን ቅንጡዋ ከተማ ዱባይ ላንተ ብዙ አማራጭ አቅርባለች

ይህ ብዙዎች እየተሻሙበት ያለ እድል እንዳያመልጥህ ፍላጎትህን በቴሌግራም አካውንታችን አሳውቀን @Bilt_Lij ህልምህ እውን እንዲሆን የተለያዩ የብድር አማራጮችን ይዘን እንጠብቅሃለን...

መልክትህን ለመላክ:
ዌብ ሳይታችንን ጎብኝ: https://www.biltlij.com/
በቴሌግራም ለመነጋጋር: https://t.me/bilt_lij
በዋትስአፕ ለመነጋገር: https://wa.link/y2j9af
ወይም ለመደወል፡ +97152989 8575
18.0K viewsedited  08:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-01 11:08:17
Register at https://www.effsaa.org/short-term-training-program-registration-form/ after the settlement of the training fee.
Venue
At the training hall of Ethiopian Freight Forwarders and Shipping Agents Association (EFFSAA) which is located at Kazanchis, Nigist Towers Hotel & Apartments 4th Floor (In front of Elilly International Hotel)
For More Information,
Call us at +251 115 589045 / +251 903 182525
OR
Visit our telegram channel
https://t.me/EFFSAAOfficial
19.1K viewsedited  08:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-31 23:11:33 #የዛሬ (23/2014)

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል፤ በጋምቤላ ክልል በአኙዋ ብሔረሰብ ዞን በዲማ ወረዳ፤ በአማራ ክልል በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ጓንጓ ወረዳ 8 ቀበሌዎች በደቡብ ክልል አማሮ ልዩ ወረዳ በሁሉም ቀበሌያት በሰብሎች ላይ #ተምች መከሰቱ ተገልጿል። በአብዛኞቹ አከባቢዎች ተምቹ በሰብሉ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርስ እንደሚችል ተሰግቷል።

የኢትዮጵያ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ህወሃት " የኤርትራ ጦር ጥቃት ከፈተ " በሚል የሚያሰራጨው መረጃ ትክክል አይደለም ብለዋል። በኤርትራና በህወሃት መካከል ግጭት እንዲፈጠር ያደረገው እራሱ ህወሃት ነው ሲሉም ተናግረዋል። ትላንት ህወሓት ባሰራጨው መረጃ ባለፈው ቅዳሜ እና እሑድ የኤርትራ ሠራዊት በሽራሮ ጥቃት ከፍቶ እንደነበር እንዲሁም ከ4 ቀን በፊት በአዲአዋላ ውጊያ መደረጉን አሳውቆ ነበር።

ሮይተርስ ዛሬ ይዞት በወጣው ዘገባ ባለፈው ሳምንት የመጨረሻ ቀናት ላይ የኤርትራ ጦር በሽራሮ ከተማ ላይ በከፈተው ጥቃት አንዲት የ14 ዓመት ታዳጊ መገደሏን እና 18 ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን አመልክቷል።

የሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት መቋጫ ያገኝ እና አስተማማኝ ሰላም ይሰፍን ዘንድ ጥረት እያደረጉ የሚገኙ የአፍሪካ ሕብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የቀድሞ ናይጄሪያ ፕሬዜዳን ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ ትግራይ ክልል ይገኛሉ። ኦባሳንጆ እና ዶ/ር ደብረፅዮን በቀጠናዊ ጉዳዮች ጋር መምከራቸው የተነገረ ሲሆን ምክክሩን የተመለከተ ዝርዝር መረጃ ይፋ አልሆነም።

በናይጄሪያ አንድ የ40 ዓመት ጎልማሳ በዝንጀሮ ፈንጣጣ / Monkeypox መሞቱን የሀገሪቱ የበሽታ መቆጣጠሪያ ማዕከል (NCDC) ትላንት ምሽት አስታውቋል። በናይጄሪያ ከሚገኙት 36 ግዛቶች ዘጠኙ የዝንጀሮ ፈንጣጣ (MonkeyPox) ተመዝግቦባቸዋል። በሌላ በኩል በኮንጎ በ2022 9 ሰዎች በበሽታው መሞታቸው ሪፖርት መደረጉን ዋሽንግተን ፖስት አስነብቧል።

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የቀጠለ ሲሆን ፤ በግንቦት 23/2014 ዓ/ም ውሎ የደቡብ ክልል ፕሬዝደንት እና ሌሎች የክልሉ የሥራ ኃላፊዎች በምልዓተ ጉባኤው ተገኝተው በቤተክርስቲያን ላይ በየጊዜው እየደረሱ ባሉ ችግሮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል። በክልሉ ያሉ ችግሮች በደብዳቤ ንባብ እንዲሁም በክልሉ በሚገኙ ሊቃነ ጳጳሳት አማካይነት የቃል ጥያቄ ቀርቦ ምላሽ እንዲያገኙም ተጠይቋል። የክልሉ ፕሬዝደንት የተፈጠሩትን ችግሮች ለመፍታት አስተዳደሩ እያደረጋቸው ያሉ ጥረቶችን አስረድተው፥ በየደረጃው ለመፍታት እንደሚሠሩ ገልፀዋል።

ዛሬ በኦሮሚያ ክልል በሰበታ ከተማ 100 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር የፈጀ የኮካኮላ ምርት ማምረቻ ፋብሪካ ተመርቋል። ፋብሪካው በዓመት 100 ሚሊየን በላይ እሽግ ለስላሳ ለማምረት ያስችለዋል የተባለ ሲሆን የማምረቻ ግብዓቶችን በማምረትም ከውጪ ወደ ሀገሪቷ የሚገቡ ምርቶችን ይቀንሳልም ተብሏል። ኮካ ኮላ " ሚኒት ሜድ " የተሰኙ የጁስ ምርቶቹን ወደ ኢትዮጵያ ገበያ እያመጣ መሆኑን ዛሬ በነበረው የፋብሪካው ምረቃ ሥነ-ስርአት ላይ ተሰምቷል።

በደሴ ከተማ አራዳ ክፍለ ከተማ ትላንት ከምሽቱ 5:30 አካባቢ በተለምዶ ሙጋድ አካባቢ በተነሳው መንስዔው ያልታወቀ የእሳት ቃጠሎ 6 ሰዎች ከመጎዳታቸው በተጨማሪ 24 መኖሪያ፣7 የንግድና ድርጅት ቤቶች ከእነ ሙሉ ንብረታቸው ሙሉ በሙሉ መውደማቸውን ፖሊስ አረግጧል። በቃጠሎው በከባድ መሳሪያ ተተኳሽ ቅሪቶች ምክንያት በከፍተኛ ሁኔታ የነበረው ፍንዳታ ህዝብ እንዳይጠጋ መሠናክል ሆኖበት አምሽቷል ተብሏል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
26.8K viewsedited  20:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-31 21:29:50
#Jimma

የጅማ ዩኒቨርሲቲ የአደጋ ግዜ አስቸኳይ ምላሽ ቡድን እና የጅማ ከተማ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት በመተባበር ያዘጋጁት በድንገተኛ አደጋ ግዜ ቁጥጥርና ምላሽ አሰጣጥ ዙርያ የሚካሄደው የመስክ ሙከራ ነገ ስለሚካሄድ ከዚህ በፊት ባልተለመደ መልኩ የአንቡላንሶች እንቅስቃሴና ድምፅ(ሳይረን)፣ እንድሁም የጤና የባለሙያዎች እንቅስቃሴ እንደሚኖር ተገልጿል።

በዚህም፥ በከተማዋ ከጧቱ 3 ስዓት እስከ ከቀኑ 6 ሰዓት በሚኖረው እንቅስቃሴ ህብረተሰቡ እንዳይደናገጥ የጅማ ከተማ ከተማ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት መልዕክት አስተላልፏል።

የእንቅስቃሴዎቹ ስፍራዎች፦

1.ከጅማ ዩኒቨርስቲ ትልቁ ስታዲየም
2.የጅማ ዩኒቨርስቲ ሪፈራል ሆስፒታል
3. ሸኔን ግቤ ሆስፒታል
4.የጅማ ጤና ጣቢያ

ሁሉም አካላት እንቅስቃሴዉ በሚደረግባቸዉ በሁሉም ስፍራዎች ለአንቡላንሶችና ለጤና ባለሞያዎች የቀና ትብብር እንድያድርጉም ተጠይቋል።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
28.3K viewsedited  18:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-31 20:45:59
ለጉልበት ብዝበዛ 13 ህጻናትን አሳልፎ ለመሸጥ ሲሞክሩ የነበሩ ሁለት ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ።

በባሌ ዞን 13 ህጻናትን ከምዕራብ አርሲ ሻሸመኔ ወረዳ በማምጣት ዞኑ ሲናና ወረዳ ላይ ለጉልበት ብዝበዛ (በከብት ጥበቃ፣ለቤት ሰራተኝነት እና ለንግድ ቤት) እያንዳንዳቸዉን በሶስት ሺህ ብር ለመሸጥ ሲሞክሩ የነበሩ ሁለት ግለሰቦች በእስራት ተቀጥተዋል ተብሏል።

አንደኛ ተከሳሽ ጀማል ሱሳ እንዲሁም ሁለተኛ ተከሳሽ ሂርጶ ዲማ በምዕራብ አርሲ ዞን ሻሸመኔ ወረዳ አባሮ ቀበሌ ነዋሪ ሲሆኑ አስር ወንድ እና ሶስት ሴት ህጻናትን በህገወጥ መንገድ ወደ ባሌ ሲያጎጉዙ በአንድ ህጻን ላይ በተፈጠረ የዋጋ አለመግባባት ምክኒያት ህብረተሰቡ ለፖሊስ ባደረሰው ጥቆማ ተጠርጣሪዎቹ ሊያዙ መቻላቸዉ ተገልጿል፡፡

ፖሊስ ጉዳዩን ሲከታተል ቆይቶ መዝገቡን ለባሌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ባቀረበው መሰረት ፍርድ ቤቱ በመጀመሪያ ተከሳሽ ጀማል ሱሳ ላይ በአስራ ስምንት ዓመት እስራት እንዲሁም በሁለተኛ ተከሳሽ ሂርጶ ዲማ ላይ ደግሞ የአስር ዓመት እስራት ወስኖባቸዋል፡፡

የባሌ ዞን ፖሊስ መምሪያ ኮሚኒኬሽን ባለሙያ የሆኑት ኮማንደር ናስር ዑመር ለብስራት ኤፍ ኤም እንደገለጹት በደቡብ ክልል እና በምዕራብ አርሲ ዞን ህገወጥ የህጻናት ዝውውር በከፍተኛ መጠን እየጨመረ በመሆኑ የሚመለከተው አካል ለጉዳዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አሳስበዋል።

Credit : Bisrat Fm 101.1

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
27.0K viewsedited  17:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-31 19:56:34
#ጤናረቡዕ በነገው ዕለት .....

'ጤናማ አንጀት' ምንድን ነው?

የአንጀት ማይክሮባዮም ምንድን ነው?

የአንጀት ማይክሮባዮም ጠቀሜታ ምንድን ነው?

ጤናማ የሆነ የማይክሮባዮም መጠንን ለማጠናከር ምን ማድረግ እችላለሁ?

ለእነዚህ ጥያቄዎች ምላሽ በነገው ዕለት በ @tikvahethmagazine ይጠብቁን!

[ ክሮንስ እና ኮላይተስ ኢትዮጵያ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የሚያቀርብ ]

@tikvahethmagazine @ibdeth
25.1K views16:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-31 19:42:39
የተምች ወረርሽኝ በሰብሎች ላይ መከሰቱን የቡርጂ ልዩ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ገለፀ።

በደቡብ ክልል አማሮ ልዩ ወረዳ በሁሉም ቀበሌያት ፀረ ሰብል የሆነው የ #ተምች ተባይ ወረርሽን መከሰቱ ተገልጿል። የቡርጂ ልዩ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሽብሩ ኦቴ እንደ ወረዳ በአዋር ክላስተር አካባቢ በሚያዝያ ወር ተከሰቶ 200 ሊትር መድኃኒት ተረጭቶ የነበረ ቢሆንም በድጋሚ በወረዳው ሁሉም ቀበሌያት በመከሰቱ ጉዳዩን ይበልጥ አሳሳቢ አድርጎታል ይላሉ።

በአጠቃላይ ሰብሉ የተሸፈነው በ39000 ሄክታር አከባቢ በመሆኑና የተምች ስርጭት መጠኑ ከፍተኛ በመሆኑ በመድኃኒት ቶሎ ካልተቆጣጠርን ሰብሎችን እንደሚጎዳና ህብረተሰቡን ለከፋ ችግር እንደሚያዳርግም ኃላፊው ተናግረዋል።

የክልሉ መንግሥትም ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ የሚገልፁት ኃላፊው 1400 ሊትር መድኃኒት ከክልል እስከ ነገ እንደሚገባምና ለቀጣይም የተምች ተባይ የመራባት አቅሙ ከፍተኛ በመሆኑ የመድኃኒት እጥረት እንዳይከሰት የክልሉ መንግሥት ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።

አርሶ አደሮቹ በበኩላቸው እስካሁን ምንም የደረሳቸው መድኃኒት እንደሌለ ገልፀው የክልሉ መንግሥትም ሆነ የወረዳው መንግሥት ጊዜ ሳይሰጥ የተምች የመሰራጨት መጠኑ ከፍተኛ በመሆኑ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ ቶሎ መድኃኒት እንዲያቀርቡም አበክረው ጠይቀዋል ሲል የዘገበው የቡርጂ ልዩ ወረዳ መንግሥት ኮሚኒኬሽን ነው።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
25.1K viewsedited  16:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-31 17:15:56
ባለፉት ዘጠኝ ወራት 444 ሐሰተኛ ማስረጃዎች ጥቅም ላይ እንዳይውሉ ተደርጓል።

የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት በዘጠኝ ወራት ውስጥ 303 መታወቂያ፣ 12 የጋብቻ ማስረጃ ፣ 111 ያላገባ ማስረጃ.፣ 8 የውክልና ሰነድ፣ እና ሌሎች ሰነዶችን ጨምሮ በአጠቃላይ በተቋሙ 444 ሐሰተኛ ማስረጃዎች ጥቅም ላይ እንዳይውሉ ማድረጉን ገልጿል።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
24.5K viewsedited  14:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ