Get Mystery Box with random crypto!

Think Abyssinia

የቴሌግራም ቻናል አርማ thinkabyssinia — Think Abyssinia T
የቴሌግራም ቻናል አርማ thinkabyssinia — Think Abyssinia
የሰርጥ አድራሻ: @thinkabyssinia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 157
የሰርጥ መግለጫ

➠ ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ፣
➠ የስፓርት እና መዝናኛ ዘገባዎች፣
➠ የምሁራን እይታዎችና መጽሐፈቶች፣
➠ የአለም ሙሉ መረጃና የታሪክ መዛግብቶች ።
ለማንኛውም መረጃ ➥ @Contact_Thinkabyssinia

🎬 "ተመራጭ የዜና ምንጭ"

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2022-09-29 14:10:16
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የደንበኞች የኔትወርክ ሙከራውን በአወዳይ እና ጎንደር ከተሞች ጀመረ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በዛሬው ዕለት በአወዳይ እና ጎንደር ከተሞች  ያስጀመረው ይህ የደንበኞች ሙከራ የሳፋሪኮምን ኔትወርክ እየሞከሩ ያሉትን ከተሞች ቁጥር ዐስር የሚያደርሰው ሲሆን፤ ባለፉት አራት ሳምንታት ድሬዳዋ፣ ሐረር፣ ሐረማያ፣ ባሕር ዳር፣ አዳማ፣ ቢሾፍቱ፣ ሞጆ እና ደብረ ብርሃን ላይ ሙከራው መጀመሩ ይታወቃል፡፡

ኩባንያው እንዳሳወቀው የሁለቱ ከተሞች ደንበኞች በO7 በሚጀምረው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ መስመር የስልክ ቁጥሮቻቸውን መርጠው ሲም ካርድ መግዛት የሚችሉ ሲሆን፤ ኔትወርኩን ለአንድ ወር ያህል እንዲሞክሩት የሚረዳ የደንበኝነት ማስጀመሪያ የዳታ፣ የድምጽ እና የጽሁፍ መልዕክቶች ጥቅል የያዘ መሆኑም ተገልጿል።

በተጨማሪም ደንበኞች በኔትወርክ ሙከራው ዳታ መጠቀም፣ ጥሪዎች እና የጽሁፍ መልዕክቶችን ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እና ከኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ጋር መለዋወጥ እንዲሁም የዓለም አቀፍ ጥሪዎችን ማድረግ እንደሚችሉም ገልጿል፡፡

• @ThinkAbyssinia •
6.1K views11:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-29 12:06:26
አዲሱ የኤሌክትሮኒክ የግዥ ሥርዓት በዓመት አምስት ቢሊየን ብር ወጪ ይቀንሳል ተባለ

በተያዘው በጀት ዓመት በ73 ተቋማት እየተተገበረ የሚገኘው የኤሌክትሮኒክ የመንግሥት ግዥ ሥርዓት፣ በዚህ ዓመት ብቻ አምስት ቢሊየን ብር ወጪ ሊቀንስ ይችላል ተብሎ እንደሚጠበቅ የመንግሥት ግዥ ባለሥልጣን አስታወቀ። አዲሱ አሠራር በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት ሙሉ ለሙሉ ሲተገበር፣ የግዥ ወጪን በ50 በመቶ ይቀንሰዋል መባሉን ሪፖርተር ዘግቧል፡፡

በ18 ሚሊየን ብር ወጪ የበለፀገው አዲሱ የግዥ ሥርዓት፣ ባለፈው በጀት ዓመት በዘጠኝ መሥሪያ ቤቶች ላይ በሙከራ ደረጃ ተተግብሮ የነበረ ሲሆን፣ ግዥ ሲከናወን የሚወጡ አላስፈላጊ ወጪዎችን ከመቀነስ ባለፈ፣ ብልሹ አሠራሮችን ለማስቀረት ትልቅ ሚና ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል። በአዲሱ ሶፍትዌር ላይ ያልተመዘገቡ አቅራቢዎች፣ የፌዴራል መንግሥት ቢሮዎች በግዥዎች ላይ መሳተፍ እንደማይችሉ ባለሥልጣኑ አስታውቋል፡፡

• @ThinkAbyssinia •
7.1K views09:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-29 10:52:04
የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከሌሎች ሀገራት ጋር ያለው ንፅፅር

የንግድ እና ቀጣናዊ ትሥሥር ሚኒስቴር ትላንት ማምሻውን የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማሻሻያ መደረጉን አስታውቋል። በዚህም መሰረት ቤንዚን በሊትር - ባለፈው ወር ከነበረበት 47 ብር 83 ሳንቲም ወደ 57 ብር ከ05 ሣንቲም ከፍ ብሏል። ይህም ከአፍሪካዊቷ ሀገር አይቮሪኮስት ጋር ያለው የዋጋ ንፃሪ በ20 ሳንቲም ብልጫ አሳይቷል።

እንዲሁም ነጭ ናፍጣ በሊትር - ባለፈው ወር ከነበረበት 49 ብር 02 ሳንቲም ወደ 59 ብር ከ90 ሣንቲም ከፍ ብሏል። ይህም በጎረቤት ኬንያ ካለው ዋጋ የአንድ ብር ከዘጠና ሳንቲም ጭማሪ አሳይቷል። ኬሮሲንም በሊትር ባለፈው ወር ከነበረበት 49 ብር 02 ሳንቲም ወደ 59 ብር ከ90 ሣንቲም ከፍ ማለቱ ተገልጿል። 

ሚኒስትሩ በመግለጫው የአውሮፕላን ነዳጅ፤ ቀላል ጥቁር ናፍጣና ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሥራ ላይ የነበረው ዋጋቸው ባለበት እንዲቀጥል የወሰነ ሲሆን የታለመ ድጎማ ተጠቃሚ የሕዝብ ትራንስፖርት ተሽክርካሪዎች በሚጠቀሙት ነዳጅ ላይ በሁለተኛው ምዕራፍ ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ አልተደገረም ብሏል።

• @ThinkAbyssinia •
7.7K views07:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-28 19:32:47
ኢትዮ ቴሌኮም በከፊል ያጋጠመው የአገልግሎት መቋረጥ ሙሉ በሙሉ መፈታቱን አስታወቀ።

ኢትዮ ቴሌኮም ዛሬ በከሰዓት በአንደኛው ዋና ጣቢያው (core site) ላይ ባጋጠመው የውስጥ የኃይል አቅርቦት ቴክኒካል ችግር ምክንያት በከፊል ደንበኞቹ ላይ የአገልግሎት መቆራረጥ ችግር አጋጥሞት እንደነበርና ለተፈጠረው ችግርም ይቅርታ ጠይቆ ችግሩ ሙሉ በሙሉ የተፈታ መሆኑን አሳውቋል።

• @ThinkAbyssinia •
5.4K views16:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-28 17:48:20
አዲሱ የፋይናንስ ስርዓት ወደ ሀገር ውስጥ በሚገቡ የውጭ ባንክ ተወካዮች ዘንድ ቅሬታን ፈጠረ

በኢትዮጵያ የሚገኙ የውጭ ባንኮች ተወካዮች የውጭ ዜጎች ወደ ባንክ ዘርፉ እንዲገቡ የሚጠበቀውን አዲሱን የፋይናንስ ኮድ በቅርበት እየመረመሩ ይገኛሉ። ተወካዮቹ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቦ ተግባራዊ እንዲሆን በፀደቀው አዲሱ ፖሊሲ ላይ ቅሬታ እንዳላቸው ካፒታል ጋዜጣ አስነብቧል።

ፖሊሲው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ዘርፍ ተጫዋቾች እንደጠበቁት አይደለም ያሉ ሲሆን ይህም ብዙ እጩ ተወዳዳሪዎች ወደ ገበያው ለመግባት ፍላጎታቸው እንዲቀንስ ያደርጋል” ሲሉ ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ የውጭ ባንክ ተወካይ ለካፒታል ተናግሯል። ተወካዩ አክለውም የውጭ ዜጎች በአስተዳደርና በውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶች ላይ የሚኖራቸውን ሥልጣን መገደብ ተገቢ አይደለም ብለዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ መቀመጫውን በዩናይትድ ኪንግደም ያደረገው የቻርተርድ አካውንታንቶች እና የአስተዳደር አማካሪዎች ድርጅት ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ ጌታቸው በሻወርድ መንግስት ዘርፉን ሙሉ በሙሉ መክፈት የለበትም ባይ ናቸው። የውጪ ባንኮች ድርሻቸው ካልተወሰነ የአገር ውስጥ ባንኮችን ተወዳዳሪነት ያጠፋሉ፤ ኢኮኖሚውም ሙሉ በሙሉ በውጭ ዜጎች ቁጥጥር ስር ሊወድቅ ይችላል ሲሉ ስጋታቸውን ለካፒታል ገልጸዋል። አቶ ጌታቸው አክለውም “መንግስት አንድ ነገር ከመከሰቱ በፊት ጉዳዩን ለማከም እድሉ ስላለው የረጅም ጊዜ ጥቅሞችን እና ውጤቶችን በአግባቡ ማየት አለበትም ብለዋል።

የባንክ ዘርፉ ለውጭ ባለሃብቶች መክፈቱ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ከተቀረው አለም ጋር ያለውን ትስስር ከማጠናከር በተጨማሪ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እና እውቀትን ወደ ኢንዱስትሪው ለማምጣት ያስችላል ተብሏል።

• @ThinkAbyssinia •
7.2K views14:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-28 12:40:50
የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት ሕገወጥ ገንዘብ አስተላላፊዎችን አስጠነቀቀ

የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት ሰኞ መስከረም 16 ቀን 2015 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፣ በሕገወጥ ገንዘብ ማስተላለፍ ድርጊት መሰማራታቸውን አረጋግጫለሁ ብሎ የጠቀሳቸው አዶሊስ፣ ሸጌ፣ ሰላምና ሬድ የተባሉ የገንዘብ አዘዋዋሪዎችና የውጭ ምንዛሪ በማስቀረት በአገር ውስጥ በብር የሚከፍሉ ሌሎች አካላት፣ ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ በማሳሰብ ሕጋዊ ዕርምጃም እንደሚወስድ ማስታወቁን ሪፖርተር ዘግቧል፡፡

ተቀማጭነታቸውን በውጭ አገሮች ያደረጉና በገንዘብ ማስተላለፍ ድርጊት የተሰማሩ አካላት፣ በሕጋዊ መንገድ ውደ ኢትዮጵያ መግባት የነበረበትን የውጭ ምንዛሪ ለኢትዮጵያ ባንኮች የላኩ በማስመሰል፣ የውጭ ምንዛሪ እዚያው ሲያስቀሩ እንደነበርም አስታውቋል፡፡

ሐሰተኛ ደረሰኝ ጭምር በማዘጋጀትና በመጠቀም የውጭ ምንዛሪውን በውጭ አገሮች በማስቀረት፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የውጭ አገሮች ገንዘብ ምንዛሪና የኑሮ ውድነት እንዲባባስ በማድረግ ላይ መሆናቸውንም፣ ባገኘው መረጃ ማረጋገጡን ገልጿል፡፡ አገልግሎቱ መሰል የፋይናንስ ወንጀሎችን የሚፈጽሙ አካላትንም ሆነ ግብረ አበሮቻቸውን በሕግ ተጠያቂ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡   

• @ThinkAbyssinia •
3.7K views09:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-28 12:10:24
ኢትዮ ቴሌኮም የ”ዌስተርን ዩኒየን“ ሃዋላ አገልግሎት ጀመረ

ኢትዮ ቴሌኮም አዲስ ባስጀመረው በዚህ  አገልግሎት ደንበኞቹ በዌስተርን ዩኒየን ከባህርማዶ ሃዋላ ሲላክላቸው በአቅራቢያቸው በሚያገኙት የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎት መስጫ ማዕከላት በመሄድ፤ ምቾት እና ቅልጥፍና ከተላበሰ መስተንግዶ ጋር መቀበል እንደሚችሉ ገልጿል።

በተጨማሪም ደንበኞች ገንዘቡ በቀጥታ ወደቴሌብር አካውንታቸው እንዲዛወር ካደረጉ ደግሞ 5 በመቶውን በስጦታ እንደሚያበረክትም ኢትዮ ቴሌኮም አስታውቋል።

• @ThinkAbyssinia •
4.1K views09:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-28 12:10:03 Think አቢሲንያ pinned a GIF
09:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-28 12:09:00
ኪያድ ዳቦ እና ኬክ
Kiyad Bakery and Coffee

ለልደት፣ ለሰርግ እና ለምርቃት በፈለጉት ዲዛይን እና መጠን እናዘጋጃለን።

Bring us your cake designs! We prepare cakes for every occasion!

0911467026
0913911679

የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት ይችላሉ

https://t.me/kiyad_bakery

አድራሻ: ልደታ ፍሊንት ስቶን አካባቢ
      የልደታ የፍታብሔር ምድብ ችሎት ፊት ለፊት

https://maps.app.goo.gl/4hYtermcawkxksDH7
4.1K viewsedited  09:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-27 18:00:13 #ቲንክአቢሲኒያ_የመክሰስ_መረጃዎች

1፤ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በአርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ ሞት የተሰማቸውን ጥልቅ ኅዘን ገለፁ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ “አርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ በማረፉ የተሰማኝ ኀዘን ከባድ ነው" ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት የኅዘን መግለጫ። "ለሀገሩ በአጭር እድሜው ብዙ የሠራ ከያኒ ነው፤ ሀገር በተደፈረች ጊዜ ሕመሙን እየቻለ ግንባር ተገኝቶ ሠራዊቱን አጀግኗል፤ ሠልጣኞችን አበርትቷል፤ ነፍሱ በሰላም ትረፍ” ብለዋል።

2፤መንግስት የሰለጠኑ ባለሙያዎችን ወደ ውጭ ሀገራት መላክ ጀመረ።

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ በ2011 ዓ.ም በተለያዩ የሙያ መስኮች የሰለጠኑ ባሙያዎችን ወደ መካከለኛው ምስራቅና አውሮፓ ለመላክ ከተለያዩ አገራት ጋር የሁለትዮሽ ስምምት እየተደረገ መሆኑን በፓርለማው በተናገሩት መሰረት ወደ 180 ነርሶችና የተሽከርካሪ መካኒኮች ወደ ተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስና ኔዘርላንድ መላካቸውን ዋዜማ የስራ ክሕሎት ሚኒስቴር ሀላፊዎችን ዋቢ አድርጋ ዘግባለች።

3፤ተቋርጦ የነበረው የቪዛ ማራዘምና የመኖሪያ ፈቃድ እድሳት ተጀመረ።

ከሐምሌ 18/ 2014 ዓ.ም ጀምሮ ተቋርጦ የቆየው ቪዛቸዉ እና የመኖሪያ ፈቃዳቸው የሚፀናበት ጊዜ ከአንድ ወር በላይ ላለፈባቸው ግለሰቦች የቪዛ ማራዘምና የመኖሪያ ፈቃድ እድሳት ከመስከረም 16 2015 ዓ.ም. ጀምሮ አገልግሎቱን መስጠት መጀመሩን የኢፌዲሪ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አስታውቋል።

4፤የቀድሞው የጃፓን ጠቅላይ ሚንስትር ሺንዞ አቤን የቀብር ስነ ስርዓት ተፈጸመ።

ጃፓናውያን የቀድሞ የጃፓን ጠቅላይ ሚንስትር ሺንዞ አቤ ብሄራዊ የቀብር ስነ ስርዓት አከናውነዋል። በብሄራዊ የቀብር ስነ ስርዓቱ ላይ የሟች ባለቤት አኪ አቤን ጨምሮ በሺዎች የሚቆጠሩ ሃዘንተኞች በቶክዮ መገኘታቸው መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። በሌላ በኩል በጃፓን ለንጉሳውያን ቤተሰቦች ብቻ የሚደረገው ብሄራዊ የቀብር ስነ ስርዓት ቢያንስ 12 ሚሊዮን ዩሮ ገደማ ወጪ ማስወጣቱ አነጋገሪ ሆኗል፡፡ 

5፤ስድስት የቀድሞ የፋሲል ከነማ ተጫዋቾች በክለቡ ላይ ቅሬታቸውን አሰሙ።

ፋሲል ከነማ በ2014 ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ደረጃ ይዞ በማጠናቀቁ ለተጫዋቾቹ የ10 ሚልየን ብር ሽልማት ለማበርከት ቃል ገብቶ በቅርቡ ለአብዛኛው የቡድኑ አባላት የገንዘብ ሽልማቱን ቢያበረክትም በያዝነው ዓመት ከክለቡ ጋር ለተለያዩ ስድስት ተጫዋቾች ይህ ሽልማት አለመፈፀሙ በተጫዋቾቹ ላይ ቅሬታ አስነስቷል። ክለቡ በበኩሉ የገንዘብ ሽልማቱ የተሰጠው ከ2015 በጀት ለዚህ ዓመት ከቡድኑ ጋር አብረው ለሚገኙ ተጫዋቾች የማነቃቂያ ሽልማት መሆኑን ገልጿል።

መልካም በአል
• @ThinkAbyssinia •
4.9K views15:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ