Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-MAGAZINE

የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 196.57K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን 251913134524

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 227

2022-06-20 11:27:44 “የስፖርት ውርርድ ወይም ቤቲንግ እንዲታገድ እየሰራሁ ነው” - የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር

የስፖርት ውርርድ ወይም ቤቲንግ እንዲታገድ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ከታዲጊዎች እና ወጣቶች ስብዕና ግንባታ እንዲሁም በተለያየ መንገድ ከሚያስከትላቸው ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ቀውሶች አንጻር ዘርፉ ሊታገድ ይገባል በሚል በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ በሚኒስቴሩ የወጣቶች ስብዕና ልማት ዳይሬክቶሬት ተወካይ አቶ አበበ ሃይማኖት መናገራቸውን ኢቢሲ ዘግቧል።

የስፖርት ውርርድ ለማስቆም የተለያዩ የንቅናቄና የውይይት መድረኮች ተዘጋጅተው ሲካሄዱ መቆየታቸውን የገለፁት ኃላፊው፤ አሁን ላይ በተለያዩ ምክንያቶች መሰል የምክክር መድረኮች በበቂ መጠን እየተካሄዱ እንደማይገኝ ተናግረዋል።

በተለያየ ጊዜ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተዘጋጁ የዳሰሳ ጥናቶች የስፖርት ውርርድ ለወጣቱና ለታዳጊው ዘርፈ ብዙ አደጋ የደቀነ መሆኑን ያመላከቱ ናቸው ያሉት ኃላፊው፤ ዘርፉ በተጨባጭ ችግር የሚፈጥር መሆኑን ገምገመናል ብለዋል።

የስፖርት ውርርድ ቁማር ነው ብለን እንቅስቃሴ ጀምረናል፤ ቁማር የሚባለው ነገር ደግሞ በራሱ ዘርፈ ብዙ ችግሮች የሚያስከትል ጉዳይ ነው ብለዋል።

ቁማር ታዳጊዎችንም ይሁን አዋቂ ሰዎችን ወዳልተፈለገ መንገድ ሊወስድ የሚችል ማህበራዊ ቀውስ ነው የሚሉት ኃላፊው፤ ማንኛውም ሰው ሰርቶ የመለወጥ እሳቤውን የሚያቀጭጭ፣ ቤተሰብን ጭምር ወደ መበተን ሊያደርስ የሚችል ጉዳይ እንደሆነም ገልፀዋል።

እንደ ኃላፊው ገለጻ፣ ወጣቶች እና ታዲጊዎች ለቤቲንግ ውርርድ ሲሉ ያላቸውን ነገር በሙሉ እስከማውጣት እንደሚደርሱ ጠቅሰው፤ ወጣቶች ስራን ከመስራት ይልቅ በአቋራጭ መክበር እንዲያስቡ በማድረግ ምርት እና ምርታማነትን የሚቀንስ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል።

ዘርፉ በስነልቦና ረገድም ለጭንቀት፣ ለድብርት ብሎም እራስን እስከማጥፋት የሚዳርግ ችግር የሚያስከትል በመሆኑም የሚመለከተው አካል በጊዜ እርምጃ መውሰድ አለበት ብለዋል።

ከዚህ ጋር ተያይዞ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ መሰል የስራ ዘርፎች እንደስራ መታየት እንደሌለባቸው እና ከደቀኑት ፈርጀ ብዙ አደጋ አንጻር ሊታገዱ ይገባል በሚል ለሚመለከታቸው አካላት የማሳወቅ ስራ እየሰራ እንደሚገኝ ኃላፊው ተናግረዋል።

ተቋሙ በተሰጠው ኃላፊነት መሰረት መድረኮችን በማዘጋጀት ፍቃድ ለሚሰጡት የንግድ ሚኒስቴር እና የብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ተቋማት አስፈላጊውን የግንዛቤ እና የማሳወቅ ስራ መሰራቱን የገለፁት ኃላፊው፤ እነዚህ ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ አለማድረጋቸው ለውሳኔው መዘግየት ዋነኛ ምክንያት መሆኑን መግለጻቸውን የኢብኮ ዘገባ ያስረዳል።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
22.5K viewsedited  08:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-20 11:27:30
Chargable hearing aid
የማዳመጫ መርጃ
በቻርጅ የሚሰራ
ዋጋ- 5,000ብር
  0911284606
ያለተጨማሪ ክፍያ ያሉበት ድረስ እናመጣለን
20.4K views08:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-20 11:27:21
#HARAMBEE_MOTORS
መኪና መግዛት አስበዋል...?
ጥሩ አጋጣሚ !!!

10,000 K.M BENZENE FERE

ድርጅታችን #ሐራምቤ_ሞተርስ አዳዲስ የ 2021/22 ሞዴል በሌትር ከ 20 KM በላይ የሚሄዱ ዘመናዊና SUZUKI መኪኖችን አስመጥቶ በተለያዩ አማራጮች በቅናሽ ዋጋ በመሸጥ ላይ እንገኛለን ከወዳጅዎ ጋር ይጎብኙን...!

የ 100 ቀን ነዳጅ ከኛ ነው!
ወሎ ሰፈር ከ አይቤክስ ሆቴል ፊትለፊት

Our Contact
0911222262 0911754675
0929237800 +251114626262

Please join as

Telegram website Instagram

WhatsApp Facebook

የኮሚሽን ሰራተኛ ከሆኑም ብቅ ይበሉ መላ አይጠፋም ! ! !
24.5K views08:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-18 22:45:30 #የዛሬ (ሠኔ 11/2014)

#ምርመራ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በማኅበራዊ መገናኛ ብዙኃን በመዘዋወር ላይ የሚገኘውን እና በርካታ ሰዎች ከመኪና እንዲወርዱ በማድረግ በጅምላ ሲገደሉ የሚያሳየውን ተንቀሳቃሽ ምስል ከሕግ ውጭ የተፈጸመ የግድያ ድርጊት (Extra-judicial killings) ኮሚሽኑ መጋቢት 2 ቀን 2014 ዓ.ም. ባወጣው ሪፖርት ላይ የተካተተ ነው።

ድርጊቱ በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ደዋ ጨፋ ወረዳ ልዩ ቦታው እንቶሊ አካባቢ በታኅሣሥ ወር 2014 ዓ.ም. የመጀመሪያ ሳምንት (ቀኑ በትክክል ያልታወቀ) የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በሁለት የጭነት መኪኖች ጭነው ያመጡዋቸውን እና ወደ 30 የሚጠጉ የኦነግ ሸኔ አባሎች ናቸው ያሏቸውን ሰዎች በጅምላ በጥይት ደብድበው መግደላቸውን ይገልጻል። 

በኢሰመኮ ምርመራ የተዘገበው ከፍርድ ውጭ የተፈጸመ የግድያ ድርጊት የሚያመለክት ተጨማሪ ማስረጃ ስለመሆኑ በምክንያታዊ አሳማኝነት አረጋግጧል፡፡ ስለሆነም ኢሰመኮ ከዚህ ቀደም ባቀረበው ምክረ ሃሳብ መሰረት የተሟላ የወንጀል ምርመራ ተደርጎ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ በድጋሚ ያሳስባል።
**
ሮይተርስ ባወጣው የምርመራ ሪፖርት " በሺሕዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ተወላጆች፣ ያለፍርድ በጊዜያዊ እስር ቤቶች ተይዘው ይገኛሉ " ብሏል። እንደ ምርመራ ሪፖርቱ መንግሥት አብዛኞቹ እስረኞች ተለቀዋል ቢልም 9,000 የሚሆኑ የትግራይ ተወላጆች አሁንም ታስረው ይገኛሉ ይላል። ሮይተርስ ከ17 የቀድሞ እስረኞች እና በሳተላይት ፎቶ ተደግፎ ባደረገው ማጣራት፣ ያለፍርድ ተይዘዋል ያላቸው እስረኞች ብዛት ተመድ ከሚገምተው ቢያንስ በ3‚000 እንደሚበልጥ ተመልክቷል።
||

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ ዶ/ር ይናገር ደሴ ዛሬ በዛሬው የአማራ ባንክ ይፋዊ ምረቃና ስራ ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ የሞባይል አገልግሎት የሚሰጡ የውጭ ተቋማት በቅርብ ጊዜ የአገልግሎት ፈቃድ ሊያገኙ ይችላሉ ሲሉ ጠቁመዋል።
||
#ማስታወሻ

የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በ #መሰቀል_አደባባይ ባዘጋጀው ስፖርታዊ ዝግጅት እና መነሻና መድረሻውን መስቀል አደባባይ በሚያደርገው የ5 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ምክንያት ነገ እሁድ ሰኔ 12 ቀን 2014 ዓ.ም ከንጋቱ 11 ከ30 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ 6:00 ሰዓት ድረስ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወሰዱ መንገዶች ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
**
አማራ ባንክ በዛሬው ዕለት ተመርቆ ሥራውን በይፋ ጀምሯል።ባንኩ 72 በሚሆኑ ቅርንጫፎቹ በይፋ ስራ መጀመራቸው ተነግሯል። አማራ ባንክ ዘመኑ የደረሰበትን የኮር ባንኪንግ ሲስተም በመጠቀም ከ165,000 በላይ ባለአክሲዮኖችን በመያዝ የተመሰረተ ባንክ ነው።
||
#ስፖርት

የሀያ ሰባተኛው ሳምንት የ ቤት ኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ በባህር ዳር ስታዲየም መካሄዱን ሲቀጥል ወልቂጤ ከተማን የገጠመው ቅዱስ ጊዮርጊስ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ መሪነቱን አስጠብቋል። በሌላ ጨዋታ ሀዋሳ ከተማ ባህር ዳር ከተማን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
8.1K viewsedited  19:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 23:42:09 #የዛሬ (ሠኔ 9/2014) #የዶሮበሽታ በኢትዮጵያ "የዶሮ በሽታ" መከሰቱን ተከትሎ ጥንቃቄ እንዲደረግ ማሳሰቢያ ተላልፏል። የኢፌዴሪ ግብርና ሚኒስቴር መረጃ እንደሚያሳየው የዶሮ በሽታ በኦሮሚያ እና አዲስ አበባ ከተማ ተከስቷል። በሽታው እስካሁን በቢሾፍቱ፣ በአቃቂ ቃሊቲ እና ኮልፌ ክፍለ ከተሞች መከሰቱን እና ከ50 ሺህ በላይ ዶሮዎች ሞተዋል። በሽታው ወደ ሌሎች አካባቢዎች እንዳይሰራጭ ልዩ…
5.3K viewsedited  20:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 20:56:12
በሶማሊ ክልል የእርሻ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተገዙ 100 ትራክተሮች ጅግጅጋ ገቡ።

በሶማሊ ክልል መንግስት በክልሉ የእርሻ ምርትና ምርታመነትን ለማሳደግ በመጀመሪያው ዙር ለመግዛት ከታዘዙ 162 ትራከተሮች መቶ (100) ትራክተሮች ጅግጅጋ ደርሰዋል። የእርሻ ትራክተሮቹ በብድር ለክልሉ አርሶአደሮች ተላልፈው የሚሰጡ መሆኑን ተገልጿል።

ትራክተሮቹ በክልሉ የእርሻ ልማትን ለማሳደግ ለተያዘው እቅድ ከዚህ ቀደም ለመግዛት ታዘው የነበሩ ሲሆን የሶማሊ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድና የክልሉ የእርሻና የተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር አብዲቃድር ኢማን ጅግጅጋ ከተማ የደረሱትን 100 ትራክተሮችን ተረክበዋል።

በዚህ ወቅት የሶማሊ ክልል ርእሰ መስተዳደር አቶ ሙስጠፌ የክልሉ ህብረተሰብ በክልሉ ያለውን ለም የመሬት ሀብት ተጠቅመው የእርሻ ምርታማነታቸውን እንዲያሳድጉ አሳስበዋል። (SRTV)

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
14.5K viewsedited  17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 17:29:03
“ማስተርካርድ ዌልነስ ፓስ” የጤና መረጃ አያያዝ መተግበሪያ ይፋ ተደረገ።

የጤና ሚኒስቴር “ማስተርካርድ ዌልነስ ፓስ” የተሰኘ የጤና መረጃ አያያዝ መተግበሪያ ይፋ አድርጓል። ሚኒስቴሩ መተግበሪያውን ወደ ሥራ ለማስገባት "ማስተር ካርድ፣ ጋቪ እና ከ ጄ ኤስ አይ" ከተሰኙ ተቋማት ጋር ስምምነት ተፈራርሟል።

"ማስተርካርድ ዌልነስ ፓስ" የተሰኘው መተግበሪያ ለ15 ወራት የሚቆይ የሙከራ ምዕራፍ በመላው ሀገሪቱ በተመረጡ የጤና ተቋማት ውስጥ የሚተገበር ይሆናል ተብሏል።

መተግበሪያው ከሌሎች የመረጃ ስርዓቶች ጋር ሊናበብ የሚችል እና አውታር መረብ በሌለበት የተገልጋዮች የህክምና መረጃን ለማንበብ የሚችል መሆኑ ተነግሯል።

የመጀመሪያ የሙከራ ትግበራ ምዕራፍ በኮቪድ-19 ክትባት ክትትል መረጃ አያያዝ ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ገልጸው፤ በዚህም1 ሚሊዮን ታካሚዎችን ተደራሽ ለማድረግ መታቀዱን ጠቁመዋል፡፡

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
19.5K viewsedited  14:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 16:57:08
በመዲናዋ "ህዝባዊ ሰራዊቱ'' ይመራበታል የተባለ አዲስ ደንብና ረቂቅ መመሪያ መዘጋጀቱን ተነገረ።

በአዲስ አበባ በአሥራ አንዱም ክፍለ ከተማ የሚገኙ ከ246ሺ በላይ የሕዝባዊ ሠራዊት አባላት ከፖሊስ ጋር በቅንጅት ለመሥራት በሚያስችለው መልኩ ከጓድ አስከ ብርጌድ ፖሊሳዊ አደረጃጀትን በተከተለ መልኩ የሪፎርም ሥራ መከናወኑ ተገለጸ።

የከተማዋ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ፤ የሠላም እሴት ዘርፍ ም/ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ እንደሰጡት ማብራሪያ በርካታ የተደራጁ ወንጀለኞችንና የሽብር ድርጊቶችን ህዝባዊ ኃይሉ ከጸጥታ ተቋማት ጋር በጣምራ ሲከላከል መቆየቱን ጠቅሰው፤ የፖሊሳዊ አደረጃጀት ሪፎርሙ ያስፈለገው አገልግሎቱን በዘላቂነት አጠናክሮ ለማስቀጠል በማሰብ ነው ብለዋል።

አዲስ የተዘጋጀው የሕዝባዊ ሠራዊት ረቂቅ ደንብና መመሪያ ትዕዛዝ ከበላይ የሚወርድበት የራሱ የዕዝ ሰንሰለት እንዲኖረው ተደርጎ የተዘጋጀ ሲሆን በተጨማሪ ተጠያቂነትንም የሚያካትት ነው ተብሏል።

በአዲሱ የሕዝባዊ ሠራዊት ረቂቅ ደንብና መመሪያ መሠረት የሠራዊቱ አባላት ማንነታቸውን የሚገልጽ የደንብ ልብስና ኃላፊነታቸውን በዝርዝር የሚገልጽ የመታወቂያ ካርድ እየተዘጋጀላቸው ምክትል ቢሮ ኃላፊዋ ተናግረዋል።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
18.4K viewsedited  13:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 16:56:49
መልኅቅ ማርኬቲንግ እና ሊደርሺፕ ኢንስቲትዩት የ11 ዓመት ልምዱን ቀንጭብ አድርጎ ለእርስዎ አመቺ በሆነ መልኩ በ2 ወር እያሰለጠነ ይገኛል። ምሩቅ፣ የሽያጭ ሰራተኛ፣ በሃላፊነት ቦታ ያሉ ሰው፣ የድርጅት ባለቤት እንዲሁም በማንኛውም ሞያ ላይ ሆነው የሽያጭ እና የግብይት፣ የዲጂታል ማርኬቲንግ እና ማይንድሴት ክህሎትዎን ማዳበር ካሰቡ እኛ ጋር ይምጡና በተግባር ይሰልጥኑ! የስራ እድል እና የምክክር አገልግሎት (Mentorship) አዘጋጅተንልዎታል። ታዲያ ምን ይጠብቃሉ? በ0967280828 ፈጥነው ይደውሉና ይቀላቀሉን!

#MelhikMarketingandLeadershipInstitute #MMLI #Salesandmarketing #Digitalmarketing #Mindset #Training
16.2K views13:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 16:56:15
Register at https://www.effsaa.org/short-term-training-program-registration-form/ after the settlement of the training fee.
Venue
At the training hall of Ethiopian Freight Forwarders and Shipping Agents Association (EFFSAA) which is located at Kazanchis, Nigist Towers Hotel & Apartments 4th Floor (In front of Elilly International Hotel)
For More Information,
Call us at +251 115 589045 / +251 903 182525
OR
Visit our telegram channel
https://t.me/EFFSAAOfficial
16.5K views13:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ