Get Mystery Box with random crypto!

FastMereja.com

የቴሌግራም ቻናል አርማ fastmereja — FastMereja.com F
የቴሌግራም ቻናል አርማ fastmereja — FastMereja.com
የሰርጥ አድራሻ: @fastmereja
ምድቦች: ዜና , ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 36.72K
የሰርጥ መግለጫ

FastMereja.net

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 22

2020-11-30 15:32:01 ዛሬ በክቡር ጠቅላይ ሚንስትራችን በፓርላማ የተሞገሱ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች እና የጀግናዉ መከላከያ ሰራዊታችን አመራሮች
1. ድል ቁርሱ ጀነራል ብርሃኑ ጁላ
2. ትንታጉ ሌ/ጀነራል አበባዉ ታደሰ
3. ነበልባሉ ሌ/ጀነራል ባጫ ደበሌ
4. ሀገር ወዳዱ ሌ/ጀነራል ዮሃንስ ገብረመስቀል
5. የወገን አቅም ገንቢዉ ሌ/ጀነራል ሀሰን ኢብራሂም
6. ግስላዉ ሌ/ጀነራል ጌታቸዉ ጉዲና
7. አነፍናፊዉ ሌ/ጀነራል አስራት ዲናሮ
8. የጦርነት ሊቁ ሜ/ጀነራል አለምሸት ደግፌ
9. ሰዉ ሀይል አመጋጋቢ ሜ/ጀነራል ሀጫሉ ሸለማ
10. አይበገሬዉ ሜ/ጀነራል ዘዉዱ በላይ
11. ሳተናዉ ሜ/ጀነራል በላይ ሥዩም
12. ልበ ቆራጡ ሜ/ጀነራል መሰለ መሰረት
13. ሎጂስቲክስ አሳላጩ ሜጀር ጀኔራል አብዱራህማን እስማኤል
14. ንስሩ ሜ/ጀነራል ሹማ አብደታ
15. አርዕድ አንቀጥቅጡ ሜጀር ጀነራል ይልማ መርዳሳ
16. ነጎድጓዱ ሜ/ጀነራል ሰለሞን ኢተፋ
17. ንስሩ ሜ/ጀነራል ብርሃኑ በቀለ
18. ካርታን እንደ ምድር አንባቢዉ ብ/ጀነራል ተስፋዬ አያሌዉ
19. ጀግናዉ ብ/ጀነራል ግርማ ከበበዉ
20. ቆራጡ ብ/ጀነራል ናስር አባዲጋ

@FastMereja
10.1K views12:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-11-30 12:02:20 በመከላከያ ውስጥ የነበረውን የትግራይ ተወላጆች የበላይነት በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ተዘርዝሮ ተነግሯል

መከላከያ ውስጥ የሙሉ ጀነራል ማዕረግ 60 በመቶ በትግራይ ተወላጆች የተያዘ ነበር፤ የሌሎች ብሄሮች ድርሻ 40 በመቶ ብቻ ነበር፤

ሌተናል ጄነራል የትግራይ ተወላጆች 50 በመቶ ድርሻ ነበራቸው፤

ሜጀር ጀነራል የትግራይ ተወላጆች 45 በመቶ ድርሻ ነበራቸው፤ በብርጋዴር ጀነራል ማዕረግ የትግራይ ተወላጆች 40 በመቶ ድርሻ ነበራቸው፤

በኮሎኔል ደረጃ 58 በመቶ የትግራይ ተወላጆች ድርሻ ነበራቸው፤

በሌተናል ኮሎኔል ደረጃ 66 በመቶ በትግራይ ተወላጆች የተያዘ ነበር፤

በሻለቃ ማዕረግ 53 በመቶ በትግራይ ተወላጆች የተያዘ ነበር፤

እዞች ውስጥ አዛዥ መቶ በመቶ በትግራይ ተወላጆች የተያዘ ነው፤

ምክትል አዛዥ መቶ በመቶ በትግራይ ተወላጆች የተያዘ ነበር፤ በሁሉም የሰሜን እዝ ላይ አዛዥ እና ምክትል አዛዥ ሎጂስቲክ እና አስተዳደር በትግራይ ተወላጆች የተያዘ ነው፤

ክፍለ ጦሮች ውስጥ የኢትዮጵያ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦሮች መቶ

በመቶ አዛዦቹ በትግራይ ተወላጆች የተያዙ ናቸው፤

እግረኛ ክፍለ ጦሮች 80 በመቶ በትግራይ ተወላጆች የተያዘ ነው፤

በመከላከያ ዋና መምሪያ ውስጥ 80 በመቶ በትግራይ ተወላጅ የተያዘ ነበር፤

ሜካናይዝድ ብርጌዶች 85 በመቶ እግረኛ ብርጌድ 80 በመቶ በትግራይ ተወላጆች የተያዘ ነበር፤

በመከላከያ ስልጠና ተቋማት ውስጥ 85 በመቶ በትግራይ ልጆች ነው የሚመራ ነበር፤

EPA
-------------
@fastmereja
9.6K views09:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-11-28 20:32:46 የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጀነራል ብርሀኑ ጁላ ጀግናው ሠራዊታችን መቀሌን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠሩን አረጋገጡ ።
9.9K views17:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-11-27 11:23:16 የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ኅዳር 24 እና 25 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ገለጸ።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ኅዳር 24 እና 25 ቀን 2013 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ገለጸ።ቢሮው ተማሪዎች በተገለጹት ቀናት ወደ መፈተኛ ጣቢያዎች በመገኘት ፈተና እንዲወስዱ ጥሪ አቅርቧል።

[AMN]
-------------
@fastmereja
12.6K views08:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-11-26 09:24:59
የመጨረሻው የዘመቻው ምዕራፍ ተጀምሯል።
22.3K views06:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-11-25 20:04:44 በየሄደበት ሁሉ በሁለቱም እጆቹ ላይ ሁለት ሰዓቶችን ያጠልቃል፤ አንደኛው የሀገሩን የአርጀንቲናን የሰዓት አቆጣጠር ይከተላል፤ ሁለተኛው ሰዓት ደግሞ የሚሄድበትን ሀገር ሰዓት ይቆጥራል

ዛሬ ግን የአርጀንቲናውም የአለሙም ሰዓት ቆሟል። ዲያጎ አርማንዶ ማራዶና የእግር ኳሱ ንጉስ ከዚህች አለም በሞት ተለይቷል

የጊዜ መቁጠሪያው የ24 ሰዓት ርዝመት፣ የሰዓቱ የ60 ሰከንድ መዘውር ማራዶናን በ60 አመቱ በቃህ ብሎት ቆጠራውን አቁሟል። በእግሩም በእጁም እግር ኳስን እንደፈለገው ያሾረው ባለ ዘውድ ንጉስ ትዝታውን ትቶ አልፏል... ነፍስ ይማር!!!
Via: ታምሩ አለሙ
-------------
@fastmereja
11.5K views17:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-11-24 12:08:53 መንግሥት የሰጠውን የ72 ሰዓት ጊዜ በመጠቀም እጅግ በርካታ የትግራይ ሚሊሻና ልዩ ኃይል አባላት በየግንባሩ እጅ እየሰጡ ነው ።

መንግሥት የሰጠውን የ72 ሰዓት ጊዜ በመጠቀም እጅግ በርካታ የትግራይ ሚሊሻና ልዩ ኃይል አባላት በየግንባሩ እጅ እየሰጡ መሆኑን የአስቸኳይ ጊዜ መረጃ ማጣሪያ አስታወቀ።

በአፋር ክልል በኩል ብዙዎች ገብተው እጅ የሰጡ ሲሆን በማይጸብሪ ተቆርጦ የቀረው ኃይል እጁን በሰላም በመስጠት ላይ መሆኑም ተገልጿል።

ጥሪውን ሰምተው እጅ በመስጠት ላይ ለሚገኙ የትግራይ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ አባላት ለሕዝባቸው በማሰባቸው መንግሥት ምስጋናውን ያቀርባል።

በጁንታው ኃይል ተጽዕኖ ውስጥ ሆናችሁ እጅ ለመስጠት ያልቻላችሁ ሁሉ በያላችሁበት ትጥቃችሁን ፈትታችሁና የጁንታው መጠቀሚያ ከመሆን ተቆጥባችሁ መከላከያ እስከሚደርስላችሁ እንድትጠብቁ በአጽንዖት እናሳስባለን።
-------------
@fastmereja
12.5K views09:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-11-24 11:57:59 የ12ኛ ክፍል ፈተና ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ

@fastmereja
10.4K viewsedited  08:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-11-22 14:32:25 ሰበር ዜና

የመከላከያ ሠራዊታችን ከአዲግራት ወደ መቀሌ በሚወስደው መንገድ የምትገኘውን እዳጋ ሐሙስ ከተማን ተቆጣጥሯል። የመከላከያ ሠራዊቱ የዘመቻው የመጨረሻ ግብ የሆነችውን መቀሌን ለመያዝ እየገሠገሠ ነው።

የመከላከያ ሠራዊቱ ከሰሞኑ ሽሬን፣ አክሱምን፣ አድዋንና አዲግራትን ከጁንታው ነጻ ማውጣቱ ይታወቃል።

@fastmereja
12.6K viewsedited  11:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-11-21 19:42:42 በአክሱም አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ጉዳት መድረሱ ተጠቆመ

በመሰረተ ልማቶች ላይ ከፍተኛ ውድመት እየፈጸመ በመሸሽ ላይ የሚገኘው የሕወሓት ህገወጥ ቡድን በአክሱም አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ጉዳት ማድረሱ ተጠቆመ።
የቱሪስት መዳረሻ በሆነችው የአክሱም ከተማ የተገነባው የአውሮፕላን ማረፊያ በ526 ሚሊዮን 860 ሺህ 200 ብር ወጪ የተገነባ መሆኑን፣ ለአካባቢው ማህበረሰብና ለአገር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅሙ ሰፊ እንደነበር ተገልጿል።
የአየር ማረፊያው መጎዳት የአክሱም ሐውልትን ከጉዳት ለመታደግ የሚደረገውን የጥገና ስራ እንደሚያስተጓጉልና በርካታ ችግር ሊያስከትል እንደሚችል ተጠቁሟል።
አውሮፕላን ማረፊያው በቱሪስቶች የሚታወቅ፣ በቀንና በምሽት አገልግሎት የሚሰጥ፣ የተሟላ እንደነበር ይታወቃል ሲል የዘገበው ሪፖርተር ነው።
------------
@fastmereja
12.8K viewsedited  16:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ