Get Mystery Box with random crypto!

በትረማርያም አበባው

የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው
የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው
የሰርጥ አድራሻ: @betremariyamabebaw
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.25K
የሰርጥ መግለጫ

አቀድም አእኵቶቶ ለእግዚአብሔር

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-04-27 15:20:23
#ክቡር #ሊቀ #ሊቃውንት #ያሬድ #ሽፈራው
ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ትልቅ ባለውለታ ናቸው። ለሀገራችንም ቢሆን የግእዝ ቋንቋ እንዳይጠፋ የቅኔ የምስክር መምህራንን እያስመረቁ ቅኔ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች በተለይም በጎጃም፣ በጎንደር፣ በሸዋ፣ በወሎ፣ በትግራይ በስፋት እንዲሰጥ ምክንያት ናቸው። ከእርሳቸው ያስመሰከሩ መምህራን በጣም ብዙ ናቸው። አሁንም በማስተማር ላይ ይገኛሉ። ልዑል እግዚአብሔር እድሜ ማቱሳላን ይስጥልን።
2.2K views12:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 14:08:19 መስክ ስለሆነ በራሱ ኃጢአት አይደለም። ሰው ካመለከው ግን እግር ኳስ ብቻ ሳይሆን እርሻም ንግድም እንጀራም ዳቦም ጣዖት አምልኮ ነው። በተረፈ እግር ኳስ ተመልካች ጣዖት አምላኪ ነው የሚል ትምህርት ግን የለም። ምናልባት ከመበለቶች መጽሐፍ ከተገኘ እንጃ። የመበለት አጫዋቾችን ጠይቁ። አንዱ ስለዶሮ ብልት ይተነትናል። አንዱ ወንጌል በሚነገርበት ዓውደ ምሕረት ስለኳስ ይሰብካል። እረ ተው ጎበዝ እንዳታስቀስፉን። መጋቤ ኳስ ወቡና ወዶሮ ብልት ወእንቁላል እየሆናችሁ ስንት አመስጥሮ ያላትን ቤተክርስቲያን በእናንተ ተራ ወሬ አታሰድቧት ለማለት ያህል ነው።

ሌላው የምዕራባውያን የሆነውን ሁሉ እንደ ርኩስ መቁጠር ነውር ነው። መልካሙን መያዝ ክፉውን መተውን እንልመድ። ምዕራባውያንን መጥላትምኮ ክርስትና አይደለም። ክርስትና ሁሉንም ሰው መውደድ ነው። ለይተን ክፉ ሥራቸውን ለመጥላት እንሞክር። በአሁኑ ጊዜኮ ከእኛ አይብሱም። በሚልየን ሕዝብ የተገዳደልን እኛ ነንኮ። ከእኛም ከእነርሱም ክፉውን እንተወው። ከእኛም ከእነርሱም መልካሙን እንያዝ። በኳስ ምክንያት፣ በእርሻ ምክንያት፣ በትምህርት ምክንያት፣ እና በመሳሰሉት ከቅዳሴ መቅረት አይገባም። አንድ ሰው በእነዚህ ምክንያት ከቅዳሴ ስለቀረ ግን ትምህርት፣ እርሻ፣ ኳስ፣ ጽሕፈት ጣዖት አምልኮ ናቸው አይባልም።

ፍልጢ አርዌ ምድር___አንቺ እባብ ለዪ

መ/ር በትረማርያም አበባው
2.0K views11:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 14:08:18 _ወንጌልንና ተረት ተረትን እንለይ__
በተለይም ማንኛውም ሰው ጉባዔ ያልዋለበትን እና ያላደላደለውን መጽሐፍ ቅዱስ በራሱ መሰለኝ መተርጎም አይገባም። ጥቅስን ለራስ ዓላማ ማዋል ሰይጣናዊ ጠባይ ነው። ጌታን እንዲህ ተብሎ ተጽፏል ብሎ ሰይጣን ለራሱ ዓላማ መጽሐፍ ቅዱስን ጠቅሶ ነበር። ነገር ግን ጌታ እንዲህም ተብሎ ተጽፏል ብሎ ነገሩን ከንቱ አድርጎበታል። ያልተማሩትን ቃል መጥቀስ ያላሳደጉትን ውሻ ጆሮ እንደመቆንጠጥ ነው። ያ እንዲናከስ። ይህም ያሰናክላል። አጥዐወ ጣዖት አመለከ ከሚለው የግእዝ ግሥ "ጣዖት" የሚል ምዕላድ ይወጣል። ጣዖት ምሥጢራዊ ትርጓሜው ሳይፈጥር የሚመለክ የሚፈራ ማለት ነው። ሰማይንና ምድርን የፈጠረ አንድ አምላክ ነው ያለው። ሳይፈጥሩ በውሸትና በተንኮል የሚመለኩ ፍጥረታት ጣዖታት ይባላሉ። እግዚአብሔር ግን ፈጥሮ የሚገዛ ስለሆነ ከእኔ ውጭ ሌላ አምላክ አታምልክ ብሎ ተናግሯል። ዘጸ. ፳፣፪ "ወይቤ አነ ውእቱ እግዚእ እግዚአብሔር ዘአውፃእኩከ እምድረ ግብፅ እምቤተ ቅንየት። ጽኑ አገዛዝ ከምትገዛበት ከግብፅ አገር ያወጣውህ ፈጥሬ የምገዛህ እግዚአብሔር እኔ ነኝ። ኢታምልክ አማልክተ ወኢምንተኒ ዘእንበሌየ። አሁንም ያለ እኔ ምንም ምን ሌላ ባዕድ አምላክ አታምልክ። ካለ በኋላ ቁጥር ፭ ላይ ኢትስግድ ሎሙ ወኢታምልኮሙ ይላል። አትስገድላቸው ተብሏል። ይህ ስግደት የአምልኮ ስግደት ነው። አምልኮ ተገዢነትን፣ ፈሪሕን፣ አክብሮን፣ እና ሰጊድን አጠቃሎ የያዘ ቃል ነው። ራእየ ዮሐንስ ፳፪፣፲፭ ላይ እንደተገለጸው አምስቱ ውሾች ከተባሉት አንዱ "ጣዖት አምላኪ" ነው። ጣዖት አምላኪ የሚባለው እንጨት ጠርቦ፣ ድንጋይ አለዝቦ አምላኬ ነህ ፈጣሪዬ ነህ የሚልና ራሱ ለሠራው ጣዖት መሥዋዕትን የሚያቀርብ አሳዛኝ ሰው ነው። ማንኛውም ሃይማኖተኛ ከሁሉም በፊት ሊጠብቀው የሚገባ ሕግ "ከእኔ በቀር ሌላ አምላክ አታምልክ" ያለውን ቃል ነው። እግዚአብሔርን ትቶ በሌላ ያመለከ ሰው ጣዖት አምላኪ ይባላል። ዋናው የፍቅረ እግዚአብሔር መገለጫ እግዚአብሔርን ማምለክ ነው። እግዚአብሔርን የማምለክ መገለጫው ደግሞ ተጠምቆ ቆርቦ የእርሱ የጸጋ ልጅ ሆኖ፣ ምሥጢራትን መፈጸምና መልካም ሥራን መሥራት ነው።

አንድ እግዚአብሔር አንድ አምላክ አንድ ሃይማኖት እያለ ይህ ሁሉ እምነት ከምን መጣ? ማቴ. ፲፫፣፳፭ "ሰዎቹ ሲተኙ ግን ጠላቱ መጣና በስንዴው መካከል እንክርዳድን ዘርቶ ሄደ" ተብሎ እንደተገለጸው ክፉ አስተሳሰብንና ትምህርትን ሰይጣን በሰዎች ልቡና እያሳደረ ብዙ ቤተ እምነቶች እንዲመሠረቱ ሆኗል። በተጨማሪም በጉሥዐተ ልብ (በልብ ወለድ) ሰው የራሱን መሰለኝ ሃይማኖታዊ አስተምህሮ እያደረገ ቤተእምነት እስከመመሥረት ደርሷል። በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አርዮሳውያን ያደረሱት በደል የጉሥዐተ ልብ ውጤት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ትቤ ጥበብ ፈጠረኒ አብ መቅድመ ኩሉ ተግባሩ ያለውን ጥቅስ ያለ አግባብ ጠቅሶ ጥበብ ወልድ ነው። ስለዚህ ወልድን አብ ፈጠረው ብሎ የራሱን መሰለኝ የሃይማኖት አስተምህሮ አስመስሎ አቀረበ። ነገር ግን ዝቅ ብሎ ቢያየው እምቅድመ አድባር ወአውግር ወለደኒ ሲል ያገኘው ነበር። ፈጠረ ወለደ ተብሎ ይተረጎማል። ወለደም ፈጠረ ተብሎ የሚተረጎምበት ወቅት አለ። ኦሪት ዘልደት ባለ ጊዜ ኦሪት ዘፍጥረት ማለት መሆኑን ልብ ይሏል። የራስን መሰለኝ የሃይማኖት አስተምህሮ አድርጎ ማቅረብ ይህ ሁሉ ቤተ እምነት እንዲፈበረክ ምክንያት ሆኗል። ጣዖት ማምለክን ሴሩህ ጀምሮታል። ይህ ሴሩህ ብኑ የሚባል ልጅ ነበረው። በሕፃንነቱ ተቀሠፈበት። ይወደው ነበርና እንቅበረው ቢሉ ከመውደዱ የተነሣ አላስቀብርም አለ። ሲወጣ ሲገባ ልጄ ብኑ፣ ልጄ ብኑ እያለ ኀዘን ጸናበት። የሀገሩ ሰዎች ወጥቶ በሄደበት ያንን ልጅ ቀብረው እንጨት ጠርበው ጆሮ፣ አፍንጫ፣ ዓይን፣ እጅ፣ እግር ቀርጸው ቀለም ቀብተው ቀሚስ አጥልቀው በኋላው አቁመው ልጅህ ተነሣልህ አሉት። ልጄ ብኑ ነህን አለው። በዚያ በእንጨት ያደረ ሰይጣንም "እ" አለ። አምላክ ካልሆነ ተነሥቶ ተነጋገረውን? ብለው የሚያመልኩበት ሆኗል። ንጉሠ እስራኤል ዳዊት ስለጣዖታት በመዝ. ፻፲፫፣፲፫-፲፭ ላይ "አፍ አላቸው አይናገሩም። ዓይን አላቸው አያዩም። ጆሮ አላቸው አይሰሙም፣ አፍንጫ አላቸው አያሸቱም፣ እጅ አላቸው አይዳስሱም፣ እግር አላቸው አይሄዱም___" ብሎ ተናግሯል። ጣዖት የሚባሉት እንዲህ ናቸው። ሰው ያመልካቸዋል እንጂ ማንንም አልፈጠሩም። በማንም ላይም ጉዳትን አያመጡም። ደካሞች ናቸው። ሰው ዝም ብሎ ነው የሚፈራቸው።

የሰው ልጅ ጥሮ ግሮ ይበላ ዘንድ ከፈጣሪው ትእዛዝ ተሰጥቶታል። ስለዚህም ሰው በተለያዩ የሥራ መስኮች ተሰልፎ ይሠራል። ያርሳል፣ ይቆፍራል፣ ይጽፋል፣ ይደጉሳል፣ ይሮጣል፣ ቤት ይሠራል፣ ወዘተ። ይህንን ሥራውን ደግሞ በየዘመናቱ በተሠሩ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ያሳልጣል። ለምሳሌ በበሬ ያርስ የነበረው በትራክተር እያለ ድካሙን ይቀንሳል። ነገር ግን አዳዲስ የቴክኖሎጂ ውጤቶች በተሠሩ ቁጥር ተፈጥሮን እና ለሰው ልጅ ጥበብን የሰጠ እግዚአብሔርን ከማመስገን ይልቅ ሰይጣናዊ አሠራር አድርጎ የማቅረብ ክፉ ልማድ አለ። ለምሳሌ በአጼ ምኒልክ ዘመን ስልክ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያ ሲመጣ እና ንጉሠ ነገሥቱ ሲነጋገሩበት የሰሙ አንዳንድ ቄሶች ንጉሡ ከሰይጣን ጋር ተነጋገረ ብለው እንደነበር ይነገራል። ሕዝቡም ስላልተማረ የእነ ቄሴ ንግግር ለተወሰነ ጊዜ ተስማምቶት ነበር። በኋላ ዓይናማ ሊቃውንት ከንጉሡ ጋር ሲሆኑ ውሸት እየቀለለች መጣች። ብዙ አትፍረዱባቸው። ብዙ ያልተማረ ሰው ትምህርቱ ካለቀበት አላዋቂ መባልን ስለሚፈራ እርሱ የማያውቀውን ነገር ሁሉ ከሰይጣን ጋር ያያይዘዋል። በእርግጥ ትሕትና ያለው ከሆነ ዝቅ ብሎ ይማራል። ምሁራኑ ሊቃውንቱ ግን የማያውቁት ጉዳይ ከገጠማቸው አላውቀውም ይላሉ እንጂ በግምት አይናገሩም።

ስፖርት ከሳይንስ ክፍሎች አንዱ ነው። በውስጡም ብዙ ዘርፎች አሉት። ሩጫ፣ ውርወራ፣ ዝላይ፣ እግር ኳስ፣ መረብ ኳስ፣ ቅርጫት ኳስ፣ ፈረስ ጉግስ፣ ዋና እና የመሳሰሉት የስፖርት ዓይነቶች ናቸው። እነዚህ ነገሮች እንኳንስ ጣዖት አምልኮ ሊሆኑ በራሳቸው ኃጢአት ሊሆኑ እንኳ ፈጽሞ አይችሉም። ጣዖት አምልኮ የሃይማኖት ነው። ኃጢአት ደግሞ በሃይማኖት ውስጥ ያለ ሰው ሆኖ ምግባረ ጽድቅን አለመሥራት ነው። በሀገራችን ሀገራችንን በበጎ ያስጠሩ እነ አትሌት አበበ ቢቂላ፣ እነ መሠረት ደፋር፣ እነ አትሌት ደራርቱ ቱሉ፣ እነ ቀነኒሳ በቀለ፣ እነ ጥሩነሽ ዲባባ እና ሌሎችም ይጠቀሳሉ። ሩጫ አንድ የሙያ ዘርፍ ነው። ስለዚህ በሩጫው ዓለም ያላችሁ ውድ ክርስቲያኖች ካላችሁ በርትታችሁ ሥሩና እንደቀደሙ ወንድሞቻችንና እኅቶቻችን ኢትዮጵያን በዓለም መድረክ አሳውቋት። እግር ኳስ አንድ የሙያ መስክ ነው። በእግር ኳስ ያላችሁ ወንድሞች ጠንክራችሁ ሥሩና ሀገራችሁን በሙያችሁ አስጠሯት። ይህ ሥራችሁ ጽድቅ ነው አንልም። ኩነኔም እንዳልሆነ ግን አስረግጨ እናገራለሁ። ቤተክርስቲያን ዘፋኝነትን ነው አጥብቃ የምትቃወመው። ስለዚህ ዘፋኞች ደግሞ ንስሓ ገብታችሁ ሌላ ሙያ ቀይሩ። ስፖርተኛ ስፖርት ሠርቶ አሥራቱን ለቤተክርስቲያን ይስጥ። አራሽም አርሶ አሥራቱን ለቤተክርስቲያን ይስጥ። የዘፋኝንና የዘማውያንን አሥራት ግን ቤተክርስቲያን አትቀበልም። መጀመሪያ ንስሓ መግባት አለባቸውና። ስለዚህ እግር ኳስም ልክ እንደ እርሻ እና ንግድ ሁሉ አንድ የሥራ
1.8K views11:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 14:06:51
1.6K views11:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 11:55:09 +
፬:- ሕፃን ያገኘ ሰው ቢኖር ባዕለጸጋ ቢሆን ወስዶ ሊያሳድገው ይገባል።
+
፭:- ሩቅ ሀገር የሄደ ሰው የሄደበት ቦታ ባይታወቅ በሕይወተ ሥጋ መኖሩ አለመኖሩ ባይታወቅ ገንዘቡ ቢገኝለት ወደዳኛ ይውሰዱት።
+
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
ክፍል ፳፫ ይቀጥላል
መ/ር በትረማርያም አበባው
1.7K views08:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 11:55:09 __ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፳፪___
አንቀጽ ፴፮
ይህ አንቀጽ መጠመን ማስጠመን (መከራየትና ማከራየት) እንዲገባ ይናገራል። (በእንተ ተዐስቦ ነው)።
፩) ተዐስቦ ረብሕ ጥቅም ለማግኘት በመጠመን በማስጠመን ጊዜ በቃል የሚዋዋሏት ውል ናት። ዋጋው አስጠማኝ በቆረጠው ሊሆን ይገባል።
+
፪:- የመጠመን የማስጠመን ሥርዓት በተጠማኝ በአስጠማኝ ፈቃድ እንጂ ያለእነዚህ ፈቃድ አይጸናም አይፈጸምም። አስጠማኝ ለተጠማኝ ከብቱን መሬቱን አሳይቶ አስታውቆ መስጠት ይገባዋል። በሥራም ቢሆን መጠመን ይገባል። ይኽውም ልብስ ለመስፋት ከብት ለመጫን መጠመን ነው።
+
፫:- መጻሕፍት መምህራን የከለከሉትን መጠመን ማስጠመን አይገባም።
+
፬:- ልብስ ለሚሰፋ ለሚያጥብ፣ ለእንጀራ ጋጋሪ፣ እነዚህን ለመሰሉት ሁሉ ሥራቸውን ሳይፈጽሙ ዋጋቸውን ስጡን ማለት አይገባም። ሥራቸውን ከፈጸሙ በኋላ ቢሆን ነው እንጂ።
+
፭:- ባለቦታ በዋጋዋ ከተዋዋለ በኋላ ቢያድሩም ባያድሩም ከተዋዋላቸው ሰዎች የቦዘኑበትንም ያደሩበትንም የማደሪያ ዋጋ ይቀበል።
+
፮:- ሠራተኛ ሁሉ ዋጋውን እስኪቀበል ድረስ የሚሠራውን መያዝ ይገባዋል። (ሐተታ) ቀለም አግቢ ልብሱን፣ አንጥረኛ ጻሕሉን መያዝ ይገባዋል።
+
፯:- ማናቸውንም የተጠመነ ሰው በእርሱ እጅ ሳለ ቢጠፋ፣ ጥፋቱ በተንኮል በቸልታ ካልሆነ መክፈል አይገባውም።
+
፰:- በዓለ ሐመር ከባልንጀሮቹ ተለይቶ አክብዶ ቢጭን፣ ነፋስ ማዕበል ሞገድ በተነሣበት ጊዜ በሰባራ በአሮጌ መርከብ ጭኖ ቢያሰጥም መክፈል ይገባዋል። ቸል ባይል ግን መክፈል አይገባውም።
+
፱:- ለልብስ አጣቢ ከሰጡት ልብስ አይጥ ቢበላበት መክፈል ይገባዋል።
+
፲:- ተጠማኙን ጥፋት ክፋት እንዲያገኘው እያወቀ ማናቸውንም ገንዘብ ያስጠመነ ሰው ባይነግረው መክፈል ይገባዋል። ዘንዶ እባብ ያለበት ፈት ቦታ እንደማስጠመን ያለ ነው።
+
፲፩:- ቤትን ለውሽባ ቤትነት መጠመን ማስጠመን አይገባም። ዘር ለመዝራት መሬት መጠመን ማስጠመን ይገባል።
+
፲፪:- እስከዚህ ቦታ እሄዳለሁ ብሎ ከብት የተጠመነ ሰው አልፎ የሄደ ቢሆን ብትጠፋ መክፈል ባትጠፋ አልፎ የሄደበትን ጨምሮ መስጠት ይገባዋል።
+
፲፫:- ቦታ የተጠመነ የገዛ ሰው ቢኖር ለማደር የማያበቃ ነውር ቢያገኝበት ውሉን ማፍረስ ይገባዋል።
+
፲፬:- አናጢ ሥራውን ከፈጸመ በኋላ ዋጋውን መቀበል ይገባዋል።
+
አንቀጽ ፴፯
ይህ አንቀጽ የሁሉ መሄጃ የአውራ ጎዳናውን፣ የሁሉ መውጫ መጋጫ ሜዳውን፣ ቤት የመሥራትን ነገር፣ በእርሻና በእርሻ መካከል የሚሄድ የውሃን ጎዳና ነገር ይናገራል።
፩) የአንድነት ቤት ካላቸው ሰዎች አንዱ ከባልንጀሮቹ ፈቃድ ወጥቶ ጠባቂ ሹም መሾም አይገባውም። የአንድነቱንም አጥር ቅጥር አንዱ ማፍረስ ወይም መሥራት አይገባውም። በባልንጀራው ፈቃድ ቢሆን ነው እንጂ።
+
፪) አንድ ሰውስ እንኳ በአንድነቱ አጥር አጠገብ የማድ ቤት፣ የውሽባ ቤት መሥራት አይገባውም።
+
፫) አንድ ሰው በደርብ ያሉትን ሰዎች የሚያፍናቸው ጢስ የሚወጣበት ማድ ቤት የውሽባ ቤት ቢሠራ ጢስ ከማጤስ ይከልከል። በደርብ ያሉትም ምድር ቤት ያሉትን እንዳያሳዝኗቸው እጣቢውን ማፍሰስ ጥራጊውን መጣል አይገባቸውም።
+
፬) ሰው ሁሉ በቤቱ ጎረቤቱ የሚያዝንበትን ሥራ መሥራት አይገባውም።
+
፭) አንድ ሰው ቅጽር ሊሠራ ቢወድ ከባልንጀራው አንድ እርምጃ ርቆ ይሥራ። ቤት ቢሆን ስድስት እርምጃ ርቆ ይሥራ። የውሃ ጉድጓድ ቢሆን አምስት ክንድ ይሁን። (ይህ በዘመናቸው የነበረ ሲሆን በአሁን ዘመን ላይሠራ ይችላል። ምክንያቱም የቤት አሠራሩ የቀድሞውና የአሁኑ የተለያየ ነውና)
+
፮:- ዳኞች የተወሰነውን መመርመር ይገባቸዋል። ወጉን ታሪኩን ማጥናት መመርመር ይገባቸዋል። ቃል ለቃል ሲያያዝ የመጣውን፣ ከልማደ ሀገር የተገኘውን ማወቅ መመርመር ይገባቸዋል።
+
፯:- ቅጽሩ ወደጎዳና አዘንብሎ ሰዎች አፍርስልን ብለውት ሳያፈርስ ቀርቶ ተንዶ ሰው ቢጎዳ ባለቤቱ መክፈል ይገባዋል።
+
አንቀጽ ፴፱
ይህ አንቀጽ የተአምኖን ነገር ይናገራል።
፩) ራሱን የቻለ አካለ መጠን ያደረሰ ሰው በእውነት በደሉን ቢናገር ኃጢአት ስለሠራ ንስሓ ይገባዋል። ገንዘብ ሰርቄያለሁ ቀምቻለሁ ቢል ገንዘብ መክፈል ይገባዋል።
+
፪:- ብድሩን የሚከፍለውን ያጣ ድኃ አለብኝ ቢል ይጸናል። ያን ጊዜ መክፈል አይገባውም። ሲያገኝ ይክፈል እንጂ።
+
፫:- አንድ ሰው ለጽንስ ከርስቱ ቢያዝለት፣ ገንዘብ ጽፎም ቢያዝለት ሕያው ሆኖ ከተወለደ ይጸናለታል።
+
አንቀጽ ፵
ይህ አንቀጽ ጠፍቶ ስለተገኘ ገንዘብ ይናገራል።
፩:- ለወንድምህ የጠፋውን ገንዘብ መልስለት። ምንም ቅርብህ ባይሆን ሰውየውንም ባታውቀው ወደቤትህ አግባው። ወንድምህ አምጣ እስኪልህ ድረስ በአንተ እጅ ይቀመጣል። ካገኘህበት ቦታ ወስደህ ሰባት ቀን መልኩን ዓይነቱን ሳይናገር ገንዘብ የጠፋው ይበል። ዓይነቱን በትክክል ተናግሮ ባለቤቱ የእኔ ነው ቢል ያገኘው ሰው በዳኛ ፊት ይመልስለት።
+
፪:- በጠፋበት ጊዜ ባለቤቱ ያልታወቀለት ገንዘብ ያገኘ ሰው፣ ባለቤቱን የሚያውቅ ቢመጣና ምልክቱን የሚናገር ቢመጣ፣ የእርሱ እንደሆነ የልቡናውን ጥርጥር ቢያርቅለት ገንዘቡ እንደመሆኑ ይመልስለት። ያለዚያ ግን ገንዘቡ ጥቂት ቢሆን መብላት መጠጣት ይገባዋል።
+
፫:- ገንዘብ ያገኘ ሰው ገንዘቡ ከተገኘበት ሀገር ካሉ ሰዎች ወገን ባይሆን በዳኛ እጅ በዳኛ እጅ ያኑረው። ሊያስመረምርም ቢወድ እንደወደደ ያድርግ። ከምርምሩ ቀን በኋላ አንድ ሰው መጥቶ የጠፋው ገንዘብ የእርሱ እንደሆነ ቢናገር፣ ገንዘቡ ባገኘው ሰው እጅ ቢኖር ይመልስለት። ቢሸጠውም ዋጋውን ይመልስለት። ቢበላው ባለጸጋ ቢሆን መሰሉን መክፈል ይገባዋል። ድኃ ቢሆን የተረፈውን መመለስ ይገባዋል። ከገንዘቡ ባይተርፍ ግን ምንም ምን ክፈል አይበሉት።
1.7K views08:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 11:25:36 _ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፳፩__
አንቀጽ ፴፫ ስለመሸጥና ስለመግዛት ይናገራል።

እሑድ፣ በጌታችን በዓላትና በእመቤታችን በዓላት መሸጥ መግዛት አይገባም። [አክብሩ ያለውን ሥርዓር ማፍረስ ነውና። ቁጥር ፲፻፩፻፬]

፩) ሻጭና ገዥ በገንዘባቸው ቢያዙ ቢሰለጥኑ ነው እንጂ ካላዘዙ ካልሰለጠኑ መሸጥ መግዛት አይጸናም አይፈጸምም። አውቀው ወደው መዋዋል ይገባቸዋል።
+
፪) ሻጭና ገዢ በዋጋ ሳይስማሙ ቢለያዩ መሸጥ መግዛት ትቀራለች። መሸጥ መግዛት በሁለቱ ፈቃድ ነውና።
+
፫) በደብዳቤም ያለ ደብዳቤም የሚሆን መሸጥና መግዛት አለ። ደብዳቤ የሚናገረው በዋጋ መስማማታቸውን፣ ውሉን፣ የሚሸጡትን የከብቱን አኳኋን፣ የዋጋውን ቁጥር፣ የቀኑን ልክ፣ ዓመተ ምሕረቱን ነው። ያለ ደብዳቤ የሚሆን ዋጋ ዐረቦኑን (ቀብዱን) በመቀበል ይሆናል። ያለ ዐረቦንም ይሆናል።
+
፬) ሻጭ ቦታ የሚሸጥ ከሆነ ለይቶ ይሽጥ። ተክሉንም ይጨምራል ወይስ ቦታውን ብቻ የሚለውን ለይቶ መንገር አለበት።
+
፭) ሻጭ ለገዢ የሸጠለት ንብረት ቢጠፋ ከሻጩ እንዳለ ከጠፋ ገዢው አይጠየቅም። ገዢው ከተረከበ በኋላ ቢጠፋበትም ሻጭ አይጠየቅም።
+
፮) የተሸጠው ነገር ከተሸጠ በኋላ እጅ እግሩ ቢሰበር ዓይኑ ቢጠፋ፣ ቤት ቢሆን ቢቃጠል፣ ሀገር ቢሆን በመላው ውሃ ቢተኛበት፣ ወይም የተወሰነው ቢጎደጉድ፣ ናዳ ቢወስዳት፣ ቤቶቿ ቢፈርሱ፣ ዛፎቿ እየተነቀሉ ቢወድቁ አንድም ቢደርቁ፣ ይህ ሁሉ ሲሆን በሻጭ ምንም ተንኮል ሳይኖርበት የተደረገው ሁሉ ለገዥ ሀብቱ ነው። ሻጭ ከዕዳ ይድናል።
+
፯) ከብት የሸጠ ሰው ቢኖር ገዡ እስኪፈትነው ሦስት ቀን ወይም አራት አምስት ቀን ይስጠው። ፈተናውን ባይወጣ ገዢ ለሻጩ መመለስ ይገባዋል። ገዢ ከወደደውና በኋላ ግን የራሱ ይሆናል።
+
፰) ሰው ሁሉ ንግድ አወቅሁ ብሎ ከሚገባው ዋጋ አዋርዶ መግዛት ነውር ነው። [ቁጥር ፲፻፺፫]። ሻጭ ለገዢ የሸጠለት ተዋጊ በርጋጊ አበያ በሬ መሆኑን ሳይነግረው ከሆነ፣ ሌላም ነገር ቢሆን ነውሩን ሳይነግረው ከሸጠለትና ገዢው በኋላ ቢያውቅ ሻጭ ለገዢው መክፈል ይገባዋል።
+
፱) [ቁጥር ፲፻፺፯] ያመኑትን አገልጋዮች ላላመኑ ሰዎች መሸጥ አይገባም። ለቤተክርስቲያን የጎለቱትን ጉልት መሸጥ አይገባም። ጠብቅልን ብለው በአደራነት የሰጡትን በገንዘብ መሸጥ አይገባም።
+
፲) ይዞ መስጠት የማይቻለውን መሸጥ አይገባም። ይኽውም ምሳሌ በወንዝ ያለውን ዓሣ ሽጨልሀለሁ ወንዙ የእኔ ነው ዓሣውን ሽጨልሀለሁ አይበል። በክንፍ የሚበረውን ቆቁን ጅግራውን ሽጨልሃለሁ አይበለው። አዳኝ በዱር ያለውን ፌቆውን ዋልያውን ድኩላውን ሳይያዝ መግዛት አይገባውም።
+
፲፩) ለጣዖት የተሠዋውን፣ ሙቶ ያደረውን፣ የአውሬውን ትራፊ፣ በመርዛቸው የሚገድሉ እንስሳትን ሥጋ፣ የሚገድሉ መርዛም እፀዋትን፣ አራዊትን መግዛት አይገባም።
+
፲፪) ፈጽመው የማይረቡትን የማይጠቅሙትን መሸጥ መግዛት አይገባም። ፅንሱን ከእናቱ ለይቶ መሸጥ አይገባም። ፍሬው ሳያፈራ ቡቃያውን፣ ሳይታለብ ወተቱን፣ በማድጋ ውስጥ ያለውን ማር ሳያሳዩ መሸጥ ሳያዩ መግዛት አይገባም።
[ሐተታ እስከ ሥዑል ሚካኤል ድረስ ይሸጥ ነበር። በሥዑል ሚካኤል ጊዜ አንድ ሰው የቅሉን የዱባውን አንጀት ጨምሮ ላዩን ማር ቀብቶ ሽጧል። ከዚያ ወዲህ ሻጭም አሳይቶ ገዢም አይቶ ይግዛ ተብሎ አዋጅ ተነግሯል]
+
፲፫) የአንድነት ቦታዎችን መሸጥ አይገባም። ይኽውም አውራ ጎዳናን፣ የሁሉ መውጫ መጋጫ ሜዳን፣ ወንዝን መሸጥ አይገባም። ጡት ሳይተው ጥጃን ወይም ሌላን እናቱን ከልጇ ለይተው መሸጥ አይገባም።
+
፲፬) ከሌባ መግዛት አይገባም። ጥፋትን ለሚያመጡ ሰዎች መሣርያ መስጠት አይገባም። ጽፈው ያዘዙለት ሐፃኒ ከሕፃናቱ ገንዘብ ማናቸውንም መግዛት አይገባውም።
+
፲፭) እሑድ፣ በጌታችን በዓላትና በእመቤታችን በዓላት መሸጥ መግዛት አይገባም። [አክብሩ ያለውን ሥርዓር ማፍረስ ነውና]
+
አንቀጽ ፴፬
ይህ አንቀጽ ስለተሳትፎ ይናገራል። ተሳትፎ የሚለው አንዱ በከብት አንዱ በጉልበት ሆነው የሚነግዱት ንግድ ነው።
+
፩) ተሳትፎ በገንዘብ በማይተካከሉ ሰዎች መካከል ትጸናለች። ገንዘብ የሌለው ድኃ በትርፉ አንድም በጉልበቱ ፈቃዱን ይፈጽማልና። [ድኃ በጉልበቱ ባለጸጋ በከብቱ እንዲሉ]
+
፪) በተሳትፎ የገንዘቡ ልማትም ጥፋትም ለሁለቱም ሊሆን ይገባል። በአንድነቱ ገንዘብ ለባልንጀራው ቀርቶበት አንዱ ብቻ ሊያዝበት አይገባውም።
+
፫) አንድነት ከገቡ ሰዎች ሁሉ እያንዳንዱ በቃን በቃን ቢሉ፣ አንዱ አንዱን ሽማግሌ ልኮ ገንዘቤን ስጠኝ ቢለው፣ በዳኛ ቢይዘው አንድነት ትቀራለች። ትቅር።
+
አንቀጽ ፴፭
ይህ አንቀጽ ስለ አገብሮና ስለ ተኃይሎ ይናገራል። አገብሮ የሚለው የግድም የውድም የሆነን ነገር ነው። ተኃይሎ ግን የግድ የሆነ ነገር ነው።
፩:- አገብሮ ሃይማኖትህን ካድ ብሎ ቢያገብረው በፍጹም ልቡናው ቢያምን መከራውን እንጂ አገብሮውን መቀበል ፈጽሞ አይገባም።
+
፪:- ሃይማኖቴን አልክድም ብሎ መከራ የሚቀበል ሰው በሰማዕትነት ቢሞት ሰማዕት ዘበደም ይባላል። ለሃይማኖቱ የታመነ ምስክር ሆኖ ከመከራ ቢድን ሰማዕት ዘእንበለ ደም ይባላል።
+
፫:- አንዱ አንዱን ሕግ አፍርስ፣ ነፍስ ግደል፣ ሰስን ብሎ ቢያገብረው አገብሮውን መቀበል አይገባም። ያገኘውን መከራ ታግሦ መቀበል እንጂ።
+
፬:- (ተኃይሎ) ቀማኛ ባዕለጸጋ ቢሆን) በአንድ አራት በአንድ አምስት ይክፈል። ይህን ካልተቻለው እትፍ ይክፈል። ይህንም ካልቻለ ዓይነታውን ይመልስ። (ሐተታ) ምእመናንን ከሰደበ ኤጲስ ቆጶሱን የሰደበ ሰው ቅጣት ይጸናል።
+
፭:- የሰው ልብስ የቀደደ ሰው ጉዳያውን (የተቀደደውን የሚተካ) ይክፈል።
+
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
ክፍል ፳፪ ይቀጥላል
መ/ር በትረማርያም አበባው
1.9K views08:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 17:25:52 __ዲድስቅልያ ክፍል ፭__
√አንቀጽ ፳፭
፲፯:- የሙታን ትንሣኤ በክርስቶስ ዳግም መምጣት ነው።
፳፰-፴:- ትንሣኤ ሙታን የለም የሚሉ ወንጀለኞችን ስሙ ፊንክስ የሚባል ተፈጥሮው አንድ የሚሆን ወፍ ያስረዳቸዋል። ወደ አመድነት ከተለወጠ በኋላ በትል መልኩ እንደገና ታድሶ ይነሣል
፴፪:- ሰውን ካለመኖር የፈጠረ እግዚአብሔር በፍጹም ከሃሊነቱ ሙታንን ማስነሣት አይችልምን?? (ያስነሣል)።
√አንቀጽ ፳፮
፩:- እነሆ ሰማዕታትን ከፍ ከፍ አድርጓቸው ፈጽማችሁም አክብሯቸው።
√አንቀጽ ፳፯
፩:- የምትወደዱ ወንድሞች ሆይ ዘፈንን ከማድመጥና ከጨዋታ ነገር፣ ከተድላ ደስታና ከመባልዕት ጣዕም፣ ረብህ ጥቅም ከሌለው ከብላሽ ሥራም ሁሉ ትርቁ ዘንድ በጎ ምክርን እንመክራችኋለን።
√አንቀጽ ፳፰
፳:- በራስህ አትማል። አላዋቆች አይሁድ በራሳቸው ይምላሉና።
፳፩:- የምእመናን ነገራቸው እውነቱን እውነት ሐሰቱን ሐሰት ማለት ነው።
√አንቀጽ ፳፱
፩-፱:- የበዓላትን ቀን ጠብቁ። እነዚህም በዓለ ልደት ታኅሣሥ ፳፱፣ በዓለ ጥምቀት ጥር ፲፩
፲-፲፪:- በሆሣዕና ማግሥት ሰኞ ቀን ሕግንና ሃይማኖትን የካዱ ክፉዎች አይሁድ ተሰብስበው በጌታ ላይ ተማክረዋል። ማክሰኞ ቀን ምክርን ጨመሩ፣ በረቡዕ ቀን ምክርን ፈጸሙ።
፷፰:- የተለየች የፋሲካ ጾምን ስድስት ቀን እንጹም።
፷፱:- ዳግመኛም ዓርብ ረቡዕን እንጹም።
፸:- በቀዳሚት ሰንበት እንዳንጾም መሆን አገባብ ነው። መከራን ከተቀበለባት ከቀዳም ሥዑር በቀር።
√አንቀጽ ፴
፩:- የሕማማትን መታሰቢያ በዓመት አንድ ጊዜ ያድርጉ።
፰:- ትንሣኤ በተቀደሰች የክርስቲያን ሰንበት ይሁን።
፲-፲፪:- በሕማማት ሳምንትም በጨው ከተሠራ ቂጣና ከውሃ በቀር ምንም አትብሉ አትጠጡ። የቻለ በየሁለት ቀኑ ይጹም። ያልቻለ በቀን በቀን ይጹም።
፴፰:- ጌታ ካረገም በኋላ በአሥረኛው ቀን በዓለ ሃምሳ ሲፈጸም በዓልን አድርጉ።
√አንቀጽ ፴፩
፵፯:- የእግዚአብሔር ልጅ ወልድ በማርያምና በዮሴፍ ሩካቤ በሥጋ ፈቃድ ተወለደ የሚሉ ከኃድያን ፍዮኒዮክን ይባላሉ።
√አንቀጽ ፴፫
፵፮-፵፯:- የእሪያዎች ሥጋ ንጹሕ ነው የሚሉ አሉ። ነገር ግን ርኩስ ነው እንጂ ንጹሕ አይደለም። በመጽሐፍ ንጹሕ የሆነውን ግን ከእርሱ ይብሉ። (ይህ ሥርዓት ልክ ኤጲስ ቆጶስ አንድ ያገባ ይሁን እንደሚለው በሐዋርያት ዘመን የነበረ በኋላ በሠለስቱ ምእት የተሻሻለ ነው። ስለዚህ በአሁኑ ሰዓት እርያ የሚበላ ርኩስ ነው አይባልም)።
√አንቀጽ ፴፫
፭:- (ስለ ሥላሴ) ሁለት አይደለም። በሦስትነቱም አራተኛ አይጨመርበትም። ብቻውን ለዘለዓለሙ የሚኖር አንድ ነው እንጂ።
፲፬:- እንግዲህ የእግዚአብሔር ፍጥረት ሁሉ መልካም እንደሆነ እንናገራለን።
፺፯:- እናንተ ግን ልጆቻችሁን ሕፃናት ሳሉ አጥምቁ። መንፈሳዊ ምግብንም መግቧቸው። በምክርና በጥበብም አሳድጓቸው።
፻፴፬:- ሥርዓት ጽድቅ ነው።
፪፻፳፰:- ሴቶች ለባሎቻቸው በፍቅርና በፍርሀት ይታዘዙ። ክብርት ሣራ ለባሏ ለአብርሃም ትታዘዘው ጌታዬም ትለው እንደነበረ። ጌታዬ አለቃዬ ትለው ነበር እንጂ በስሙ አትጠራውም ነበርና።
፪፻፴:- የልጅነት ሚስትህን ውደድ። የአንተ ናትና። ሁልጊዜም ከአንተ ጋር ትኖራለችና። አካልህም ናትና።
√አንቀጽ ፴፬
፩-፪:- ስለሞቱ ሰዎች ቅዱሳት መጻሕፍትን አንብቡ። ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙንም በምስጋና በቤተክርስቲያን አሳርጉላቸው። በመቃብርም የዳዊትን መዝሙር በፊታቸው አንብቡ።
፱:- የሞቱትን ሰዎች በድን በዳሰሳችሁ ጊዜ አጽማቸውን መሸከም አትጸየፉ። ስለእነርሱ የምትረክሱ አይደላችሁምና።
√አንቀጽ ፴፭
፯-፰:- ማንንም እንዳትጠሉ ዕወቁ። ሰውን ሁሉ አትጥላ። ግብፃዊውንም ቢሆን ኤዶማዊውንም ቢሆን ሁሉም የእግዚአብሔር ፍጥረቶች ናቸውና።
፱:- ነገር ግን ከክፉ ሰዎችና ከዚህ ዓለም ፈቃድ ራቅ።
፴፪:- ቁጡና ቀናተኛ አትሁን።
፴፰:- በአንተ ላይ የሚመጣውን መከራ ሁሉ ተቀበል። እንደ ኢዮብና እንደ አልዓዛር ከእግዚአብሔር ዋጋህን ትቀበል ዘንድ።
፵:- የእግዚአብሔርን ቃል ያስተማረህን አክብር። በቀንና በሌሊትም አስበው።
፵፪:- ጠብ ያለባቸውን ሰዎች አስታርቃቸው በእውነትም ፍረድ። ፍርድ ለእግዚአብሔር ነውና።
፵፰:- ለንጉሥም ተገዛ ሹመቱም ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደሆነ እወቅ። ገዢዎችን አክብር። እነርሱ የእግዚአብሔር መልእክተኞች ናቸውና።
፵፱:- ከክፉ ሥራህ ሳትመለስ ክፉ እየሠራህ መሥዋዕትን አታቅርብ።
√አንቀጽ ፴፮
፰:- አሥራትንም ሁሉ ለባልቴቶችና ለድሃ አደጎች፣ እናት አባት ለሞቱበት ለእንግዶች እና ለድሆች ስጡ።
√አንቀጽ ፴፯
፪:- የመላእክት የወገን ስማቸው መላእክት፣ መናብርት፣ ሥልጣናት፣ አጋዕዝት፣ ኃይላት፣ ሊቃናት፣ ኪሩቤል፣ ሱራፌል ይባላሉ። ሌትና ቀንም እግዚአብሔርን ያመሰግናሉ።
√አንቀጽ ፴፰
፲፪:- ጌታ በሰንበት እናርፍ ዘንድ አዘዘን። ከሥራው ሁሉ ያረፈባት ቀን ናትና።
፲፭:- (የክርስቲያን ሰንበትንም እናክብር)
√አንቀጽ ፴፱
፩:- ለሚጠመቅ ሰው (ንዑሰ ክርስቲያን) የምክር ቃልን ያስተምሩት።
፲፪:- ሊጠመቅ የሚወድ ንዑሰ ክርስቲያን ሰይጣንን ያውግዝ። በክርስቶስ ስም ይመን። የቀደመ ልማዱንም ይተው።
√አንቀጽ ፵
በማይ ላይ ስለሚጸለይ ጸሎት ይናገራል።
√አንቀጽ ፵፩
በሜሮን ላይ ስለሚጸለይ ጸሎት ይናገራል።
√አንቀጽ ፵፪
ሐዲስ አማንያን ሲጠመቁ የሚጸለይ ጸሎትን ይናገራል።
√አንቀጽ ፵፫
በሐዋርያት ስለተሾሙ ኤጲስ ቆጶሳት ስም ዝርዝር ይናገራል።
++++++
ተፈፀመ
አነሳስቶ ላስጀመረን
አስጀምሮም ላስፈጸመን
ልዑል እግዚአብሔር
ምስጋና ይገባል አሜን።
መ/ር በትረማርያም አበባው
1.2K views14:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 16:32:51 __ዲድስቅልያ ክፍል ፬____
_አንቀጽ ፲፪_√
፫-፬:- ከክፉ ሥራ ራቁ። ይኽውም መዝፈን፣ ጣዖት ማምለክ፣ ጥንቁልና ነው።
፮:- ምእመናን ከክፉዎች ማኅበር ሊለዩ አገባብ ነው።
፲፩:- ተግባረ እድን አናቋርጥ። ቸልም አንበል።
፳:- ጥበበኛ ሰው ለራሱ አላዋቂ መስሎ ይታያል።
፳፪:- ሥራ የማይሠራ ሁሉ ምግብን አይመገብ።
_አንቀጽ ፲፫_√
፲፫:- ሕፃናት ሴቶች በቤተክርስቲያን ውስጥ አይሾሙ። የፈቲውን ፆር መታገሥ አይቻላቸውምና። በወጣትነት ኃይል ዳግመኛ ወንድን ያገባሉና።
፳:- ለቆነጃጅቶች ሴቶችም የቀድሞ ባሎቻቸው ከሞቱባቸው መታገድ ባይቻላቸው ሁለተኛ ባል ያገቡ ዘንድ እንዲገባ እናዛለን።
፴:- ለሰው ሁሉ በጎ ነገርን ታደርጉ ዘንድ ይገባል።
፵፪:- ባልቴቶች ትዕግሥተኞች ነገርን የማያበዙ ክፋትና ቁጣ የሌለባቸው ይሆኑ ዘንድ አገባብ ነው።
፵፯:- ሥርዓትን ይማሩ ዘንድ የሚሹ ወደ መምህራን ሄደው ይማሩ። የምክር ቃልንም ይስሙ።
_አንቀጽ ፲፬_√
፩:- ሴቶች ያጠምቁ ዘንድ አይገባም።
፬:- ሴቶችን ያስተምሩ ይገሥጹ ዘንድ አታሰናብቷቸው። የክህነት ሥራንም አይሥሩ።
፲:- (ሴቶች) ፈጽመው ብልሆችም ቢሆኑ፣ ሃይማኖትም ቢኖራቸው፣ መጻሕፍትንም ቢያውቁ፣ ያጠምቁና ወንጌልን ያስተምሩ ዘንድ አናሰናብታቸውም።
_አንቀጽ ፲፭_√
፩:- ሕዝባዊ የክህነት ሥራን እንዳይሠራ፣ ዕጣንንም እንዳያሳርግ፣ እንዳያጠምቅ፣ በአንብሮተ እድም እንዳይባረክ፣ በረከተ ኅብስቱንም እንዳይሰጥ እናዝዛችኋለን።
፮:- ኤጲስ ቆጶሳትና ቀሳውስት ብቻ ያጥምቁ።
፰:- ቀሳውስት ዲያቆናትንና ዲያቆናዊትን፣ አናጉንስጢስንም፣ መዘምራንንም፣ በር ዘጊዎችንም እንዳይሾሙ እነሄ እናዝዛለን።
_አንቀጽ ፲፮_√
፲፩:- መበለት ለሰጧትና ለመጸወቷት ሰዎች ትጸልይ።
፲፬:- ሀብት ከሰው ዘንድ የሚሰጥ አይምሰላችሁ። የጸጋ ሀብት ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።
፲፱:- የዐመፅ ርግማን ባልበደለ ሰው ላይ አይደርስም። ወደ ረጋሚው ይመለሳል እንጂ።
፳፮:- ኤጲስ ቆጶስም ቢሆን ወይም ቄስ ወይም ዲያቆን ቢሆን ከሹማምንት ወገንም የሆነ ቢሆን ስለበረከት ፈንታ እርግማንን እንዳይወርስ እርግማን ከአፉ አይውጣ።
፴:- ዲያቆናዊት ነውር የሌለባት ሴቶችን ለማገልገል የተመረጠች ንጽሕት ትሁን።
፴፯:- ከበለሳን የተገኘ ቅብዐ ሜሮን የሃይማኖት ኃይል ነው።
፵፯:- (ዲያቆናት) ለተቸገሩት ሰዎች ማገልገልን እንቢ አይበሉ።
፶፯:- እነሆ ኤጲስ ቆጶስ በሦስት ኤጲስ ቆጶሳት ያም ባይሆን በሁለት ኤጲስ ቆጶሳት ይሾም ዘንድ እናዝዛለን።
፶፱:- ቀሳውስት፣ ዲያቆናትና ሌሎች የቤተክርስቲያን ሹማምንት ግን በአንድ ኤጲስ ቆጶስ ይሾሙ።
_አንቀጽ ፲፯_√
፩:- እናት አባት የሞቱባቸውን ልጆች ያሳድጓቸው ዘንድ ይገባል።
_አንቀጽ ፲፰_√
፫:- (ኤጲስ ቆጶሳት ሆይ) ለሚያገለግሉ ደመወዛቸውን ስጡ። የተራቡትን አብሏቸው። ድሆችን አሳድሯቸው። የታረዙትን አልብሷቸው። የታመሙትን ጠይቋቸው። የታሠሩትንም እርዷቸው።
፲:- እያለው ምጽዋትን የሚቀበል እርሱን እግዚአብሔር ይቆጣጠረዋል። የድሃውን ምግብ ነጥቋልና።
_አንቀጽ ፲፱_√
፮:- ባልቴቶችንና ድሀ አደጉን ለሚቀበሉ እግዚአብሔር በመንግሥተ ሰማያት ደስ ያሰኛቸዋል።
_አንቀጽ ፳_√
፩:- ከመሸተኛ መባን እንዳትቀበሉ ተጠንቀቁ።
፫:- ፈጣሪ እግዚአብሔር ከዝሙት ዋጋ መባ አትቀበሉ ብሏልና።
፮:- ክፉ የሚሠራና ዐመፅን የሚናገር ሁሉ በእግዚአብሔር ዘንድ የተናቀ ነው።
፲፪:- ከብዙ የኃጢአተኞች ሀብት ጥቂት የጻድቃን ሀብት ይበልጣል።
፳፮:- እግዚአብሔርን ከሚጠሉ ሰዎች መባን ተቀብላችሁ መሳቂያና መዘበቻ ከምትሆኑ ታግሣችሁ በመራብ በመጠማት ትኖሩ ዘንድ አገባብ ነው።
፳፯:- ከወንጀለኞች መባን አትቀበሉ።
_አንቀጽ ፳፩_√
፩:- አባቶች የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ይጠብቁ ዘንድ ልጆቻችሁን አስተምሯቸው። የእጅ ሥራንም ይማሩ ዘንድ እዘዟቸው።
፭:- ልጁን የማይገሥጽ አባት አላዋቂ ነው።
፰:- (ልጆች) ወደ መሸታ ቤት ይገቡ ዘንድ አታሰናብቷቸው።
_አንቀጽ ፳፪_√
፪:- አገልጋይ ክርስቲያን ቢሆን ጌታው ከሓዲ ቢሆን በሥራው ሁሉ ይገዛለት ዘንድ አገባብ ነው። ነገር ግን ከእርሱ ጋራ በሃይማኖት አይተባበር።
√አንቀጽ ፳፫
፩:- ደናግል ሰውነታቸውን ሳይፈትኑ ይሣሉ ዘንድ አይገባም።
√አንቀጽ ፳፬
፪-፫:- በመከራ ላሉ ሰማዕታት ከገንዘባችሁ ምግባቸውን ላኩላቸው። ዳግመኛም ለሚጠብቋቸው ጭፍሮች ምግባቸውን ስጡ። በእነርሱ ላይ መከራ እንዳያጸኑባቸው።
፭:- ሰማዕት የጌታ ወንድም ይባላል።
፰:- ገንዘብ የሌላችሁ ደግሞ መከራ እየተቀበሉ ስላሉ ሰማዕታት ጹሙ።
፸፬:- ንኡሰ ክርስቲያን ቢታመም መከራንም ቢታገሥ ስለ ክርስቶስ ስም ቢሞት መከራው ስለ ጥምቀት ይሆነዋል።
++++
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
ክፍል ፭ ይቀጥላል
መ/ር በትረማርያም አበባው
1.2K views13:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 15:56:42 __ዲድስቅልያ ክፍል ፫__
_አንቀጽ ፯_√
፩:- ያልበደለውን የሚያሳድድ ሰው ከነፍሰ ገዳይ ይከፋል።
፶:- ኤጲስ ቆጶስ ለቤተክርስቲያን ከሚገባው አሥራትና ከእህሉ ቀዳምያት ይመገብ።
፶፩:- ኤጲስ ቆጶሱም ለድኃዎች፣ የዕለት ራት ለሌላቸው ጦም አዳሪዎች፣ ለባልቴቶች፣ እናትና አባት ለሞቱባቸው ልጆች፣ ለስደተኞች፣ ምንም ለሌላቸው መፍቅዳቸው ይሰጥ ዘንድ ይገባዋል። ኤጲስ ቆጶሱ ግዳጃቸውን ባይሰጣቸው ግን ስለእነርሱ እግዚአብሔር ይመራመረዋል።
፷፰:- ያልነጹትን እንስሳት በኩራትና የሰውን በኩራት መቤዠት ነው።
_አንቀጽ ፰_√
፱:- ዲያቆናዊት ሴት ያለዲያቆኑ ፈቃድ ምንም ምን አትሥራ። ማንኛዋም ሴት ከዲያቆናዊት ጋር ካልሆነች በቀር ወደ ዲያቆኑ አትሂድ። እንደዚሁም ሴት ከዲያቆኑ ጋር ካልሆነች በቀር ወደኤጲስ ቆጶሱ አትግባ።
፲:- እንግዲህ ካህናትን አክብሯቸው ይመክሯችኋልና። የእግዚአብሔርንም መንገድ ያስተምሯችኋልና።
፲፩:- ኤጲስ ቆጶሱ ለተቸገሩት ሁሉ ያዝን ዘንድ ሕይወታቸውንም ይመረምር ዘንድ ኑሯቸውንም ይረዳ ዘንድ ይገባዋል።
፲፱:- ዲያቆናት የሕዝቡን ችግር ሁሉ ለኤጲስ ቆጶሳት ይነግሯቸው ዘንድ ይገባል።
፳፪:- ኤጲስ ቆጶሳት የእግዚአብሔር አፍ እንደሆኑ እናስብ።
_አንቀጽ ፱_√
፩:- ዲያቆን ለኤጲስ ቆጳሱ መልእክተኛ ነው።
፯:- ከእግዚአብሔር በታች አባት ለሆነህ ለኤጲስ ቆጶሱ እጅ ንሣ።
፲፪:- ክህነት ከመንግሥት ትበልጣለች።
_አንቀጽ ፲_√
፲፰:- ኤጲስ ቆጶስ ሆይ ኃጥአንን እርዳቸው በእግዚአብሔር ቃልም አጽናቸው። አትናቃቸው ከእነርሱም ጋር መብላትን እንቢ አትበል። ጌታችን ከኀጢአተኞችና ከቀራጮች ጋር መብላትን እንቢ አላለምና።
፵፪:- ኤጲስ ቆጶስ ሆይ ንኡሰ ክርስቲያንን በምታጠምቅበት ጊዜ እንዲህ አድርግ። ተቀብለህ በላያቸው ላይ እጅህን ጫንባቸው። በንስሓ ነጽተዋልና።
፶:- ኤጲስ ቆጶስ ሆይ አንተም እንደ ብልህ ባለመድኃኒት ኃጥአንን አድናቸው። ከኃጢአት ቁስልም ፈጽመህ አድናቸው።
፸፩:- ከቤተክርስቲያን ሹሞች በቀር ሕዝባዊ አይፍረድ። ሽማግሌዎችም አይፍረዱ።
፸፪:- ምሥጢራችሁን ያውቁ ዘንድ ለአሕዛብ አትፍቀዱላቸው።
፹፭:- ሐሰትን ከመናገር ተጠበቁ። ሐሰትን የሚናገር ሰው በብዙ ይፈረድበታልና።
፹፯:- የዋሆች፣ የማይቆጡ፣ ንጹሓን፣ ቸሮች፣ ትሕትናን የሚወዱ፣ የታመኑ፣ እግዚአብሔርን የሚያመልኩ ሰዎች ምስክር ይሆኑ ዘንድ አግባብ ነው። የንጹሓን ሰዎች ምስክርነት ይገባልና።
፹፱:- ለፍርድ ወደ እናንተ የመጣ ሰው ቢኖር ግብሩና ልማዱ እንዴት እንደሆነ ሕይወቱን መርምሩ።
፺፪:- የከሰሰ ሰው ቢኖር ሁለቱም በአንድነት በአደባባይ ሳይኖሩ ለአንዱ አትፍረዱ። (ከሳሹም ተከሳሹም መኖር አለባቸው)
_አንቀጽ ፲፩_√
፫:- የወንድምህን በደል አራት መቶ ዘጠና ጊዜ ይቅር ብትል ግን ራስህን ታድን ዘንድ ቸርነትህ የበዛ ቁጣህም ያነሰ ሆንክ። እንዲህም ብታደርግ የሰማያዊ አባትህ ልጅ ትሆናለህ።
፬:- ኤጲስ ቆጶሳት ሆይ ቅዱሳት መጻሕፍትን አንብቡ።
፰:- ኤጲስ ቆጶሳት ሰላምን የሚያደርጉ፣ እነርሱንም የበደሏቸውን ይቅር የሚሉ፣ ርኅሩኃን ወይ እግዚአብሔር የሚመለሱትንም ንስሓቸውን የሚቀበሉ ይሆኑ ዘንድ አግባብ ነው።
፳፪:- በንስሓ ፈጽማ የዳነችውን ነፍስ በቁጣና በብስጭት አትግደሉ።
፴:- እንግዲህ ቤተክርስቲያን እንዲህ ትሁን። ርዝመቷ በምሥራቅ በኩል ይሁን። በጎንና በጎንም በመርከብ አምሳል ሁለት ክፍሎች ይኑሩ። የኤጲስ ቆጶሱ መንበርም በመካከል የተዘጋጀ ይሁን።
፴፯:- ወንጌልም በሚነበብበት ጊዜ ቀሳውስት ዲያቆናት ሕዝቡም ሁሉ በታላቅ ፍርሀት ይቁሙ።
፵፩-፵፪:- የሚበቃቸው ቦታ ባይኖር ወንዶች ልጆች በአባቶቻቸው ፊት ይቀመጡ። ሴቶች ልጆችም ብቻቸውን ይቀመጡ። ቦታ ባይኖር ግን ባገቡት ሴቶች ኋላ ይቁሙ። ደናግልና መበለቶች ባልቴቶችም በሴቶች ፊት ይቁሙ። ባልና ልጅ ያላቸው ሴቶች ግን ብቻቸውን ይቀመጡ።
፵፬:- (በቤተክርስቲያን ውስጥ) በሳቅና በዋዛ የሚገኙ ሰዎች ቢኖሩ ዲያቆኑ ይምከራቸው። ዝም እንዲሉም ያድርጋቸው።
፵፮:- ንዑሰ ክርስቲያን ይውጡ ብሎ ዲያቆኑ አሰምቶ በሚናገርበት ጊዜ መምህራንና በንስሐ ያሉ ሰዎች ሕዝቡም ሁሉ ቆመው ወደ ምሥራቅ ይመልከቱ።
፶፮:- ሴቶች ራሳቸውን ተሸፍነው ይቁሙ። ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙንም ይቀበሉ።
፷፰:- በነግህና በሠርክ በቤተክርስቲያን ተሰብስባችሁ መዝ. 62ን እና መዝ. 140ን ዘምሩ
፸:- በክርስቲያን ሰንበት ዕለት የክርስቶስን የትንሣኤውን ስብከት እንሰማ ዘንድ፣ መከራዎቹንም እናስብ ዘንድ፣ መታሰቢያውንም እናደርግ ዘንድ፣ የነቢያትን መጻሕፍትና ቅዱስ ወንጌልንም እናነብ ዘንድ፣ መንፈሳዊ ምግብ የሚሆን መሥዋዕትንና ቁርባንን እናቀርብ ዘንድ ይገባናል።
++++
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
ክፍል ፬ ይቀጥላል
መ/ር በትረማርያም አበባው
1.2K views12:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ