Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-MAGAZINE

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE
ርዕሶች ከሰርጥ:
Update
Sale
Packingmachine
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 196.56K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን 251913134524

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 237

2022-06-03 16:18:53
#Update

ዛሬ ግንቦት 26 ቀን 2014 ዓ.ም በሶስት ዙር በተከናወነ ዜጎችን ከሳኡዲ አረቢያ የመመለስ ስራ በአጠቃላይ ቁጥራቸው 1ሺህ 85 ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው መመለሳቸው የተገለጸ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ሁለት ህጻናትና 1083 ወንዶች ናቸው ተብሏል፡፡ እስካሁን ድርስ በተከናወነው ዜጎችን የመመለስ ስራ ቁጥራቸው ከ 32,321 በላይ ኢትዮጵያውያንን መመለስ ተችሏል፡፡

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
19.8K viewsedited  13:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 11:47:34
አረንጓዴ ሀይድሮጂንና አሞኒያ ምርት ለማስጀመር ከአውስትራሊያ ካምፓኒ ጋር መግባባት ላይ ተደረሰ።

የአውስትራሊያ የኢንቨስትመንት ተቋም የሆነው ፎርትስኪው ፊውችር ኢንዱስትሪ በኢትዮጵያ አረንጓዴ ሀይድሮጂንና አሞኒያ ምርት ላይ በመሰማራት ለታዳሽ ሀይል ለማዋል ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር በሸራተን አዲስ በጋር ባካሄደው ጋዜጣዊ መግልጫ ይፋ አድርጓል፡፡

የገንዘብ ሚኒሰቴር ሚንስትር አቶ አህመድ ሽዴ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ2020 ጀመሮ የኢትዮጵያ መንግስት ከአውስትራሊያው ከፎርትስኪው ፊውችር ኢንዱስትሪ ጋር የአረንጓዴ ሃይድሮጂን እና አሞኒያ ፕሮጀክት ለማሰጀመር ውይይት ሲያደረግ እንደቆየ ገልጸዋል።

ፕሮጀክቱ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማትን በማጎልበት፣ ከበካይ ጋዝ የጸዳ የሀይል ምንጭ በማቅረብ፣ ለዜጎች የስራ እድል በመፍጠር፣ ለውጭ ገበያ የሚቀርብ ታዳሽ ሀይል በማምረት ለሀገሪቱ ልማትና እድገት የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡

የፎርትስኪው ፊውችር ኢንዱስትሪ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጁሊ ሹትልዎርዝ እንደተናገሩት ኩባንያቸው አረንጓዴ ሃይድሮጂንና አሞኒያ በማምረት የካርቦን ልቀትን ዜሮ በማደረስ መቶ በመቶ ታዳሽ ኃይልን ጥቅም ላይ እንደሚያውል አስታውቀዋል፡፡

አረንጓዴ ሃይድሮጂንና አሞነኒያ ለማዳበሪያ ምርት ለሲሚንቶ ፋብሪካ፣ ለከባድ ተሽከርካሪች፣ ለባቡርና ለመርከብ ትራንስፖርት ሀይል ምንጭነት የሚያገልግል ከበካይ ጋዝ የጸዳ የአይል ምንጭ ነው፡፡

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
22.1K viewsedited  08:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 11:47:19
ዱባይ ሁለተኛ ቤትህ ለመሆን ተዘጋጅታለች...

አንተን ለመሰሉ ስኬታማ ሰዎች በልክ የተሰራች የምትመስለው የአለማችን ቅንጡዋ ከተማ ዱባይ
አሁን ደግሞ ስኬትህን ልክ እንደ ንጉስ ያለሃሳብ እንድታጣጥም ጎልደን ረዚደንስ ወይም ወርቃማ የመኖሪያ ፍቃድ የተሰኘ አማራጭ፣ 2 ሚሊየን ድራሃም ወይም ከዚያ በላይ ዋጋ ያላቸው መኖሪያ ቤቶችን ለሚገዙ ብልጦች አቅርባለች...

ይህ ብዙዎች እየተሻሙበት ያለ እድል እንዳያመልጥህ ፍላጎትህን በቴሌግራም አካውንታችን አሳውቀን፣ ህልምህ እውን እንዲሆን የተለያዩ የብድር አማራጮችን ይዘን እንጠብቅሃለን... መልክትህን ለመላክ:
ዌብ ሳይታችንን ጎብኝ: https://www.biltlij.com/
በቴሌግራም ለመነጋጋር: https://t.me/bilt_lij
በዋትስአፕ ለመነጋገር: https://wa.link/y2j9af
ወይም ለመደወል፡ +97152989 8575
18.1K views08:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 11:47:19
Procurement Management will start on the coming Monday 6th of June 2022 starting from 02:30 local time.

You can register at https://www.effsaa.org/short-term-training-program-registration-form/ after the settlement of the payment by using the following bank address.
Ethiopian Freight Forwarders and Shipping Agents Association (EFFSAA)
Bank of Abyssinia
Bambis Branch
Account No. 27805396

If you require further information, please call us at +251 115 589045 / +251 903 182525
OR
Visit our telegram channel https://t.me/EFFSAAOfficial
18.7K viewsedited  08:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 23:16:32 #የዛሬ_2 (ግንቦት 25/2014)

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የመዝጊያ መግለጫ በቅዱስ ሲኖዶስ ፅ/ቤት ዛሬ ተሰጥቷል። በመግለጫው፥ ውይይቱን ተከትሎ በቀጣይ ጦርነትና የእርስ በርስ ግጭት ተወግዶ አጠቃላይ ሰላም በሚሰፍንበት መልኩ ተነጋግሮ ችግሩን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መፍታት እንዲቻል፣ ቤተ ክርስቲያኗ #የአስታራቂነት ሚናዋን መጫወት እንድትችል ለማድረግ ለፌዴራል መንግሥት ጥያቄ እንዲቀርብ ተደርጓል ተብሏል።

በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ስቴፋን አወር እንደገለጹት ሀገራቸው ጀርመን በኢትዮጵያ መንግሥት ጥያቄ ከቀረበላት ሀገራዊ የምክክር ሂደቱን ለመደገፍ ዝግጁ መሆኗን አሳውቀዋል።

ትናንት ከቀኑ 10 ሰዓት ገደማ በጋምቤላ ወረዳ ጎሊ በሚባል አካባቢ በተፈፀመ ጥቃት በእርሻ ሥራ ላይ የነበሩ 2 ሰዎች ሲገደሉ 3 ሠዎች ታፍነው መወሰዳቸውን የጋምቤላ ክልል አሳውቋል። ክልሉ ለጥቃቱ የጋምቤላ ነፃነት ግንባር (ጋነግ) ተብሎ የሚጠራውን ቡድን እና በህ/ተ/ም/ቤት በአሸባሪነት የተፈረጀውን " ሸኔ " / እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት እያለ የሚጠራውን የታጠቀ ቡድን ተጠያቂ አድርጓል።

4ቱ የሜቴክ የቀድሞ አመራሮች ሌ/ኮሎኔል ሰጠኝ ካሳይ፣ ኮለኔል ፍጹም አብርሃ፣ ሻለቃ ዋልታንጉስ ተስፋው እና ሻለቃ ክንድያ ግርማይ ከእስር እንዲፈቱ ታዟል። አመራሮቹ በቀረበባቸው ክስ ፍርድ ቤቱ ጥፋተኛ ብሎ የእስርና የገንዘብ ቅጣት የፈረደባቸው ቢሆንም ተከሳሾቹ በፍርድ ቤት ከተወሰነባቸው የእስራት ጊዜ በላይ ከጥቅምት 30 ቀን 2011 ዓ/ም ጀምሮ በእስር በማሳለፋቸውና የእስር ጊዜያቸውን በማጠናቀቃቸው ከእስር እንዲፈቱ ታዟል።

በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለለኝ ደብደባ እንደተፈፀመበት ወንድሙ ታሪኩ ደሳለኝ ገልጿል። ድብደባው የተፈጸመው ወንድሙን ጋዜጠኛ ተመስገንን ለመጠየቅ ፖሊስ ጣቢያ ተገኝቶ በነበረበት ወቅት መሆኑን ያስረዳው ታሪኩ ሁለት ፖሊሶች ተመስገንን አብረውት ከቆሙት እስረኞች መካከል ጎትተው በማውጣት በቦክስ፣ በጫማ ጥፊ ለሁለት እንደደበደቡት ይህንንም የሌሎች እስረኛ ጠያቂ ቤተሰቦችና እስረኞች ማየታቸውን ገልጿል። ከቆይታ በኃላ በቢሮ ውስጥ ጋዜጠኛ ተመስገንን እንዳገኘው የሚገልፀው ታሪኩ " የግራ ዓይኑ ስር አብጦ የለበሰው ቲ-ሸርት ተቀዶ አግኝተነዋል " ሲል ሁኔታውን አሳውቋል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
5.6K viewsedited  20:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 23:16:02 #የዛሬ_1 (ግንቦት 25/2014)

በጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ሰሞኑን ትግራይ ክልል መቐለ የነበሩት የአፍሪካ ሕብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ፣ ከቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ ከዓለም ባንክ የኢትዮጵያ ተወካይ ኡስማን ዲዮን እንዲሁም የፌደራል እና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር ሆነው በባሌ ዞን ሲናና ወረዳ በ3 ሺህ 200 ሔክታር መሬት ላይ በክላስተር የለማውን የሥንዴ ሰብል ጎብኝተዋል፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም በ45 ሚሊዮን ብር ወጪ በአዲስ አበባ እና በክልል ባሉ በ66 የመንግስት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከ140ሺህ በላይ ተማሪዎችን መድረስ የሚችል የዲጂታል መማሪያ ማዕከላትን ገንብቶ በዛሬው ዕለት አስመርቋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) በድርጅቱ የቱርክ /ተርኪ ስያሜ ወደ ተርኪዬ መቀየሩን ዛሬ በይፋ አሳውቋል። ለሀገሪቱ ስያሜ ለውጥ " ቱርኪ " የሚለው ስያሜ ምዕራባውያን በዓል ወቅት ለምግብ ከምትቀርበው የዶሮ ዝርያ ጋር መያያዙ እንዲሁም በካምብሪጅ የእንግሊዝኛ መዝገበ ቃላት ላይ 'ተርኪ' የሚለው ቃል፤ 'ሙሉ በሙሉ ያልተሳካ' ወይም 'ውድቀት የሆነ ነገር' የሚል ትርጓሜን በመያዙ ለስም ቅያሬው በምክንያትነት ተጠቅሷል።

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አቀፍ የሬዲዮ ጣቢያ አስመርቋል። የሬዲዮ ጣቢያው በኤፍ ኤም 104 ነጥብ 5 ሞገድ አገልግሎት ይሰጣል ተብሏል።

የምስራቅ እና መካከለኛው አፍሪካ ሴካፋ የሴቶች ሲንየር ሻምፒየን ሺፕ በዩጋንዳ ቀጥሎ ሲካሄድ ኢትዮጵያ ከ ዛንዚባር ጋር ያደረገችውን ጨዋታ 5 - 0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችላለች። የሉሲዎቹን የማሸነፊያ ግቦች ሎዛ አበራ እና ቅድስት ዘለቀ ሁለት ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥሩ አረጋሽ ካልሳ አንድ ግብ አስቆጥራለች።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
5.3K viewsedited  20:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 18:07:18
በአንቡላንስ 21 ሰዎችን ጭኖ በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሱዳን ለማሻገር የሞከረው ሹፌር ፍርድ ቤት ቀረበ።

ከኦሮሚያ እና ከደቡብ ክልል አንስተው ወደ ሱዳን ለመሻገር በተለያዩ ደላሎች አማካኝነት የመጡ 21 ሰዎችን ጭኖ በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሱዳን ለማሻገር ሲያጓጉዝ የነበረ የቋራ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት የአንቡላንስ ሹፌር ላይ በህገ ወጥ የሰዎች ዝውውርና በሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ።

ተከሳሹ ንጉሴ መኮነን ግንቦት 14 ቀን 20214 ዓም ከሌሊቱ 8:00 ሲሆን ኪነቢ ቀበሌ ጋንክ ጎጥ ላይ ከደላሎች በመቀበል በአምቡላንስ መኪና ጭኖ ወደ ሱዳን ለመሸኘት በማጓጓዝ ላይ እያለ ገለጉ ከተማ አለሙ በር ተብሎ ከሚጠራው ቦታ ላይ የፀጥታ አካላትንና ኬላ ጥሶ ማለፉን የክሱ መዝገብ ያስረዳል።

በዚህም የጸጥታ ኃይሎች ጥይት ለመተኮስ የተገደዱ ሲሆን በንብረት ላይም ጉዳት ደርሷል። ተከሳሹ ተዘዋዋሪዎቹን ወደ ጨካ እና ባዶ ቤት ወስዶ የደበቃቸው ቢሆንም ተከሳሹ እና ተዘዋዋሪዎች በፀጥታ ሀይል ክትትል ተይዘዋል ተብሏል።

ዛሬ ግንቦት 25 ቀን 2014 ዓም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ፍ/ቤት ቀርቦ የክሱ ግልባጭ ደርሶት ክሱ ተነቦለት የእምነት ክህደት ቃሉን ሲጠየቅ ክሱን አልቃወምም የወንጀል ድርጊቱን አልፈፀምኩም በማለት ክዶ ተከራክሯል።

ዐቃቤ ህግም ተከሳሸ የወንጀል ድርጊቱን ስለመፈፀሙ በሰውና በሰነድ ማስረጃ አረጋግጨ ክስ ሰላቀረብሁ የዐቃቤ ህግ ምስክሮች ይሰሙልኝ በማለት ለፍ/ቤቱ አሳስቦ የዐቃቤ ህግ ምስክሮችን ፍ/ቤቱ አድመጧል።

የምዕራብ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤትም የዐቃቤ ህግ ምስክሮችን ካዳመጠ በሗላ መዝገቡን መርምሮ ብይን ለመስጠት ለ ሰኔ 02 ቀን 2014 ዓም ቀጠሮ ሰጥቷል።

መረጃው የምዕራብ ጎንደር ዞን ፍትህ መምሪያ ነው

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
21.1K viewsedited  15:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 17:44:12
የማዕድን ሚኒስቴር 113 ሚሊየን ብር በሶማሌ ክልል ለካሉብ እና ለሂላላ አካባቢዎች ልማት እንዲውል አበረከተ።

የማዕድን ሚኒስቴር በሶማሌ ክልል በነዳጅ ፍለጋ ላይ ከተሰማሩ ኩባንያዎች የተሰበሰበበ 113 ሚሊየን ብር ካሉብ እና ሂላላ አካባቢዎች ላሉ ማኅበረሰቦች ልማት እንዲውል ለክልሉ አበርክቷል።

የማዕድን ሚኒስትሩ ኢንጂነር ታከለ ኡማ እንደተናገሩት፥ በአካባቢው በሚከናወን የነዳጅ እና የጋዝ ማዉጣት ሥራ ላይ የተሰማሩ ድርጅቶች በገቡት ስምምነት መሰረት ላለፉት አምስት ዓመታት ለማኀበረሰቡ የሚያስፈልጉ የልማት ሥራዎች በስምምነቱ መሰረት አልፈጸሙም፡፡

በመሆኑም የእነዚህን ዓመታት 113 ብር ሚሊየን ለክልሉ በማስረከብ የአካባቢው ነዋሪዎችና የክልሉ መንግስት በመነጋገር በአካባቢው የተጓደሉ የልማት ስራዎችን እንዲያከናውን ይደረጋል ብለዋል።

የነዳጅ ማውጣት ሥራ ላይ ተሰማርተው የቆዩ ኩባንያዎች በገጠማቸው የገንዘብ ችግር አቋርጠው ለመውጣት መገደዳቸውንም የተናገሩት ሚኒስትሩ፥ ሥራዎች በሚፈለገው ልክ እየተሰሩ እንዳልሆነም ነው የገለፁት።

አሁን የቀረው “ፖሊ ጂ ሲ ኤል” የተባለ የቻይና ኩባንያ እንደሆነና ወደ ሥራ እንዲገባ ከተሰጠው የ6 ወር ጊዜ ውስጥ አምስቱ አጥጋቢ ሥራ ሳይሰራበት እንዳጠናቀቀውም ጠቁመዋል፡፡

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
18.6K viewsedited  14:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 17:41:38
የሃይማኖት አስተማሪ በመምሰል በ4 ህጻናትና ወጣቶች ላይ የተመሳሳይ ፆታ ጥቃት የፈጸመው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ።

እራሱን የሃይማኖት አስተማሪ በማስመሰልና የሃይማኖት አባትና ልጅ ግንኙነት በመፍጠር ከእርሱ ጋር ተመሳሳይ ጾታ ካላቸው 4 ህጻናትና ወጣቶች ላይ የተመሳሳይ ፆታ ጥቃት ድርጊት ሲፈጽም የነበረው ተከሳሽ በ13 አመት ጽኑ እስራት ተቀጣ፡፡

አቶ ገነት አሰፋ የተባለው ተከሳሽ በጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ በአማውቴ ግፍትጌ ቀበሌ ልዩ ስሙ ጋቲራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ጸበል ፈልቋል በማለትና አራት ህጻናትና ወጣቶችን አብራችሁኝ እደሩ ፣የተለያዩ ሀይማኖታዊ መጻፍቶችን ታነቡልኛላችሁ ብሎ በመጥራት አታሎ ድርጊቱን መፈጸሙን የክስ መዝገቡ ያስረዳል።

ግለሰቡ አብረውት እንዲያድሩ ካደረገ በኋላ ልብሳቸውን አውልቀው ከራሱ ጋር እንዲተኙና በራእይ ታይቶኛል ከኔ ጋር ኑሩ በማለት በማታለል በ4 የግል ተበዳዮች ላይ የተመሳሳይ ፆታ ጥቃት ድርጊት ተፈጽሟል ሲል የሶዶ ወረዳ ዐቃቢ ሕግ ክስ አቅርቧል፡፡

የዓቃቢ ህግ ክሶች እና ካቀረባቸው የሰው እና የሰነድ ማስረጃዎች አንጻር ተከሳሽ እራሱን የሃይማነት አስተማሪ በማስመሰል ይህንን አይተው ወደሱ ይመጡ በነበሩት ተከታዮቹ ላይ ተመሳሳይ ፆታ ጥቃት የወንጀል ድርጊት ከተመሰከረበት እና ከቀረበበት ክስ አልተከላከለም፡፡

የጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ፍርድ ቤት ዛሬ በዋለው ችሎት ዐቃቢ ህግ ጠቅሶ ባቀረበው በኢ.ፌ.ድ.ሪ.የወንጅል ህግ አንቀጽ 630(2)ሀ ስር የተመለከተወን በመተላለፍ በተለያዩ ጊዜ በአራት የግል ተበዳዮች ተመሳሳይ ፆታ ጥቃት የወንጀል ድርጊት መፈጸሙ በመረጋገጡ በወንጀለኛ መቅጫ ስነስርዓት ቁጥር149(1) መሰረት ተከሳሽ አቶ ገነት አሰፋን በ13 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
16.5K viewsedited  14:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 17:41:06
የስራ ማግኛ ኦንላይን ፕላትፎርም /ሊንኮችህ/ ዝርዝር ለማግኘት

Join our telegram

https://t.me/+Zhm6yWqPh7U0N2E0
14.8K views14:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ