Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-MAGAZINE

የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 196.57K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን 251913134524

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 228

2022-06-17 14:06:40
የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር መወያየቱን ገለጸ።

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር የማዕከላዊ ጽህፈት ቤት ከፍተኛ አመራሮቹ ከትምህርት ሚኒስቴር ሚንስትሮች ጋር በጋራ ጉዳዮች ላይ ውይይት ማካሄዱን አስታወቀ።

በማህበሩና በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ መካከል ሊኖር ስለሚገባው የተጠናከረ ግንኙነት፣ በመምህራን መብትና ጥቅማ ጥቅሞች በተለይም ከሀምሌ 1/2011 ዓ.ም-መጋቢት 30/2012 ዓ.ም ድረስ ያልተከፈለው የ 9 ወር ወዝፍ ደሞዝ ጉዳይ መነሳቱ ተገልጿል።

በተጨማሪም በተደጋጋሚ እየተነሳ ያለውና በመምህራን የደረጃ እድገት ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ ስላለው PGDT፣ በክረምት ት/ት ወቅት ዶርም በማያገኙ ሰልጣኞች ላይ ስለሚያጋጥም ዘርፈብዙ ችግሮች፣ የከፍተኛ ት/ት መምህራን JEG ና የትምህርት ጥራትን ጨምሮ ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ በስፋት የተወያዩባቸው ጉዳዮች መሆናቸውን አንስቷል።

የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከማህበሩ ጋር ያለው ግንኙነት ተጠናክሮ የሚቀጥል ሆኖ ሚናውን በለየ መልኩ በሚሰሩ ስራዎች ዙሪያ ማህበሩ ሰነድ እንዲያዘጋጅና በአጠረ ጊዜ ውይይት ተካሂዶበት ወደስራ የሚገባበት መንገድ ላይ አቅጣጫ ማስቀመጣቸውን ከማኅበሩ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
21.3K viewsedited  11:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 13:24:12
የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የ405 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አደረገ።

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የ405 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አደርጓል። የድጋፍ ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴና የዓለም ባንክ ግሩፕ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ኦስማን ዲዮን ተፈራርመዋል፡፡

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ካደረገው የ405 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ዉስጥ 195 ሚሊየን ድጋፍ ስምምነቱ በኢትዮጵያ ውስጥ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ የሚያስከተለውን ጉዳት ለመቀነስ እና በሽታውን በመከላከል ሂደት ውስጥ ውጤታማ የኮቪድ 19 ክትባትን ለማከናወን እንዲያስችል ነው ተብሏል።

ከቀናት በፊት የተፈፀመው ቀሪው የ210 ሚሊየን ዶላር የድጋፍ ስምምነት ቆላማ በሆኑ አካባቢዎች የከርሰ ምድር ውሃን ለማልማትና ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያስችል ስምምነት መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ ተናግረዋል ሲል የዘገበው ፋብኮ ነው።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
20.4K viewsedited  10:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 12:59:39
ቃለመጠይቅ ከኩላሊት ህክምና ባለሙያዎች ጋር

በ #ጤናረቡዕ ‹‹ጤናማ አንጀት፣ ጤናማ ኩላሊት›› በሚል ርዕስ ላለፉት ሶስት ሳምንታት መረጃን ስናቀብላቹ ነበር፡፡ በሚቀጥለው ሳምንት እሮብ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ላይም፣ በኩላሊት ህክምና ባለሙያዎች በዶ/ር ሐመልማል ገበየሁና በዶ/ር እሴተ ጌታቸው የኩላሊታችንን ጤና እንዴት መጠበቅ እንደምንችልና የኩላሊታችን ጤና ከአንጀታችን ጤና ጋር በምን መልኩ እንደሚገናኝ በቀጥታ ስርጭት ውይይት እናደርጋለን፡፡

ከምንዳስሳቸው ጉዳዮች በከፊል...

የኩላሊት ጤናዬን እንዴት መጠበቅ እችላለሁ?
ምን አይነት ምርመራ ባደርግ የኩላሊቴን ጤና ሁኔታ ማወቅ እችላለሁ?
አንጀት ጤና እና ኩላሊት ምን ያገናኛቸዋል?
የአንጀት ህመም ስሜቶች እንደ ማስመለስ እና ማስቀመጥ ኩላሊት ላይ የሚያመጣው አደጋ


በዚህ ርዕሰ ጉዳይ ላይ እንዲብራራሎት የሚፈልጉት ጥያቄ አሎት? በ @IBDETHIOPIA መልዕክቶን ይላኩልን፡፡ በቀጥታ ስርጭቱ ላይ ተገቢውን ማብራሪያ እና ምላሽ በባለሙያዎች እንዲሰጦ እናደርጋለን፡፡

@tikvahethmagazine @ibdeth
20.4K viewsedited  09:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 11:23:53 በተለያዩ ግንባታዎች ምክንያት በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚያደርሱት ጉዳት እየጨመረ ነው።

በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ባልሆኑ ተቋማት የሚሰሩ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ከመሬት በታች በተቀበሩ የኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ ጉዳት እያደረሱ መሆኑን ተገልጿል።

በ2014 ዓ.ም በጀት ዓመት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በደቡብና ምዕራብ አዲስ አበባ ዲስተሪክቶች ብቻ በአጠቃላይ ወደ 24 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ የመሰረተ ልማት ጉዳት ደርሶበታል፡፡

በደቡብ ዲስትሪክት በቃሊቲና በለቡ አደባባይ አካባቢ በመሬት ውስጥ በተቀበሩ የኤሌክትሪክ አስተላላፊ መስመሮች ላይ በመንገድ ስራ ምክንያት በደረሰ አደጋ ከ11 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት 4 ሺህ 500 ሜትር የኤሌክትሪክ ገመድ መውደሙ ነው የተነገረው።

በተመሳሳይ በምዕራብ አዲስ አበባ ዲስትሪክት 10 በመሬት ላይ የተቀበሩ ከፍተኛ ወጪ የወጣባቸው የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ ጉዳት ደርሷል። በዚህም ተቋሙ 11 ሚሊዮን 920 ሸህ 249 ብር አጥቷል።

ጉዳቱ የደረሰው በአዲስ አበባ መንገድ ስራዎች፣ በኢትዮ ቴሌኮም እና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዲስ የህንፃ ግንባታ መሆኑን በዲስትሪክቱ የዲስትሪቢውሽን፣ ኮንስትራክሽንና ሚይንቴናንስ ስራ አስኪያጅ አቶ አህመድ ሀሺም ገልፀዋል፡፡

የደረሰውን ኪሳራ ተቋማቱ በህግ አግባብ እንዲከፍሉ ይደረጋል ያሉት አቶ አህመድ ሆኖም ተቋማቱ ያደረሱትን የጉዳት መጠን በወቅቱ የመክፈል ችግር መኖሩን አንስተው ለአብነትም በአዲሱ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ህንጻ ግንባታ በደረሰው ከ3 ሚሊየን 50 ሺህ ብር በላይ የሚገመት ጉዳት ክፍያው እስካሁን ባለመፈፀሙ ጉዳዩ በህግ መያዙን አብራርተዋል፡፡

በመሰረተ ልማት ቅንጅት ቢሮ ስር የልማት ተቋማት በተዘጋጀ የጋራ መግባባያ ሰነድ ላይ ቢፈርሙም ተቋማቱ ህጉንና ስምምነቱን ጠብቀው እየሰሩ ባለመሆኑ ላልተፈለገ ወጪ እየዳረገኝ ነው ሲል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
20.7K viewsedited  08:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 11:23:06
የሰኔ ወር የመጨረሻው ድንቅ ጉዞ ወደ አዋሽ ብሔራዊ ፖርክ እና ድሆ ሎጅ

የጉዞ ቀን:-ሰኔ 11 /2014 | መመለሻ :-ሰኔ 12 /2014
ከሃገር ውጪ ያላችሁ ሃገር ቤት ላሉ ወዳጅ ዘመዶቻችሁ ይህን ምርጥ ጉዞ በመጋበዝ ሰፕራይዝ ያድርጉ

የምንጎበኛቸው፦ |በተፈጥሮ የታደለውን የአዋሽ ፓርክ| አዋሽ ፏፏቴ| ተፈጥሯዊ ፍልውሃ ከ 40-50c በሚደርስ ውሃ መታጠብ| ዋና በድሆ ሎጅ|

ክፍያ የሚያጠቃልለው፦ | የድንኳን አዳር ፓርኩ ውስር | አንድ ምሽት ካምፕፋየር ትራንስፖርት | ምግብ,( ቁርስ ምሳ እራት ) ሻይ ቡና | የታሸገ ዉሃ | አስጎብኚ ስካውት | የፓርክ መግቢያ | ፎቶ ያጠቃልላል|

መነሻ ቦታ ሜክሲኮ ሸበሌ ሆቴል ፊት ለፊት መገኛ ሰዓት 11:30 መነሻ 12:00 ሰዓት

ዋጋ በአንድ በሰው :- 3500
ለበለጠ መረጃ የቴሌግራም ግሩፖችንን ከታች ያለዉን ሊንክ በመጫን ይቀላቀሉ https://t.me/mirt_haikinhg
0962 26 78 20 or @yenaneh
አዘጋጅ፦ የኔነህ ፊልም ፕሮዳክሽን
20.0K views08:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 11:22:58
Sejoy Blood pressure

0911284606
    ሀኪሞን በእጆ , ጤናዎትን በየግዜዉ ሳይጨነቁ በፈለጉበት ቦታ ና ግዜ ይወቁ
የደም መጠን ሚለካ 
የልብ ምት መጠንን ሚለካ
ሰለደም ግፊት አጠቃላይ መረጃ ሚሰጥ
ዋጋ- 1900  birr
Bole medanialem
19.9K views08:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-16 23:26:48 #የዛሬ (ሠኔ 9/2014)

#የዶሮበሽታ

በኢትዮጵያ "የዶሮ በሽታ" መከሰቱን ተከትሎ ጥንቃቄ እንዲደረግ ማሳሰቢያ ተላልፏል። የኢፌዴሪ ግብርና ሚኒስቴር መረጃ እንደሚያሳየው የዶሮ በሽታ በኦሮሚያ እና አዲስ አበባ ከተማ ተከስቷል።

በሽታው እስካሁን በቢሾፍቱ፣ በአቃቂ ቃሊቲ እና ኮልፌ ክፍለ ከተሞች መከሰቱን እና ከ50 ሺህ በላይ ዶሮዎች ሞተዋል። በሽታው ወደ ሌሎች አካባቢዎች እንዳይሰራጭ ልዩ ክትትል በመደረግ ላይ መሆኑንና የሞቱ ዶሮዎችንም ሳይንሱን በጠበቀ መንገድ በማስወገድ ላይ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ፍቅሩ ረጋሳ በሽታው የተከሰተባቸው አርቢዎች ገበያ ባለማውጣት እና የሞቱ ዶሮዎችን በመቅበር እንዲሁም በሽታው የተከሰተባቸውን የእርባታ ጣቢያዎች ኬሚካል መርጨት ይገባል ብለዋል።
||
#አጣዬ

ከዚህ ቀደም በተፈፀመባት ጥቃት ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የወደመችው አጣዬን መልሶ ለማቋቋም የሚደረገው ጥረት ደካማ መሆኑን እና ለዚህም ትኩረት የሚሰጥ የመንግስት አካል ማጣቷ ተነግሯል። ፌዴራል እና የክልል መንግስት ከተማውን እንዲያቋቁሙ ጥሪ ቀርቧል።

አጣዬ በተፈፀመባት ጥቃት 1400 መኖሪያ ቤቶች፣ ሆቴል፣ ግሮሰሪ ፣ መጋዘን እንዲሁም 50 ቤቶች፣ ጥቃቅን እና አነስተኛ ማምረቻ ተቋማት 1550 ሙሉ በሙሉ ተቃጥለው ነበር።

ከተቃጠሉት ምን ያህሉ ተሰሩ ? ለሚለው የከተማው ከንቲባ አሰለፍ ደርቤ ሲመልሱ ''የሞከርነው በዋና ቤት ደረጃ የተቃጠሉትን ከ423 ቤት ውስጥ በመንግስት 45 ቤት፣ በይፋት ልማት ማህበር 10 ቤት አሁን በአልማ 10 ቤት እየሰራን ነው በድምሩ 65 ቤት ነው እየተሰራ ያለው'' ብለዋል።
||
#ስፖርት

በኦስሎ ከተማ ዳይመንድ ሊግ ውድድር እየተካሄደ ሲሆን ከጥቂት ደቂቃ በፊት በተጠናቀቀው የ5 ሺህ ሜትር የሴቶች ሩጫ ውድድር ዳዊት ስዩም (የግል ሰዓቷን በማሻሻል 14:25.84)፣ ጉዳፍ ፀጋይና ለተሰንበት ግደይ ከአንድ እስከ ሦስት ተከታትለው በመግባት ማሸነፍ ችለዋል። በተመሳሳይ በወንዶች የ5 ሺህ ሜትር ውድድርም ጥላሁን ሃይሌ፣ ሳሙኤል ተፈራና ጌትነት ዋሌ በተከታታይ ከአንድ እስከ ሦስት በመግባት አሸንፈዋል።

የሀያ ስድስተኛው ሳምንት የ ቤት ኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ በ ባህር ዳር ስታዲየም መካሄዱን ሲቀጥል ሰበታ ከተማን የገጠመው ፋሲል ከነማ ጨዋታቸውን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል። ጅማ አባ ጅፋር በበኩሉ ተጋጣሚውን ሀዲያ ሆሳዕናን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
5.9K viewsedited  20:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-16 22:20:16
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 114 ኢንቨስተሮች 2 ቢሊዬን ብር ብድር ወስደው ወደ ስራ ሳይገቡ መቅረታቸው ተገለጸ።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 114 ኢንቨስተሮች ከልማት ባንክ 2 ቢሊዬን ብር ብድር ወስደው ወደ ስራ ሳይገቡ መሸሻቸውን የክልሉ ገጠር መሬት አስተዳደርና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ፡፡

በክልሉ በአሁኑ ጊዜ 9 መቶ የሚደርሱ ባለሀብቶች በተለያዩ ስራ ዘርፎች ተሰማርተው እንደሚገኙ የገለጹት የቢሮው ኃላፊ አቶ አመንቴ ገሺ ከእነዚህ ባለሀብቶች መካከል 114 የሚደርሱት  ከልማት ባንክ  ብድር ወስድው ወደ ስራ ሳይገቡ መቆየታቸውን አብራርተዋል፡፡

ባለሀብቶቹ ወደ ስራ ባለመግታቸውና መሬቱ ባለመልማቱ የክልሉ መንግስት በሚሊዩን የሚቆጠር ገንዘብ  የመሬት ግብር ማጣቱንም ኃላፊው ተናግረዋል፡፡

በክልሉ ከዚህ ቀደም በኢንቨስትመንት ስራ የተሰማሩ እና መሬት አስይዘው ያላለሙ እና ለተገቢው ዓላማ ላይ ያላዋሉ ባለሀብቶችን የማጥራት ስራ እንደሚሰራም ቢሮው አመልክተዋል፡፡

በሌላ በኩል የጸጥታ ችግር በሌለባቸው የክልሉ ስፍራዎች በማዕድን ዘርፍ የተሻለ ምርት መገኘቱን ገልጸዋል፡፡ 22 ኩንታል ወርቅ እስካሁን ወደ ብሔራዊ ባንክ መግባቱንም አክለዋል፡፡

በክልሉ ወርቅ፣ ድንጋይ ከሰል፣ መዳብ፣ እምነበረድ፣ እጣን ምርትና 12 ዓይነት የማዕድነት ሀብቶች እንደሚገኙ የገለጹት ኃላፊው በማዕድኑ ዘርፍ በርካታ ወጣቶች መሰማራታቸውን ገልጸው 10 የተደራጁ ማህበራት ደግሞ በቅርብ በክልሉ በእርሻ ኢንቨስትመንት መሰማራታቸውን ጠቅሰዋል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሐሰን በክልሉ ምክር ቤት 13ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ በሰጡት ማብራሪያ በባህላዊ የወርቅ አምራቾች በኩል ከ1ሺ ኪ.ግ በላይ ወደ ብሔራዊ ባንክ መግባቱን መግለጻቸው ይታወሳል። (DW Amharic)

@tikvahethmagazine
11.1K views19:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-16 20:32:28
መቶ የልብ ህሙማን ህፃናት በህንድ ነፃ ህክምና ሊደረግላቸው ነው።

የጤና ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህፃናት መርጃ ማዕከልና ሮተሪ ኢንተርናሽናል 100 የልብ ህሙማን ህጻናትን በህንድ ነፃ ህክምና እንዲያገኙ የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙ።

የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በግብአት አቅርቦት እጥረት እና በሌሎች ተያያዥ ምክንያቶች የልብ ህክምና ለማግኘት ተራ የሚጠባበቁ 7 ሺህ ህፃናት መኖራቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው አየር መንገዱ ወደ ህንድ ለህክምና ለሚሄዱት 100 ህፃናትና ለ100 አስታማሚዎቻቸው የደርሶ መልስ ነጻ የአየር ትኬት መስጠቱን ጠቁመዋል።

የሮተሪ ኢንተርናሽናል የኢትዮጵያ ተወካይ አቶ ተሾመ ከበደ ሮተሪ በህንድ ሀገር የሚከናወነውን የህጻናቱን የህክምና ሙሉ ወጪ እንደሚሸፍንና በቀጣይ የህክምና ማዕከሉን ለማገዝ የሚችለውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህፃናት መርጃ ማዕከል ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሰላዲን ከሊፋ፤ ማዕከሉ በዓመት እስከ 1 ሺህ 500 የልብ ቀዶ ጥገና ለማድረግ የሚያስችል አቅም ቢኖረውም በአቅርቦት ችግር ከ500 ማለፍ እንዳልቻለ ገልጸዋል።

በህንድ ህክምናቸውን ተከታትለው የሚመለሱትን ህጻናት የጤና ሁኔታ ማዕከሉ በዘላቂነት እንደሚከታተልም አስታውቀዋል፡፡ (ENA)

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
17.1K viewsedited  17:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-16 18:37:43
በድሬዳዋ አንድ ግለሰብ የደበደበውን ሰው ለመበቀል የወረወረው የእጅ ቦንብ የአንድ ሰው ህይወት ቀጠፈ።

በድሬዳዋ ከተማ ትላንት ምሽት አንድ ሰአት ከአርባ ደቂቃ አከባቢ ቀበሌ 06 ልዩ ቦታው መጋላ አይጉጉ ተብሎ ከሚጠራው ሆቴል ውስጥ በተወረወረ የእጅ ቦንብ የአንድ ሰው ህይወት ማለፉን የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል።

የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት እና የለውጥ ስራዎች ዳይሬክተር ኮማንደር ገመቹ ካቻ በሰጡት መግለጫ ግለሰቡ አደጋውን አድርሶ ከአካባቢው የተሰወረ ሲሆን ፖሊስ ባደረገው ክትትል ምሽቱኑ በቁጥጥር መዋሉን ገልጸዋል።

ተጠርጣሪው አደጋውን ያደረሰው ከሶስት ቀናት በፊት የደበደበውን ሰው ተከታትሎ ለመበቀል በማሰብ መሆኑን ዛሬ በሰጠው "የእምነት ክህደት " ሃሳብ ማረጋገጡን ኮማንደሩ አብራርተዋል።

በተከሰተው የቦንብ ፍንዳታም አንድ ግለሰብ በደረሰበት ከባድ ጉዳት በድሬዳዋ ድልጮራ ሪፈራል ሆስፒታል በህክምና ላይ አያለ ህይወቱ ያለፈ ሲሆን በአምሰት ግለሰቦች ላይም ከባድ እንዲሁም በአስር ግለሰቦች ላይ ቀላል የአካል ጉዳት ሊደርስ ችሏል፡፡

ተጎጂዎች በድል ጮራ ሆስፒታል ህክምና እየተከታተሉ መሆናቸውን ገልፀው፤ ድርጊቱን በመፈጸም ወንጀል የተጠረጠረው ግለሰብ ላይ ፖሊስ ምርመራውን መቀጠሉን ተናግረዋል።

መረጃው የድሬ ፖሊስ ነው።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
21.4K viewsedited  15:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ