Get Mystery Box with random crypto!

Think Abyssinia

የቴሌግራም ቻናል አርማ thinkabyssinia — Think Abyssinia T
የቴሌግራም ቻናል አርማ thinkabyssinia — Think Abyssinia
የሰርጥ አድራሻ: @thinkabyssinia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 157
የሰርጥ መግለጫ

➠ ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ፣
➠ የስፓርት እና መዝናኛ ዘገባዎች፣
➠ የምሁራን እይታዎችና መጽሐፈቶች፣
➠ የአለም ሙሉ መረጃና የታሪክ መዛግብቶች ።
ለማንኛውም መረጃ ➥ @Contact_Thinkabyssinia

🎬 "ተመራጭ የዜና ምንጭ"

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-10-09 12:12:32
በፍራንኮ ቫሉታ ለሚገቡ ዕቃዎች የውጭ ምንዛሪን ምንጭ ማሳወቅ ግዴታ እንዲሆን ተወሰነ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በፍራንኮ ቫሉታ አማካይነት ዕቃዎችን ወደ አገር የሚያስገቡ ግለሰቦች፣ የሚጠቀሙበት የውጭ ምንዛሪ የራሳቸው ስለመሆኑ የሚያረጋግጥ የባንክ ስቴትመንት እንዲያቀርቡ የሚያስገድደውን አሠራር እንደገና መጀመሩን ሪፖርተር ዘግቧል፡፡

ብሔራዊ ባንክ ይህንን ዕርምጃ የወሰደው በፍራንኮ ቫሉታ ዕቃ እናስመጣለን በማለት ከጥቁር ገበያ ዶላር እየገዙ መልሰው በማስወጣት እየሠሩ ያሉ መኖራቸውን ማረጋገጥ በመቻሉ እንደሆነ፣ የብሔራዊ ባንክ ገዥ ይናገር ደሴ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡በመሆኑም የጥቁር ገበያ ምንዛሪን ለመቆጣጠር ብሔራዊ ባንክ በፍራንኮ ቫሉታ ተጠቃሚዎች ላይ ያደርግ የነበረውን ቁጥጥር እንደገና ይጀምራል፤›› ያሉት ብለዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የዋጋ ንረቱንና ሕገወጥ የውጭ ምንዛሪ ዝውውርን ለመከላከል ከውጭ ወደ አገር የሚገቡ አንዳንድ ምርቶች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ የሚወስን መመርያ በቅርቡ ተግባራዊ እንደሚሆን ይናገር (ዶ/ር) አስታውቀዋል፡፡ ምርቶቹ መግባታቸው ጥሩ ቢሆንም አሁን ካለው የውጭ ምንዛሪ እጥረትና ከአስፈላጊነታቸው አንፃር ታይቶ፣ አንዳንድ ምርቶችን ከውጭ እንዳይገቡ ክልከላ ይደረግባቸዋል ብለዋል፡፡
2.4K views09:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-09 09:22:43
የውጭ ባንኮች እንዲገቡ የሚፈቅደው ረቂቅ አዋጅ ማሻሻያ ተጠናቀቀ

የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተወዳዳሪዎች ክፍት እንዲሆን ከተወሰነ በኋላ፣ በ2009 ዓ.ም. የወጣው የባንክ ሥራ ረቂቅ አዋጅ ማሻሻያ ተጠናቆ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ሊቀርብ መሆኑን ሪፖርተር ዘግቧል፡፡ በረቂቅ አዋጁ ላይ አብዛኛው ለውጥ የተደረገው ባለፈው ወር የሚኒስትሮች ምክር ቤት ካፀደቀው የባንኮች ለውጭ መከፈት ከፖሊሲ ጋር ለማጣጣም ነው፡፡ የውጭ ባንኮች እንዴት ወደ ኢትዮጵያ ገብተው መሥራት እንደሚችሉ ረቂቅ አዋጁ በዝርዝር ይደነግጋል፡፡

የውጭ ባንኮች እንዲገቡ አራት ተደጓሚ (Subsidiary)፣ ቅርንጫፍ (Branch)፣ የውክልና ቢሮ (Representative Office) እና በሥራ ላይ በሚገኙ የአገር ውስጥ ባንኮች ውስጥ አክሲዮን መግዛት አማራጭ ሆነው ቀርበዋል፡፡ ባንኮቹ ከአራቱ አንዱን አማራጭ ወይም ሁሉንም መጠቀም ይችላሉ ተብሏል፡፡

አንድ የውጭ ባንክ ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት ባንኮች ውስጥ አክሲዮን መግዛት ከፈለገ የሚፈቀድለት እስከ 30 በመቶ ብቻ ሲሆን የውጭ ዜጋና ባንክ ያልሆነ የውጭ ድርጅት ግን አምስት በመቶ የአገር ውስጥ ባንክ አክሲዮን መግዛት ይችላሉ፡፡ ይህ ማለት አንድ የአገር ውስጥ ባንክ ለውጭ ዜጋ፣ ለውጭ ባንክና ድርጅት መሸጥ የሚችለው ጠቅላላ አክሲዮን ከ40 በመቶ መብለጥ የለበትም፡፡

ቀመሩ የአገር ውስጥ ባንኮች በውጭ ሰዎች እንዳይዋጡና የአገር ውስጥ ባለአክሲዮኖች ዋነኛ ባለድርሻ ሆነው እንዲቀጥሉ ያስችላል ተብሎ ይታሰባል፡፡ ረቂቅ አዋጁ የውጭ ባንኮች ከአገር ውስጥ ባንኮች አክሲዮን እንዲገዙ ቢፈቅድም እንደ አዋሽና ዳሸን ያሉት አቅም ያላቸው የሀገር ውስጥ ባንኮች ከትንንሾቹ ባንኮች ድርሻ እንዲገዙ አልፈቀደላቸውም።
4.8K views06:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-09 08:10:16
አሜሪካ በ30 የቻይና የንግድ ኩባንያዎች ላይ ማዕቀብ ጣለች።

የዓለም አንደኛ እና ሁለተኛ ልዕለ ሀያል የሆኑት ሀገራት የሆኑት አሜሪካ እና ቻይና የንግድ ጦርነት ከጀመሩ ቆይተዋል። ቻይና በወታደራዊ ቴክኖሎጂ በአሜሪካ ላይ የበላይነትን መውሰዷ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደንን እንዳሳሰበ ሮይተርስ ዘግቧል። በዚህም የተነሳ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የቻይናውን ግዙፉ የሚሞሪ አምራች ኩባንያ የሆነው ያንትዝ ቴክኖሎጂ ኩባንያን ጨምሮ በ30 ኩባንያዎች ላይ ማዕቀብ ጥለዋል።

በተጨማሪ የአሜሪካ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ለቻይና ወታደራዊ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የማይክሮ ቺፕስ ምርቶቻቸውን እንዳይሸጡም እገዳ ተጥሎባቸዋል። ቻይና በበኩሏ ማዕቀቡ አሜሪካንንም ይጎዳል ብላለች። ቻይና ከሩሲያ እና ኢራን ጋር ባላት ግንኙነት ደስተኛ ያልሆነችው አሜሪካ በተለይም የሩሲያን ነዳጅ መግዛቷን እንድታቆም በመወትወት ላይም ትገኛለች።

via - Al ain
5.2K views05:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 14:05:20
የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን ማስተላለፍ ሊጀምር መሆኑ ተሰማ።

የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን ከዛሬ ጀምሮ ለተመልካቾቹ በመዝናኛ ቻናሉ ተደራሽ የሚያደርግ ይሆናል ተብሏል። ዛሬ ቀን 11 ሰዓት ላይ ማንቸስተር ሲቲ ከ ሳውዝሀምፕተን በኢቲሀድ ስታዲየም የሚደርጉት ጨዋታ በኢቲቪ መዝናኛ ቻናል የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛል።

ከፍተኛ ገንዘብ በማውጣት የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ጨዋታዎችን የማስተላልፍ መብትን የገዛው ኢቢሲ ጨዋታዎቹ እንደ ከዚህ ቀደሙ ለሀገር ውስጥ ተመልካቾች ብቻ በአንቴና ስርጭት ሳይሆን በሳተላይትም የዲሽ ስርጭት እንደሚኖረውም ተረጋግጧል። ከእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ በተጨማሪ የኳታሩ አለም ዋንጫ ሁሉንም ጨዋታዎች በኢቲቪ መዝናኛ የቀጥታ ስርጭት ሽፋን እንደሚኖራቸው ታውቋል።
4.1K views11:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 10:15:36 ቴሌ ብር ከኬንያው ኤም ፔሳ ጋር የሚያደርገው ፉክክር ቀላል ይሆንለት ይሆን


የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በአገር አቀፍ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት ማስጀመሪያ መረሐ ግብር በመስከረም 26 በወዳጅነት አደባባይ አካሂዷል፤ በዚሁ መርሃ ግብር ላይ መንግሥት በቅርቡ የኢትዮጵያ ገበያን ለተቀላቀለው ሳፋሪኮም የሞባይል ገንዘብ ዝውውር አገልግሎት መስጠት የሚችልበትን ፍቃድ ሰጥቷል፡፡ በዚህም ሳፋሪኮም በኬንያ በኤም ፔሳ የገንዘብ አገልግሎት ያገኘውን ስኬት በኢትዮጵያ ለመድገም እንደሚሠራም አስታውቋል።

#ቴሌ_ብር_እና_ኤም_ፔሳ_ንፅፅር

እኤአ በ2007 የተመሰረተው የኬንያው ኤም ፔሳ ከስድስት መቶ ሺህ በላይ አገልግሎቱን የሚሰጡለት ኤጀንቶች አሉት። በዋናነት በኬንያ፣ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ በግብፅ፣ ጋና ፣ ሞዛምቢክ ፣ ሌሴቶ እና ታንዛኒያ የሚንቀሳቀስ ሲሆን ከ51 ሚሊየን በላይ የተመዘገቡ ደንበኞች አሉት። በዓመት እስከ 314 ቢሊየን ዶላር ድረስ የሚጠጋ የገንዘብ ዝውውርም ያደርጋል።

ከተጀመረ አመት ከስድስት ወር ገደማ የሞላው የኢትዮ ቴሌኮም የቴሌ ብር አገልግሎት ደግሞ ከሁለት ወር በፊት ይፋ በሆነ መረጃ ወደ 23 ሚሊዮን የተጠጉ ደንበኞች አሉት። ከተጀመረ አንስቶም ከ34 ነጥብ 1 ቢሊዮን የሚልቅ የገንዘብ ዝውውር አድርጓል።

የግብር፣ የውሃ፣ የኤሌክትሪክ እና መሰል አግልግሎቶችን ከሚሰጡ በርካታ የመንግሥት ተቋማት፣ ከ13 ባንኮች እንዲሁም ከ22 ሺህ የንግድ ተቋማት ጋር የተሳሰረው ቴሌብር  በመላው አገሪቱ ከ79 ሺህ በላይ ወኪሎች አሉት። ቴሌ ብር በኢትዮጵያ ቀዳሚ የሞባይል ገንዘብ ማስተላለፊያ መሆኑ እድል ቢሆንለትም በዘርፉ የካበተ ልምድ ካለው ኤም ፔሳ ጋ የሚኖረው ፉክክር ቀላል አይሆንም ።

አሁን ላይ አጠቃላይ ኢትዮ ቴሌኮም ያሉት ደንበኞች ቁጥር 52 ሚሊዮን ነው። 120 ሚሊየን ከሚገመተው የሀገሪቱ ዜጋ አንፃር አሁንም ለኤም ፔሳ ያልተነካ እድል ከፊቱ አለ። እድሉን ሊሞክርም ይፋዊ ፍቃድ ተሰጥቶታል።

#ስጋት_ወይስ_በረከት

በጉዳዩ ላይ ለባላገሩ ማብራሪያ የሰጡት የምጣኔ ኃብት ባለሞያዎች ሳፋሪኮም የሞባይል ገንዘብ ማስተላለፍ በኢትዮጵያ የሞባይል ገንዘብ ማስተላለፍ አገልግሎት መስጠት  እንደሚጀምር ቀድሞም የሚታወቅ በውል ውስጥም የነበረ መሆኑን አንስተው ጉዳዩ ለህዝብ አዲስ ይሁን እንጂ ለመንግሥትም ሆነ ለሳፋሪኮም አዲስ አይደለም ይላሉ፡፡

የመንግሥት ተቋማት ወደ ግል መዛወር እንቅስቃሴ ላይ ተደጋጋሚ አስተያየት በመስጠት የሚታወቁት የምጣኔ ኃብት ባለሞያው አቶ ክቡር ገና ኢትዮ ቴሌኮም የቴሌ ብር አገልግሎት ሥራ ካስጀመረ የአንድ ዓመት ከስድት ወራት እድሜ ብቻ እንዳለው አንስተዋል፡፡

ተቋሙ አዲስ አገልግሎት እንደመጀመሩ መጠን የዳበረ ልምድ እንደሌለው ጠቁመው በዚህ ሁኔታ ላይ የኬንያው ኤምፔሳ ወደ ሥራ መግባቱ ለቴሌ ብር የሕልውና አደጋ ሊሆን እንደሚች ጠቁመዋል፡፡ በአንፃሩ ደግሞ ለዓመታ የቴሌኮሙን ዘርፍ  በሞናፖሊ (በብቸኝነት) ተቋጣጥሮት የቆየው ኢትዮቴሌኮም የትርፉ ምንጭ ገበያውን ያለ ተወዳደሪ መያዙ እንደሆነ የሚያነሱት አቶ አብዱልመናን መሃመድ  ተቋሙ  ከመንግሥት የጥበቃ  ጫንቃ ወርዶ በእግሩ እንዲቆም ተወዳዳሪ ያስፈልገዋል ባይ ናቸው፡፡

እንደ ኤም ፔሳ ያሉ ተቋማት ተወዳዳሪ ሆነው መምጣታቸው በባንክ የክፍያ ስርዓት ተደራሽ ያልሆነውን ማህበረሰብ  ክፍል ተደራሽ የሚሆንበትን ዕድል እንደሚፈጥር ያነሳሉ፡፡ ኤም ፒ ኤሳ  የውጭ ድርጅም በመሆኑ አብዛበኛውን ትረፉን የሚያሰላው በውጭ ምንዛሬ ነው የሚሉት አቶ ክቡር ገና በበኩላቸው ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ተከታታይ ዓመታት ከዶላር አንፃር የብር የመግዛት አቅሟን እያዳካመች በመሆኑ እና ተቋሙ  ለሚሰጠው የአገልግሎት ክፍያ  በብር የሚሰበስብ መሆኑ ሊያዋጣው እንደማይችል ያነሳሉ፡፡

ሳፋሪኮም በቴሌኮም አገልግሎት በተጨማሪ የሞባይል ገንዘብ ዝውውር ላይ እንዲገባ  መደረጉ ትልቁን ትርፍ  በዚህ ዘርፍ እንዲያገኝ  ዕድል ሊሰጠው እንደሚችል ጨምረው ጠቁመዋል። ኤም ፔሳ በኬንያ ከ40 በመቶ በላይ ትርፋን የሚያገኘው  በሞባይል ገንዘብ ማስተላለፍ እንደሆነም ይጠቁማሉ ።

አገሪቱ በጦርነት ኢኮኖሚ ላይ ባለችበት፣ ዓለም በሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ባልተረጋጋበት ሁኔታ ላይ ተቋማትን ለውጭ ገበያ ማቅረቡ  ከዋጋ አንፃር አዋጭ እንደማይሆን ያነሱት አቶ አብዱልመናን ኤም ፔሳን ከመጋበዙ በፊት የተወሰነ ጊዜ ቢጠበቅ የተሻለ እንደነበረ ተናግረዋል፡፡

ባላገሩ ቴሌቭዥን

  መልካም በዓል
• @ThinkAbyssinia •
5.8K viewsedited  07:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 10:15:28
5.1K views07:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 09:01:17
ስንዴ የጫነ አምስተኛ መርከብ ወደ ኢትዮጵያ እያመራ ነው ተባለ።

በተመድ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ኮንትራት የተያዘና ስንዴ የጫነች አምስተኛ መርከብ ከዩክሬን ጥቁር ባህር ወደብ ተነስታ ወደ ኢትዮጵያ እያቀናች መሆኑን የዩክሬን መሠረተ ልማት ሚኒስቴርን ጠቅሶ ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል። መርከቧ 30 ሺህ ቶን የዩክሬን ስንዴ ለኢትዮጵያ መጫኗም ታውቋል።

በተመድ ፕሮግራም አማካኝነት ዩክሬን እስከ አሁን 150 ሺህ ቶን ስንዴ ወደ ኢትዮጵያ፣ የመን፣ እና አፍጋኒስታን መላኳ ታውቋል። የሩሲያን ወረራ ተከትሎ የጥቁር ባህር ወደቦች በመዘጋታቸው ከዩክሬን ወደ ውጪ ገበያ የሚላከው እህል በመቆሙ፣ የእህል ዋጋ ሰማይ ሲነካ፣ በአፍሪካና በመካከለኛው ምሥራቅ እጥረት አስከትሏል።

  መልካም በዓል
• @ThinkAbyssinia •
6.1K views06:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 08:38:46
#መውሊድ

ቲንክአቢሲኒያ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1 ሺሕ 497ተኛው የነብዩ ሙሐመድ (ሰዓወ) የልደት በዓል (መውሊድ) በሠላም አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሠላምና የደስታ እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞቱን ይገልፃል።

  መልካም በዓል
• @ThinkAbyssinia •
6.1K views05:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 18:57:56
ሳዑዲ ዓረቢያ ወደ አሜሪካ በምትልከው የነዳጅ ዋጋ ላይ ጭማሪ አደረገች።

በሳውዲ መንግስት ቁጥጥር ስር የሚገኘው ሳዑዲ አራምኮ በህዳር ወር ወደ አሜሪካ በሚልከው ድፍድፍ ነዳጅ መሸጫ ዋጋ ላይ የ20 ሳንቲም ጭማሪ ሲያደርግ ባንፃሩ ዋነኛ የገበያ መዳረሻው በሆነው እስያ ገበያ ላይ ምንም ጭማሪ አለማድረጉን ብሉምበርግ አስነብቧል። አሜሪካ ውሳኔውን አርቆ አለማየት ነው ስትል ተችታለች፡፡

ሩሲያ ላይ በተጣለባት ማዕቀብ የተነሳ ከሰኔ ወር ጀምሮ የዓለም አቀፉ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ መቀነሱ ተገልጿል፡፡ ይሁንና በበርሜል 90 ዶላር የሚጠጋው አሁን ያለው ዋጋ ግን በዚህ አመት ወደ 20 በመቶ ከፍ ማለቱ ተገልጿል፡፡ ይህም በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሚታየው የዋጋ ግሽበት አስተዋጽኦ እያደረገ እንደሆነ የአር ቲ ዘገባ ያመላክታል።

• @ThinkAbyssinia •
5.9K views15:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 13:46:35
በድሬዳዋ የቤት ኪራይ መጨመርም ሆነ ተከራይን ማስወጣት የሚከለክለው ውሳኔ ለ5 ወራት ተራዘመ

የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በሳምንታዊ ስብሰባው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ አስተዳደሩ ከሰኔ 2014ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ወራት የቤት ኪራይ መጨመርና ተከራይን ማስወጣት የሚከለክል ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል፡፡

ስለሆነም ወቅታዊ የሀገሪቱን ሁኔታ እና የኑሮ ውድነት ከግምት በማስገባት በተከራይ ላይ የኪራይ ዋጋ መጨመርም ሆነ ከቤት ማስወጣት የሚከለክለው ውሳኔ ለሚቀጥሉት አምስት ወራት ተፈጻሚ ሆኖ እንዲቀጥል ካቢኔው ውሳኔ አሳልፏል፡፡

በተጨማሪም ካቢኔው በገበያ ትስስር ለኢንተርፕራይዞች ስለሚሰጥ የዋስትና ሽፋን መመሪያ እና የፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ፍኖተ ካርታን ጨምሮ በሌሎች ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ማሳለፉን የድሬዳዋ ከተማ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

via - fbc
• @ThinkAbyssinia •
5.1K views10:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ