Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-MAGAZINE

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE
ርዕሶች ከሰርጥ:
Silver
Platinum
Golden
Naturaldisaster
Alert
Update
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 196.59K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን 251913134524

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 231

2022-06-10 21:15:26
"በህጋዊ 5 መቶ ብር ሃሰተኛ 1ሺ 500 ብር እንደሚቀይሩ በምርመራ ተረጋግጧል" ፡ ፖሊስ

በሀሰተኛ ገንዘብ ሲገለገሉ ተይዘው ምርመራ በተደረገባቸው 4 ተማሪዎች መነሻነት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው ካዛንቺስ አፍሪካ ዳቦ ቤት እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በሚገኘው የተጠርጣሪ ቤት በህግ አግባብ በተደረገ ፍተሻ 13ሺ 200 ሃሰተኛ ብር እና ብሩን ለማዘጋጀት የሚጠቀምባቸውን የተለያዩ ቁሳቁሶች መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።

ተማሪዎቹ ሃሰተኛ ባለ 2 መቶ የብር ኖት ይዘው በሚማሩበት ትምህርት ቤት መዝናኛ ክበብ ግብይት ለመፈፀም ሲሞክሩ የክበቡ ባለቤት ተጠራጥረው ጉዳዩን ለፖሊስ በማሳወቃቸው ተማሪዎቹን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ የማጣራት ስራ መሰራቱ ነው አስታውቀዋል።

በተማሪዎቹ ላይ በተደረገው ምርመራ ሃሰተኛ ገንዘቡን ከሚዘጋጀው ግለሰብ በህጋዊ 5 መቶ ብር ሃሰተኛ 1ሺ 500 ብር እንደሚቀይሩ በምርመራ መረጋገጡን የላንቻ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የወንጀል ምርመራ ማስተባበሪያ ሃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ስለሺ ሸንቁጤ ገልጸዋል።

ከአራቱ ተማሪዎች በተጨማሪ ሃሰተኛ ገንዘቡን ሲያዘጋጅ የነበረው ግለሰብ እና በግብራበርነት የተሳተፉ 2 ተጠርጣሪዎች በአጠቃላይ 7 ግለሰቦች ተይዘው የምርመራው ሂደት መቀጠሉን ፖሊስ ገልጿል፡፡

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
14.1K viewsedited  18:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-10 21:14:04
#ELiDAEthiopia

“ከጦርነት በኋላ የሚፈጠር የኢኮኖሚ አቅም መዳከም እና ከግጭት በኋላ የሚደርስ ስነ-ልቡና ጉዳት ትልቅ ትኩረት ተደርጎ ሊሰራበት እና ፈጣን ምላሽ የሚሻ ችግር ነው፡፡ በመሆኑም ከግጭት በኋላ የሚሰጡ አስቸኳይ ምላሾች ሴቶችን፣ ወጣቶችን እና ተፅዕኖ ፈጣሪ የማህበረሰብ መሪዎችን ማሳተፍ አለባቸው። እንዲሁም፣ የሀይማኖት አባቶች፣የማህበረሰብ ተወካዮች፣የወጣቶችና የሴቶች ማህበር ተወካዮች በቅንጅት በመረባረብ የህብረተሰቡን የቀድሞ እና የቆየ ሰላማዊ ባህል ወደነበረበት ለመመለስ ሊረባረቡ ይገባል።”

በደሴ ከተማ በተደረገ የመጀመርያዙር ውይይት የተነሳ

For English

° Website ° Facebook ° Twitter ° Telegram
13.8K viewsedited  18:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-10 17:06:32
በተያዘው ክረምት በኦሮሚያ ክልል ስድስት ሺህ የቅድመ-መደበኛ ትምህርት ቤቶች ይገነባሉ።

በተያዘው ክረምት በኦሮሚያ ክልል ስድስት ሺህ የቅድመ-መደበኛ ትምህርት ቤቶች እንደሚገነቡ የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።

በምስራቅ ሸዋ ዞን ቦራ ወረዳ ማሊሞ ቀበሌና በምዕራብ አርሲ ዞን ዶዶላ ከተማ የትምህርት ቤቶቹ ግንባታ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ተካሄዷል።

በ’ቡኡራ ቦሩ’(የነገ ተስፋ) የመማሪያ ክፍሎች ግንባታና የመምህራን ስልጠና ስራዎች ለሚገነቡት ስድስት ሺህ ትምህርት ቤቶች እስከ 30 ቢሊዮን ብር ወጪ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።

የግንባታው ወጪ በዜግነት አገልግሎት በሚሳተፉ በጎ ፈቃደኞች፣ ባለሃብቶች፣ በጎ አድራጊ ተቋማትና በውጭ ከሚኖሩ ዳያስፖራዎች እንደሚሸፈን የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ቶላ በሪሶ ገልጸዋል።

ትምህርት ቤቶቹ በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን እድሜያቸው አምስት ዓመት የሆናቸውን ሕጻናት እንደሚቀበል ተናግረዋል።

የግንባታው አላማ በክልሉ የገጠር ክፍሎች ያሉ ዜጎች የትምህርት ተደራሽነት ማስፋት መሆኑን አመልክተዋል።

በ2013 ዓ.ም ክረምት በጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር 3 ሺህ 11 የቅድመ-መደበኛ ትምህርት ቤቶች የተገነቡ ሲሆን 1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ተማሪዎች ተቀብለው እያስተማሩ ይገኛሉ።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
21.2K viewsedited  14:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-10 11:04:34
በደቡብ ክልል 4155 ህገ-ወጥ የሰራተኛ ቅጥር ተሰረዘ

በደቡብ ክልል 4155 ህገ-ወጥ የሰራተኛ ቅጥር፣ ዝውውር ምደባና የደመወዝ ማስተካከያዎችን መሰረዙን የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ የበጀት ዓመቱን የ11 ወራት እቅድ ክንውን በሶዶ ከተማ በገመገመበት መድረክ ገልጿል።

የቢሮው ሀላፊ አቶ ዘይኔ ቢልካ በውይይት መድረኩ ላይ እንደተናገሩት በመጠናቀቅ ላይ ባለው በ2014 በጀት ዓመት የ 25 ሺህ 990 የክልሉ የመንግስት ሰራተኞች ፋይል ተመርምሮ 4155 ህገወጥ ቅጥር ፣ ዝውውር ፣ ምደባና የደመወዝ ማስተካከያዎች ተሰርዟል።

በተደረገው የሰራተኞች ፋይል ማጣራት ከ 614 በላይ ሰራተኞች በሀሰተኛ የትምህርትና የብቃት ማረጋገጫ ሰነድ ተመርምሮ ቅጥራቸው ተሰርዟል።

በበጀት አመቱ በአሰራር ችግሮች ሊባክን የነበረ 82 ሚሊዮን 887 ሺህ 682 ብር ማዳን ችለናል ብለዋል የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ዘይኔ ቢልካ። (ደሬቴድ)

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
24.3K viewsedited  08:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-10 11:03:42
በግሎባል ፈንድ ድጋፍ የተገዙ የህክምና መሳሪያዎች እየተሰራጩ እንደሆነ ተገለጸ፡፡

ለጤና ሚኒስቴር በግሎባል ፈንድ ድጋፍ የተገዙ የህክምና መሳሪያዎች ከግንቦት 1 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በመሰራጨት ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት አስታውቋል።

በተቋሙ የባዮ ሜድካል ኢንጅነር ባለሙያ አቶ የቻለ ሽፈራው የተሰራጩት የህክምና መሳሪያዎች Oxygen concentrator, pulse Oximeter እና Flow splitte መሆናቸውን ጠቁመዋል።

መሳሪያዎቹም ለኦክስጂን ህክምና አገልግሎት ለመስጠትና የኮቪድ-19ኝን ለመከላከልና ለማከም እንዲሁም በሰውነት ውስጥ የሚገኝ የኦክስጂን መጠንን ለመለካት አገልግሎት እንደሚውሉ ባለሙያው አብራርተዋል፡፡

ስርጭቱም በአገልግሎት ተቋሙ ቅርንጫፎች አማካኝነት ለአፋር፣ ለአማራ፣ ለኦሮሚያ፣ ለቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ ለደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች፣ ለደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ለሱማሊያ፣ ለጋምቤላ፣ ለሐረርና ለሲዳማ ክልሎች ፣ ለድሬደዋና ለአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር እየተካሄደ እንደሆነ ተገልጿል።

ከተገዙት የህክምና መሳሪያዎች መካከል 3 ሺህ 426 Oxygen concentrator ሙሉ በሙሉ የተሰራጩ ሲሆን ከ850 pulse Oximeter ወደ 240 እና ከ237 Flow splitter 68 ስርጭት መካሄዱን አቶ የቻለ ገልጸው ቀሪዎቹ በስርጭት ሂደት ላይ እንደሚገኙና በአጠቃላይ 928 ሚሊየን 584 ሺህ 487 ብር የሚገመት ዋጋ እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
21.6K viewsedited  08:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-10 11:03:20
የ4 ቀናት ጉዞ ወደ ውቢቷ ዱባይ በድጋሚ ይዘንልዎ መጣን!

ከ 39,799 ብር ጀምሮ!

ቪዛ እና የደርሶ መልስ ቲኬት
ባለ 4 ወይም 5 ኮከብ ሆቴል የ4 ምሽቶች ቆይታ (ማረፊያ) ከጣፋጭ ቁርስ ጋር

ጥቅሉን ይግዙ እና ለ4 ቀናት አስገራሚ ጊዜ ያሳልፉ!

ለበለጠ መረጃ 0115621010 / 0115583058 / 0111575052 ደውለው ሊያገኙን ይችላሉ!

CLICK HERE TO DOWNLOAD OUR APP AND EASILY BOOK YOUR TICKETS

በየጊዜው የምናዘጋጃቸውን ልዩ እና በቅናሽ የቀረቡ የጉብኝት ጥቅሎችን እና የበረራ ትኬቶችን የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ያግኙ!

@fourwindstravel
20.3K views08:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-10 11:03:20
ምን ለመግዛት ወይ ለመሸጥ አስበዋል?

ቤት ፡ መኪና ፡ አፓርትመንት ፡ መሬት ፡ የባንክ ሼር እና የመሳሰሉትን ንብረትዎን በፍጥነት እናሻሸጣለን።

ማይደላላን የመጀመርያ ምርጫዎ ያድርጉ!
ለግዢ፣ ለሽያጭ፣ እና ለኪራይ እኛ ጋር ይደውሉ።

አብረውን መስራት ለሚፈልጉ በራችን ክፍት ነው!
Telegram: https://t.me/MyDelala
: 0903429999
19.9K views08:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-09 23:41:55 #የዛሬ (ሰኔ 2/2014)

በኮትዲቫር አዘጋጅነት ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በምድብ አራት ላይ በቢንጉ ብሄራዊ ስታዲየም በተካሄደ ጨዋታ #የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከ ግብፅ ጋር ያደረገውን ጨዋታ ከጨዋታ ብልጫ ጋር 2 - 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል። የዋልያዎቹን የማሸነፊያ ግቦች ዳዋ ሁቴሳ እና አምበሉ ሽመልስ በቀለ አስቆጥረዋል። ዋልያዎቹ ከ እ.ኤ.አ 1989 በኋላ በኋላ የግብፅ ብሄራዊ ቡድንን ማሸነፍ ችሏል።

የዛሬው ውጤት ተከትሎ ሀገራችን በሶስት ነጥብ አንደኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች። ሀገራችን #ኢትዮጵያ ከግብፅ ጋር ያደረገችውን ፍልሚያ በማሸነፏ፤ ማላዊ ደግሞ በጊኒ በመሸነፏ ምድቧን #በአንደኛነት መምራት ጀምራለች።

በሀገራችን የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የቁርዓን እና የአዛን ውድድር የፊታችን እሁድ ይካሄዳል። ሰኔ 5/2014 በአዲስ አበባ ስቲዲዮም ለሚካሄደው ዓለም አቀፍ የቁርዓን እና የአዛን ውድድርም በርካታ እንግዶች እየገቡ ይገኛሉ። ሀገራችን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚያስጠራው ይህ ውድድር ከ56 በላይ ሀገራት የሚወዳደሩበት ሲሆን ለውድድሩ ከፍተኛ ዝግጅት ሲካሄድ ቆይቷል ተብሏል።

ዛሬ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከልዑካቸው ጋር ለአዲሱ የሶማሊያ ፕሬዜዳንት በዓለ ሲመት ለመታደም ሞቃዲሾ ተገኝተዋል። በበዓለ ሲመቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) #ኢትዮጵያ ለአዲሱ የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ያላትን ድጋፍ አረጋግጠዋል። በሶማሊያ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር በማየታቸውም ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የፓስፖርት አገልግሎት ክፍያዎችን በ " ቴሌ ብር " አማካኝነት መፈፀም እንዲቻል በኢትዮ ቴሌኮም እና በኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት መካከል ዛሬ ስምምነት ተፈፅሟል።

ድንበር የለሽ ዶክተሮች (MSF) በአፋር ክልል እየጨመረ የመጣው የምግብ እጥረት ቀውስ ስጋት እንዳጫረበት ገልጿል። ድርጅቱ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች መሠረታዊ የሚባሉ የጤና ማዕከላትን እንዲሁም ንጹህ የመጠጥ ውሃ በማያገኙበት ሁኔታ ነው የሚኖሩት ብሏል። በተጨማሪም በርካታ ሕፃናት በከፋ የምግብ እጥረት ሕይወታቸውን አጥተዋል ሲል አመልክቷል።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ሰለሞን ሹምዬ እና መዓዛ መሐመድ በስር ፍርድ ቤት የተፈቀደላቸውን የ10 ሺህ ብር ዋስትና ሽሯል። ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን የሻረው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በዋስትና ትዕዛዙ ላይ ይግባኝ ካቀረበ በኋላ ነው። የከፍተኛው ፍርድ ቤት ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 2 ቀን 2014 ከሰዓት በጽህፈት ቤት በኩል በሰጠው ትዕዛዝ ለመርማሪ ፖሊስ የ8 ቀናት የምርመራ ጊዜን ፈቅዷል።

የአብክመ ጠቅላይ ፍ/ቤት ዛሬ ሰኔ 2 ቀን 2014 ዓ/ም በዋለው ችሎት የብርጋዴል ጀኔራል ተፈራ ማሞን ጉዳይ ተመልክቷል። በዚህም፥ የጊዜ ቀጠሮውን ጉዳይ መርማሪ ፖሊስ ምርመራየን ጨርሸ የምርመራ መዝገቡን ለዐቃቢ ህግ ለመላክ በዝግጅት ላይ ነኝ ያለ ሲሆን የክልል ዐቃቤ ህግ በችሎት ቀርቦ አዎ ምርመራው አልቋል የክስ መመስረቻ ጊዜ 15 ቀናት ይሰጠኝ ሲል ጠይቋል። የዋስትና ጥያቄውም ላይ ብይን ለመስጠት ለነገ ለሰኔ 3/2014 ዓ/ም ቀጠሮ ሰጥቷል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
5.1K viewsedited  20:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-09 18:46:09
ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የኦንላይን (Online) ሙከራ ፈተና የሰጠው ት/ቤት

በሀገር ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የኦንላይን (Online) ሙከራ ፈተና መስጠቱን የአረካ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አስታዉቋል። ይህም ሀገራዊ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች በፈተና ጊዜ የቴክኖሎጂ ችግር እንዳይገጥማቸው ያግዛል ነው የተባለው።

ፈተናው በሙክራ እየተሰጠ የሚገኘው ትምህርት ቤቱ በራሱ መምህር አማካኝነት በበለጸገው ሥርዓት አማካኝነት ነው። ትምህርት ቤቱ የዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ በተገኙበት በይፋ በዛሬው ዕለት ሲስተሙን አስተዋዉቋል።

የወላይታ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ታደሰ ኩማ ይህ ተግባር እጅግ ተስፋ የሚሰጥ ተግባር መሆኑን በመግለፅ የዚህን ትምህርት ቤት ተሞክሮ ወደ ሌሎች በዞን ወደሚገኙ ትምህርት ቤቶች በአጭር ጊዜ ለማስፋፋት እንደሚሰራ ጠቁመዋል።

ይህ የኦንላይን (Online) ፈተና ዝግጅት ከማዳበር ባሻገር ለተማሪዎች የቴክኖሎጂ ክህሎታቸውን እንዲያዳብሩና እንድያጎለብቱ መልካም እድል እንደሆነ የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር አቶ አለማየሁ ተናግረዋል።

ትምህርት ቤቱ በዚህ ዘርፍ ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የጠቀሱት አቶ አለማየሁ በረካታ በጀቶችን ወደዚህ መስክ በማሰማራት ዉጤታማ ለመሆን እየተሰራ እንደሚገኝ ጭምር ጠቁመዋል።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
22.0K viewsedited  15:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-09 16:42:02
በመዲናዋ የቱሪስት ፖሊስ ለማቋቋም የሚያስችል መነሻ ሰነድ ላይ ውይይት ተካሄደ።

የአዲስ አበባ ባህል፣ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ በከተማ ደረጃ የቱሪስት ፖሊስ ለማቋቋም የሚያስችል መነሻ ሰነድ ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ማካሄዱን ገልጿል።

መነሻ ሰነዱን ያቀረቡት የቢሮው የቱሪዝም መዳረሻ ልማት ቡድን መሪ አቶ ሳምሶን አይናቸው ከተማዋ ካላት እምቅ የቱሪስት መስህብ ሀብት ለመጠቀም የቱሪስትን ሰላምና ደህንነት ለማረጋገጥ የቱሪስት ፖሊስ በተቋም ደረጃ ማደራጀት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።

የቢሮው ኃላፊ ዶ/ር ሂሩት ካሳው በቱሪዝም ዘርፉ ያለውን ብዛት የለው መስህብ ለቱሪስቱ ተደራሽ ለማደረግ ደህንነቱ የተጠበቀና አስተማማኝ ሰላም ያለባት ለማደረግ የቱሪስት ፖሊስ እንደሚያስፈልግ በመገንዘብ ወደ ስራ እንደተገባ ገልፀው ቱሪስት ፖሊስ ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ እንሰራለን ብለዋል፡፡

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
22.4K viewsedited  13:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ