ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የደንበኞች የኔትወርክ ሙከራውን በአወዳይ እና ጎንደር ከተሞች ጀመረ። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በዛሬው ዕለት በአወዳይ እና ጎንደር ከተሞች ያስጀመረው ይህ የደንበኞች ሙከራ የሳፋሪኮምን ኔትወርክ እየሞከሩ ያሉትን ከተሞች ቁጥር ዐስር የሚያደርሰው ሲሆን፤ ባለፉት አራት ሳምንታት ድሬዳዋ፣ ሐረር፣ ሐረማያ፣ ባሕር ዳር፣ አዳማ፣ ቢሾፍቱ፣ ሞጆ እና ደብረ ብርሃን ላይ ሙከራው መጀመሩ ይታወቃል፡፡ ኩባንያው እንዳሳወቀው የሁለቱ ከተሞች ደንበኞች በO7 በሚጀምረው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ መስመር የስልክ ቁጥሮቻቸውን መርጠው ሲም ካርድ መግዛት የሚችሉ ሲሆን፤ ኔትወርኩን ለአንድ ወር ያህል እንዲሞክሩት የሚረዳ የደንበኝነት ማስጀመሪያ የዳታ፣ የድምጽ እና የጽሁፍ መልዕክቶች ጥቅል የያዘ መሆኑም ተገልጿል። በተጨማሪም ደንበኞች በኔትወርክ ሙከራው ዳታ መጠቀም፣ ጥሪዎች እና የጽሁፍ መልዕክቶችን ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እና ከኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ጋር መለዋወጥ እንዲሁም የዓለም አቀፍ ጥሪዎችን ማድረግ እንደሚችሉም ገልጿል፡፡ • @ThinkAbyssinia • 6.1K views11:10