Get Mystery Box with random crypto!

FastMereja.com

የቴሌግራም ቻናል አርማ fastmereja — FastMereja.com F
የቴሌግራም ቻናል አርማ fastmereja — FastMereja.com
የሰርጥ አድራሻ: @fastmereja
ምድቦች: ዜና , ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 36.72K
የሰርጥ መግለጫ

FastMereja.net

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-06-09 17:57:23 የሸዋሮቢት ከተማ ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስቱ የሰዓት እላፊ ገደብ መጣሉን አስታወቀ፡፡
ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስቱ በሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር እና በአካባቢዋ የሚተገበሩ ክልከላ ውሳኔ አስተላልፏል።
በመሆኑም
1) መጠጥ ቤቶች እስከ ምሽት 4 ( አራት) ሰዓት
2) እግረኛ እስከ ምሽቱ 5 ( አምስት) ሰዓት
3) ባጃጅና ሞተር ሳይክል አስከ ምሽት 1( አንድ ) ሠዓት ድረስ ብቻ መንቀሳቀስ የሚችሉ መሆኑን አስታውቆ ይበልጥ በከተማዋ ሰላምና መረጋጋት እንዲፈጠር የተጣሉ ክልከላዎችን በማክበርና በማስከበር ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በሀላፊነት በመንቀሳቀስ አስታዋጽኦ እንዲያበረክቱ የሸዋሮቢት ከተማ ኮማንድ ፖስት ዛሬ ባወጣው መግለጫው አሳስቧል ፡፡

@fastmereja
5.1K views14:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-09 15:37:16
የአዲስ አበባ ነዋሪ የሆነውና በኤሌክትሪሻን ሙያ የተሰማራው አቶ አስቻለው ለገሰ በቆረጡት ልዩ ሎተሪ የ1ኛ ዕጣ የ3,500,000 ብር ዕድለኛ ሆነዋል። አቶ አስቻለው ለገሰ በገንዘቡም ወደ ንግድ ለመሰማራት እንዳሰቡ ተናግረዋል።

እንኳን ደስ አሎት $$$$$

@fastmereja
6.1K views12:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-09 12:56:23 ህፃን ልጅ የሰረቀችው ግለሰብ በፅኑ እስራት ተቀጣች!!
#FastMereja
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ህፃን ልጅ ወስዳ የጠፋችው በቁጥጥር ስር ውላ መቀጣቷ ነው የተነገረው የፍ/ቤቱ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ ወ/ሮ አመልማል ተስፋሁን ለወረዳው የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት እንዳስታወቁት ተከሳሽ ወ/ሮ ፈለቁ ጣሰው የተባለችው ግለሰብ ህፃን ልጅን ወስዳ ገንዘብ በመጠየቅ የማይገባትን ጥቅም ለማግኜት በማሰብ ሚያዚያ 22/2015 ዓ.ም ከቀኑ በግምት 9፡00 በሚሆንበት ጊዜ በሻሁራ ከተማ አስተዳደር ቀበሌ 02 ልዩ ቦታው ቀጠና 05 እየተባለ በሚጠረው ቦታ የቤት አከራይዋን የአቶ ግዛቸው አመራ ልጅ የሆነችውን ህፃን ረድኤት ግዛቸው የተባለችውን ህፃን ከረሜላ ልግዛልሽ በማለት በማታለል ሰርቃ ከተሰወረች በኋላ በተደረገው የፀጥታ አካላት ክትትል በአዲስ አበባ ፖሊስ ልዩ ቦታው እንጦጦ ተብሎ በሚጠራው ቦታ በፍተሻ ጣቢያ ላይ ሚያዝያ 23/2015 ዓ.ም ከምሽቱ በግምት 2፡00 ሲሆን ህፃኗን ይዛ እጅ ከፍንጅ የተያዘች በመሆኑ በፈፀመችው የጠለፋ ወንጀል መከሰሷን ገልፀው የአለፋ ወረዳ ፍ/ቤት ግንቦት 24/2015 ዓ.ም በዋለው ችሎት ወንጀለኛዋን ያርማል ሌሎችንም ያስተምራል በማለት በ7 ዓመት ከ2 ወር ፅኑ እስራት መቀጣቷን አስታውቀዋል፡፡

@fastmereja
6.8K views09:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-09 12:35:03
«ቃል የተገባላቸው ቤት አሁንም አለ ለማንም አልተሰጠም፣ አልተከለከሉም» የአዲስ አበባ መስተዳደር
#FastMereja
ባሳለፍነው ሳምንት በሞት ያጣናቸው ታንክ ማራኪው ሻለቃ ባሻ አሊ በርኬ ህይወታቸው ካለፈ በኋላ በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር የተሰጣቸው ቤት ተከለከሉ የሚሉ መረጃዎች በስፋት ተደምጧል። ጉዳዩን አስመልክቶ ፋስት መረጃ ወደ ከተማ መስተዳደሩ ጥያቄውን አቅርበን ነበር።

ለሻለቃ ባሻ አሊ በርኬ ቃል የገባቹለትን ቤት ለምን ሳትሰጡት ስንል የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደርን ፋስት መረጃዎች ጠይቀናል!!

«በወቅቱ ለሻለቃ ባሻ የተሰጣቸው ቤት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ካዛንቺስ የሚገኘው ተገጣጣሚ ቤት ነበር እሳቸው ደግሞ ይህን አልፈልግም ግቢ ቤት ነው የምፈልገው በማለታቸው ነው ያልገቡበት ግቢ ቤት ያለው ቤቶች ኮርፖሬሽን እንጂ ከተማ መስተዳደሩ የለውም የተሰጣቸው ቤት አሁንም ለሌላ ሰው አልተሰጠም አለ» ብለውናል።

@fastmereja
6.5K views09:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-08 20:18:50
በጉጂ ዞን እንጨት ተሸክሞ ሲሸጥ የነበረው የ7 አመት ልጅ ምስሉ በፌስቡክ ከተሰራጨ በኋላ አሜሪካ የመማር እድል አገኘ
#FastMereja
ነገሩ እንዲህ ነው ገለታ ደምቦባ ይባላል 7 አመቱ ነው ጉጂ ዞን አዶላ ሬዴ የተባለ ወረዳ ጬምቤ የተባለ አከባቢ እንጨት ሲሸጥ ፎቶ ወጣ፣ ታሪኩን የተመለከተው አሜሪካ የአሪዞና ነዋሪው አበራ ቦጋለ የትንሹን ልጅ ታሪክ ለመቀየር መወሰኑን ለቢቢሲ ተናግሯል።

መጀመሪያ ላይ ልጁ እንጨት መሸጡን አቁሞ ወደ ትምህርት ቤት በመመለስ ከአንደኛ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ያለው ወጪ ለመሸፈን ነበር የወሰንኩት ይላሉ አቶ አበራ ከቤተሰቦቻቸው ጋር ከተወያዩ በኋላ ህፃኑን እዚያ ማስተማር የብላቴናው ቤተሰብ ችግር ውስጥ ስላለ ውጤታማ ሊሆን እንደማይችል ተስማማን ብለዋል።

«ከቤተሰቦቼና ከቤተሰቡ ጋር ተነጋግረን ልጁን ወደ አሜሪካ ወስደን ለማሳደግ ተስማማን» ብለዋል።

ልጁ እንጨት በመልቀም አንድ ሰዓት በእግር ተጉዞ ከተማ እንጨት ይሸጥ ነበር።

የሕፃኑ አባት አቶ ዳምቦቢ ዎዲቦ ለቢቢሲ እንደተናገሩት አቶ አበራ ለልጁ ያሳየው መልካምነት እሱን ብቻ ሳይሆን የመንደሩን ነዋሪዎችንም አስደስቷል ብሏል።

@fastmereja
7.7K views17:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-08 20:08:26
የኦዳ ተማሪዎች በቻይንኛ ቋንቋ ውድድር ከአንድ እስከ ሶስት ወጡ!!
#FastMereja
ባለፈው ቅዳሜ የቻይና ኤምባሲ አዘጋጅነት በአዲስ አበባ በተካሄደው የቻይና ቋንቋ የንባብና የጥበባ ውድድር የኦሮሚያ ልማት ማህበር (ኦዳ ልዩ አዳሪ ት/ቤት) ተማሪዎች ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘው አሸንፈዋል።

“ከአንድ ዓመት ተኩል በላይ ቻይንኛ ተምሬያለሁ። በውድድሩ መጀመሪያ ላይ ፈርቼ ነበር። በኋላ ተረጋግቼ ችሎታዬን አሳይቼ አሸንፌ አንደኛ ወጥቻለሁ። በጣም ደስተኛ ነኝ” ብላለች ውድድሩን በአንደኝነት ያጠናቀቀችው ተማሪ ሲያኔ ታደሰ ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ

በአዲስ አበባ የሚገኘው የቻይና ኤምባሲ ለአሸናፊዋ ትምህርት ሲዘጋ ክረምት ቻይናን እንድትጎበኝ ጎብዣ አድርገውላታል።

የኦሮሚያ ልማት ማህበር በአዳማ እና ቢሾፍቱ ከተሞች ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን ከመደበኛ ትምህርት ጎን ለጎን የውጭ ቋንቋዎችን በማስተማር ላይ ይገኛል።

በአገር ውስጥ አፋን ኦሮሞ እና አማርኛ ይማራሉ፣ በተጨማሪም የአለምን ዋና ዋና ቋንቋዎች እንግሊዝኛ፣ አረብኛ፣ ቻይንኛ እና ፈረንሳይኛ ይማራሉ። እነዚህ ቋንቋዎች ከመደበኛ ትምህርት በተጨማሪ ወደ ሥርዓተ ትምህርት ተካቶ ትምህርቱ እየሰጣቸው ነው።

@fastmereja
7.3K views17:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-08 11:40:13
በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በወቅታዊ ጉዳይ የተሰጠ መግለጫ

@fastmereja
7.9K views08:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 18:14:55 የትዳር አጋሩን በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለው ፖሊስ በ 20 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጣ!

ተከሳሸ ረዳት ሳጅን መኳንንት ብርሃኑ በምዕራብ ጎንደር ዞን አዳኝ አገር ጫቆ ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤት የፖሊስ አባል ሲሆን ሚያዚያ 18 ቀን 2015 ዓም በግምት ከምሽቱ 2:00 ሲሆን ነጋዴ ባህር ከተማ ከሚኖርበት ቤት የትዳር አጋሩ የሆነችውን ረ/ሳጅን ልክነሽ የትነበርክን በትዳራቸው በነበረ አለመግባባት ምክንያት በያዘው የጦር መሳሪያ በሰደፍ አንገቷን መትቶ እንድትወድቅ በማድረግ ጀርባውን በተደጋጋሚ በጥይት ተኩሶ በመምታት እንድትሞት አድርጓል።

የአዳኝ አገር ጫቆ ፖሊስም ምርመራውን አጣርቶ ለዞን ዐቃቤ ህግ የላከ ሲሆን ዐቃቤ ህግም የኢፌድሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 539( 1-ሀ) በመጥቀስ በምዕራብ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በከባድ የሰው ግድያ ወንጀል ክሰ በማቅረብ ሲከራከር ቆይቷል።

ተከሳሽም ወንጀሉን አልፈፀምኩም ብሎ የተከራከረ ቢሆንም ፍ/ቤቱ የዐቃቤ ህግን ማስረጃ ከሰማ በሗላ ዐቃቤ ህግ እንደክሱ ስላስረዳ ተከሳሹ የዐቃቤ ህግን ክስ እንዲከላከል እድል ቢሰጠውም የመከላከያ ምስክር የለኝም ስላለ ጥፋተኛ ተብሏል።

የምዕራብ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤትም የዐቃቤ ህግን እና የተከሳሹን የቅጣት አስተያየት ካዳመጠ በሗላ ዛሬ በቀን 30/ 09/2015 ዓም በዋለው ችሎት ተከሳሹንና ሌሎችን መሰል የወንጀል ድርጊት የሚፈፅሙ ግለሰቦችን ያስተምራል ያርማል ያለውን የ20ዓመት ፅኑ እስራት ቅጣት ወስኖበታል።

መረጃው የምዕራብ ጎንደር ዞን ፍትህ መምሪያ ነው።

@fastmereja
9.3K viewsedited  15:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 14:29:55 የአዲስ አበበ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በኢማሞች ህብረት የተሰጠ የአቋም መግለጫ

በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሸገር ከተማ እየተፈፀመ የሚገኘዉን የመስጅድ ፈረሳ በመቃወም በአዲስ አበባ ከተማ በታላቁ አንዋር እና ኑር መስጅዶች ህዝበ-ሙስሊሙ ድምፅ በማሰማቱ ምክንያት በተከሰተዉ ችግር በሰዉ ሕይወት እና አካል ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ብዙ ዜጎች በህግ ጥላ ስር ይገኛሉ፡፡
በሸገር ከተማ እየተካሄደ የሚገኘዉ የመስጆዶች ፈረሳ ፍፁም ተገቢ ባለመሆኑ የምናወግዝ መሆኑን እየገለፅን የሚመለከተው አካል አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጥ የኢማሞች ሀብረት ጥያቄውን ያቀርባል፣
በተጨማሪም የኢማሞች ሀብረት በሸገር ከተማ እየተፈፀመ የሚገኘዉን የመስጅድ ፈረሳ እና ከዚህ ጋር በተያያዘ በምዕመናን ላይ የተወሰደዉን ተገቢ ያልሆነ እርምጃ በፅኑ እያወገዘ የሚከተሉትን ባለ 5 ነጥብ የአቋም መግለጫ አዉጥቷል፡፡
1. ከዛሬ ቀን ጀምሮ እስከ ዙልቂዕዳ ወር መጨረሻ ድረስ በሁሉም መስጅዶች ቁኑት እና ዱዓ አንዲደረግ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፣
2. በሁሉም መስጂዶች የፊታችን ጁሙዓ የኩጥባ ይዘት በሠላም፣ በአንድነት እና በሰብር ላይ እንዲያተኩር እና ህብረተሰባችን ይበልጥ በሚረዳው በአማርኛ ቋንቋ ዳዕዋ እንዲደረግ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
3. በነገዉ እለት ሐሙስ ዙልቂዕዳ 19 ፤ 1444 ዓ.ሂ ሙስሊሙ ማህበረሰብ በመፆም፤ በሰደቃ፣ በዱዓ እና በኢስቲግፋር ወደ አላህ በመቃረብ እና አላህ የተፈጠረውን ችግር እንዲያነሳልን እንዲለምን ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
4. በተፈጠረዉ ችግር ሕይወታቸዉ ያለፈ እና የተጎዱ ቤተሰቦችን ሙስሊሙ ማህበረስብ የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ባዘጋጀው የባንክ ቁጥሮች እንዲረዳ ጥሪያችንን እያስተላለፍን፡፡
5. በመጨረሻም የጁምዓ ሰላታችን በሠላም ተሰግዶ አንዲጠናቀቅ እና ሙስሊሙ ማህበረሰብ በሰላም ወደ ቤቱ እንዲመለስ ጥሪያችንን እያቀረብን አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ የመጣውን በላእ እንዲያነሳልን እና እንዲመልስልን እንለምነዋለን፣

አላሁ አክበር !!!
@fastmereja
9.1K views11:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 08:38:30 «የጸጥታ ሃይሎች እያሰሩን ገንዘብ እየወሰዱና እያሰቃዩን ነው» የሸገር ከተማ ነዋሪዎች
#FastMereja
የቀድሞ ፊንፊኔ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን የነበረው አሁን የሸገር ከተማ አስተዳደር ተብሎ በዘንድሮ አመት ምስረታ ያደረገ ከተማ ነው። ከተማዋ ከተመሰረተችበት አላማዎች አንዱ ህብረተሰቡን በልማት ተጠቃሚ ማድረግ አንዱ ነው። ከተማዋ በስሩ የተለያዩ ክፍለ ከተማ እና ወረዳዎች ተዋቅራ ተመስርታለች።

ነገር ግን ዘረፋ፣ ማስፈራራት እና በዘፈቀደ ማሰር የተለመደ እየሆነ መምጣቱን ነዋሪዎች ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ተናግረዋል የህብረተሰቡ ቅሬታ በፋስት መረጃ በዚህ መልኩ ይቀርባል።
እነዚህ ድርጊቶች በዋናነት የሚፈጸሙት በጸጥታ ሃይሎች ማለትም በፖሊስ፣ ሚሊሻ፣ ​​የወንጀል መርማሪዎችና የጸጥታ ሃይሎች መሆኑን ነዋሪዎች ለቢቢሲ መናገራቸውን ፋስት መረጃ ተመልክቷል።

በቡራዩ ከተማ ከ15 ዓመታት በላይ የኖረው ነጋሳ ለቢቢሲ እንደተናገረው በጸጥታ ሃይሎች ሁለት ጊዜ ተይዞ እንዲፈታ ገንዘብ መክፈሉን ይናገራል። የመጀመሪያ ቀን መጠነኛ የመኪና አደጋ ደርሶብኝ ወደ ሆስፒታል እየሄድኩ በሚሊሻ ተያዝኩ ከዛ ፖሊሶች በፓትሮል ይዘውኝ ሄዱ ምንም ሳልጠየቅ ታስሬ ቆየሁ ከዛ 20ሺ ብር ከፍዬ ወጣሁ ከወጣሁ በኋላ 10ሺ ብር ከፈልኩ በአጠቃላይ 30ሺ ብር መክፈሉን ነጋሳ ለቢቢሲ ገልፇል። የታሰርኩበትን ምክንያት ስጠይቃቸው ከተማ ቁጭ ብለህ ለሸኔ ሎጂስቲክ ታመቻቻለህ የሚል ምላሽ ሰጡኝ ነው የሚለው።

ሌላኛው አቶ ገምታ የተባለ አስተያየት ሰጪ ለቢቢሲ ሲናገር “የጸጥታ ሃይሎች ሰላማዊ ዜጎችን ማሰር እና ገንዘብ መቀበል የተለመደ ተግባር አድርገውታል። ወንጀል የፈፀመ አካል ከተያዘ እና ከተጠየቀ እኛም አንቃወምም። ነገር ግን ከዚያ ውጪ ይህ እየሆነ ነው” ይላል ጋምታ

ገምታ መንግስት ሰራተኛ ሲሆን ከስራ ወጥቼ ወደ ቤት እየሄድኩ እያለ በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ታፍኜ ታሰርኩ ይላል በእስር ቤት ቆይታውም “ወንጀለኛ መርማሪዎች እና ፖሊሶች ሰዎች ከእስር ቤት ለመውጣት ገንዘብ እንደከፈሉ የሚነግሩበት ኮድ [ምልክት] አላቸው” ብሏል። ብዙ ሰዎች ለመልቀቅ ገንዘብ ከፍለዋል ይላል።

ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ነቢራ ይባላል በሸገር ከተማ የግል ስራ አለው ከታሰረ በኋላ 100,000 ብር እንዲከፍል ቢነገረውም ለመክፈል ፈቃደኛ ባለመሆኑ ለአራት ወራት ያህል ታስሯል።

"መንግስት ለፖሊስ የሚከፍለው ህዝብ ለመጠበቅ ነው እንጂ ህዝብን ለመዝረፍ አይደለም" የፀጥታ ሃይሎች ዘረፋው የእለት ቋሚ ስራቸው እየሆነ ነው ብሏል።

ምርመራ ክፍል አስገብተው ገንዘብ ነው የሚጠይቁት እምቢ ካልክ ሸኔ ነህ፣ መሳሪያ ትነግዳለህ እያሉ የማታውቀውን ነገር ይለጥፉበሃል ብሏል ረቢራ።

ሁሉም ታሳሪዎች ለቢቢሲ እንደተናገሩት ፍርድ ቤት ቀርበው እንደማያውቁ ግማሹ ከፍሎ እንደወጣ አልከፍልም ያለው ለወራት ታስሮ እንደተለቀቁ ነው የሚናገሩት።

ቢቢሲ የሸገር ከተማ አስተዳደር የጸጥታ ሃላፊ ኮማንደር ሌንጂሶ ጆቴ ከነዋሪው በጸጥታ ሃይሎች ላይ ስለቀረበው ክስ ጠይቋል ተጠይቀው ይህን ብሏል "የሸገር ከተማ 12 ክፍለ ከተማ እና 36 ወረዳዎች ያሏት ሲሆን እስካሁን ድረስ እንዲህ አይነት ቅሬታ አላገኘንም" ብሏል።

"ማንም ሰው በአካል መጥቶ እኔንም ሆነ ለሌሎች ጥቆማ ሊሰጠን ይችላል" ብሏል።

አሻዋ ሜዳ እየተባለ የሚጠራው አካባቢ በጸጥታ ሃይሎች ህዝቡን እያስፈራሩ እና እያሰሩ በማሰቃየት "ቤርሙዳ" የሚል ስያሜ ወጥቶለት ነበር አሁን የሸገር ከተማ ከተመሰረተች በኋላ በፖሊስ ጣቢያ የስነምግባር ችግር ባለባቸው የጸጥታ አካላት ላይ እርምጃ መወሰዱን ኮማንደር ሌንጂሶ ተናግረዋል።

ዘገባው ረጅም ሲሆን ቀሪው በቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ላይ ይገኛል።

@fastmereja
9.2K views05:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ