Get Mystery Box with random crypto!

በትረማርያም አበባው

የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው
የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው
የሰርጥ አድራሻ: @betremariyamabebaw
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.25K
የሰርጥ መግለጫ

አቀድም አእኵቶቶ ለእግዚአብሔር

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 76

2022-08-29 18:36:38 #ስምዐ #ጽድቅ
ስለዚህም ተክለሃይማኖት ሆይ የእውነት ምስክር ሆንክ። "ወበእንተዝ ተሰመይከ ተሰመይከ ተክለ ሃይማኖት። ስምዐ ጽድቅ ኮንከ ስምዐ ጽድቅ ኮንከ ተክለሃይማኖት"። ዋሽቶ ከመኖር እውነትን ተናግሮ መሞት ይበልጣል። ዋሽቶ ከመከበር እውነትን ተናግሮ መጠላትና መሰደብ ይሻላል።

ታላቁ ቅዱስ አባት አቡነ ተክለሃይማኖት ዘመኑን ሁሉ ቅዱስ እግዚአብሔር የገለጠውን እውነት በአንደበቱ በመስበክ በሕይወቱ በመተግበር ኖሯል። በእርግጥ የመኖር ፍሬ ነገርም ለእውነት እስከ ሞት ድረስ ታምኖ መኖር ነው። ቅዱስ አባታችን በዛሬው እለት ነሐሴ ፳፬ ቀን ከዚህ ዓለም ድካም አርፎ ወደ ዘለዓለማዊው ሕይወት የተሸጋገረባት ቀን ናት። ሞቶሙሰ ለጻድቃን ሕይወቶሙ ውእቱ። የጻድቃን ሞታቸው ሕይወታቸው ነው። ቅዱሳን እውነትን በመያዛቸው በሐሰተኞች ቢሳደዱም መከራ ቢደርስባቸውም ሁልጊዜም ደስተኞች ነበሩ። የደስታቸው ምንጭ እግዚአብሔር ነውና። ለዚያምኮ ነው ቅዱስ ዳዊት ንዑ ንትፈሣሕ በእግዚአብሔር ኑ በእግዚአብሔር ደስ ይበለን ያለው።

እንኳን አደረሳችሁ።
2.1K views15:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 17:31:27
ቅኔ ጥበብ ነው።
ቅኔ መንፈሳዊ ፍልስፍና ነው።
በቅኔ ተግሣጽ አለ።
በቅኔ ምዕዳን አለ።
2.2K viewsedited  14:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 17:16:48
ጥዑም ዜማ @ደብረ ኃይል ወደብረ ጥበብ በዓታ ለማርያም።

ይመጽእ ላእሌኪ መንፈስቅዱስ ኃይለ ልኡል ይጼልለኪ። አንጺሖ ሥጋሃ ኀደረ ላእሌሃ ላእሌሃ መንፈስ ቅዱስ።
2.2K viewsedited  14:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 13:45:11
1.7K views10:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 13:44:27 #ሳልናገረው #እንዳልቀር
ሕይወት ብዙ ታስተምራለች። መልካችን አካላችን ልዩ ልዩ እንደሆነ ሁሉ አስተሳሰባችንም ልዩ ልዩ ነው። የአስተሳሰብ እና የፍላጎት ልዩነቶች ወደ መሰዳደብ ወደ መገዳደል ወደ መጠላላት ያመሩናል። እኔ በግሌ ብዙ ጊዜ ተሳስቼ ነበር። ስህተትን አምኖ ወዲያው ይቅርታ ለመጠየቅ ትልቅነት ይጠይቃል። ነገር ግን ትንሽነቴ ከልክሎኝ ዝም ያልኩበት ወቅት አለ። ብዙ ጊዜም ልክ ነበርኩ። ትክክልነቴ እንዲጎለብት "በርታ፣ ቃለ ሕይወት ያሰማልን፣ መልካም" እያሉ ያበረታቱኝ አሉ ነበሩ። ስህተቴን እንዳስተካክል ጥርግርግ አድርገው የሰደቡኝም አሉ ነበሩ። እውነቱን ለመናገር ራሴን በብዙ ረገድ እንዳስተካክል የረዱኝ እነዚህ ናቸው። ሁሉንም ልዑል እግዚአብሔር በቸርነቱ መንግሥቱን ያውርስልኝ። የተቃርኖ መኖር ለሐሳብ ጥራት ትልቅ አስተዋጽኦ አለው። ብዙ ጊዜ መሰደብ ለጊዜው ይመር ይሆናል። መራራውን ታግሦ መቆየት ግን ትልቅ መንፈሳዊ ፈውስ ይሰጣል።
√√√√
ሳልናገረው ማለፍ የማልፈልገው ከሁሉም ከሁሉም ለሰደቡኝ ሰዎች ትልቅ አክብሮት እንዳለኝ ነው። ብዙ ጊዜ ብሎክ የማላደርግም ለዚያ ነው። ስሰደብ የተሳሳትኩት ምኑ ላይ ነው? የሚለውን እንዳይ ረድቶኛል። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ሰው ዝም ብሎ ይሳደባል። ለምሳሌ ምርጥ ሐሳብ አንስተህ ግን ይሰድብሀል። ይህ በብዙ ምክንያት ይሆናል። አንደኛው ማንኛውም ሰው አኗኗሩ ባወቀው ልክ ነው።ቀድሞ የተሳሳተ ነገር አውቆ ከነበረ እውነትን ስትነግረው ቀድሞ በያዘው በተሳሳተው እውቀት መዝኖ ደንበኛውን እውቀት ይጠላል። ይሳደባል። የዚህ ዓይነት ተሳዳቢ ትልቁ ጥቅም የራስህን እውቀትና ሐሳብ እውነትነት ዞር ብለህ እንድትገመግም እና በጥራት ለመያዝ ይረዳል።
√√√√
ሰው እስከ ዕለተ ሞቱ ድረስ ተማሪ ነው። ተማሪ ደግሞ ስህተቱን እያረመ እውቀቱን እያጎለበተ የሚሄድ ነው። ማንኛውም ሰው የሚሳሳት መሆኑን መረዳት ይገባል። የብዙ ሰው ስህተት ምንጩ አለማወቁ ሊሆን ይችላል። ላለመሳሳት ዋናው ነገር አለማወቃችንን አውቀን የማናውቀውን ጉዳይ በግምትና በመሰለኝ ከመናገር ይልቅ ከሚያውቁት በትሕትና መጠየቅ ነው። ነገር ግን ሁሉን የሚያውቅ እግዚአብሔር ብቻ ስለሆነ አለማወቅ በራሱ ኃጢኣት አይደለም። በጠቅላላው ገንቢ ሐሳብ የሰጣችሁኝ ያበረታታችሁኝ ይልቁንም ራሴን እንዳይ የሰደባችሁኝ እግዚአብሔር መልካሙን ሁሉ ያድርግላችሁ።
+++
በዚሁ ሚድያ ባጠፋሁት ጥፋት፣ በአነጋገሬ በጽሑፌ ያስቀየምኳችሁ ካላችሁም ይቅርታ እጠይቃለሁ። አምላከ ቅዱሳን እግዚአብሔር ባለፈው ይቅር ይበለን፣ ለወደፊቱም ይጠብቀን። ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን።
1.8K views10:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 09:04:58 "ወይቤሉ ሰላም ሰላም ወአልቦ ሰላም"።
ሰላም ነው ሰላም ነው ይላሉ ሰላም ግን የለም። ፍቅር ነው ፍቅር ይደረጋል ይላሉ ፍቅር ግን የለም"
ነቢዩ ቅዱስ ኤርምያስ
4.1K views06:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 12:03:06
"ሥራህን ሥራ"
ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ
4.9K views09:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 10:32:11 _#ግእዝ #ክፍል ፷፩_
ሙሻዘር ከክፍል 60 የቀጠለ
#ዘመድ #ዝርዝር
ዘመድ ዝርዝር የሚባለው በየራሱ የሚዘረዘረው ነው። ለምሳሌ አምላክ ሞቶ ለአዳም ሲል በይኔሁ/ሎቱ ይወጣሉ ትርጉሙ ስለእርሱ/ለእርሱ ለአዳም ስለ አዳም አምላክ ሞተ ማለት ነው።
-
ቦቱ ሲወጣ:-አምላክ ተሰቅሎ ለመስቀል ይላል ትርጉሙ በእርሱ በመስቀል አምላክ ተሰቀለ ማለት ነው።
-
እምኔሁ ሲወጣ:-ነጋዲ ወጽኦ ለቤት ከእርሱ ከቤቱ ነጋዲ ወጣ ይላል።
-
ምስሌሆሙ፣ከማሆሙ ሲወጡ:- አምላክ ተሰቅሎሙ ለፈያት ይላል ትርጉሙ እንደነርሱ ከእነርሱ ጋራ አምላክ ተሰቀለ ማለት ነው።
-
ኀቤሃ፣እስከኔሃ ሲወጡ:- ገብርኤል ተፈነዋ ለማርያም ይላል ትርጉሙ እስከ እርሷ ወደእርሷ ወደማርያም እስከ ማርያም ገብርኤል ተላከ ማለት ነው።


#ባዕድ #ቅጽል
አገባቡ ዝርዝሩ ለባለቤት አንቀጹ ለተሳቢ ሲሆን ባዕድ ቅጽል ይባላል። አንድና ብዙ፣ ሴትና ወንድ፣ ሩቅና ቅርብ ሳያናግር ያናገረ ይመስላል። አንቀጽን፣ ተሳቢን እና አገባብን ይዘረዝራል።
-
አንቀጽ ሲዘረዝር:-ማርያም እንተ አክበሩ ሥላሴ አበው ይላል ትርጉሙ ሥላሴ አባቶች ያከበሯት ማርያም ማለት ነው። ብእሲ ዘአክበረት ብእሲት ይላል ትርጉሙ ሴት ያከበረችው ሰው ማለት ነው። መላእክት እለፈጠርከ አንተ ወልድ ይላል ትርጉሙ አንተ ወልድ የፈጠርካቸው መላእክት ማለት ነው።
-
የተሳቢ ዝርዝር:- ማርያም ዘአክበሩ አበዊሃ ይላል ትርጉሙ አባቶቿ ያከበሯት ማርያም ማለት ነው። መላእክት እለ ፈጠርከ አንተ እግዚኦሙ ይላል ትርጉሙ አንተ ጌታቸው የፈጠርካቸው መላእክት ማለት ነው።
-
የአገባብ ዝርዝር:- አበው እለ ከብረት ማርያም ይላል።ትርጉሙ ማርያም የከበረችላቸው አባቶች ማለት ነው። መላእክት እንተ ተፈጥሩ ወልድ ይላል ትርጉሙ መላእክት የተፈጠሩለት ወልድ ማለት ነው። ብእሲ ዘተፈጥረት ብእሲት ይላል። ሴት የተፈጠረችለት ሰው (ወንድ) ማለት ነው።

እነዚህ በግልጸ ዘ ሲነገሩ ነው። ብቻ በሳድስ ቅጽል ሲነገሩ ደግሞ የሚከተለውን ይመስላሉ።
-
አንቀጽ ሲዘረዝር:-ማርያም ወይን ትክልተ ሥላሴ ገባእት ፈረየት ፍሬ ይላል ትርጉሙ ሥላሴ ምንደኞች የተከሏት/የተከላችኋት/የተከልናት ማርያም ወይን አፈራች ይላል።ወይም ሥላሴ ምንደኞች የተከሉሽ ማርያም ወይን አፈራሽ ይላል።ወይም ሥላሴ ምንደኞች የተከልንሽ ማርያም ወይን አፈራሽ ይላል። ሥላሴ ምንደኞች የተከሉኝ/የተከላችሁኝ ማርያም ወይን ፍሬን አፈራሁ ይላል።
-
አገባብ ሲዘረዝር:-ድንግል ንግሥት ወልድ ይላል።ትርጉሙ ወልድ የነገሠላት ድንግል/ ወልድ የነገሥኩላት ድንግል/ ወልድ የነገሠልሽ ድንግል/ ወልድ የነገሠልኝ ድንግል/ ወልድ የነገሥክልኝ ድንግል/ ወልድ የነገሥኩልሽ ድንግል/ ወልድ የነገሥክላት ድንግል ይላል።
-
ተሳቢ ሲዘረዝር:-ጴጥሮስ ምሁረ አርድእት ወንጌለ ይላል ትርጉሙ ተማሪዎቹ ወንጌልን የተማሩ ጴጥሮስ ይላል።
-
የተደራጊ አንቀጽ ከአድራጊ ከአስደራጊ ተናቦ በአድራጊ በአስደራጊ አመል ይፈታል። ለምሳሌ አምላክ ተሰቃሌ ይሁዳ ሲል ትርጉሙ ይሁዳ የሰቀለው አምላክ ይሆናል። አምላክ ተሰቃሌ ይሁዳ አይሁደ ሲል ይሁዳ አይሁድን ያሰቀለው አምላክ ተብሎ ይተረጎማል።
-
የአድራጊ አንቀጽ ከአስደራጊ ተናቦ በአስደራጊ አመል ይፈታል። አምላክ ሰቃሌ ይሁዳ አይሁደ ይላል ትርጉሙ ይሁዳ አይሁድን ያሰቀለው አምላክ ማለት ነው።
-
የተደራራጊ አንቀጽ ከአደራራጊ ተናቦ በአደራራጊ አመል ይፈታል ምሳሌ አምላክ ተሰቃሌ ይሁዳ ምስለ አይሁድ ይላል።ትርጉሙ ይሁዳ ከአይሁድ ጋር ያሰቃቀለው አምላክ ማለት ነው።

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን።
4.5K views07:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 09:59:19 ግእዝ ክፍል ፷
#ሙሻ #ዘር #የቀጠለ
ሙሻዘር ከሚሆኑ ቀለማት አምስቱ ማለትም ቀዳማይ አንቀጽ፣ ካልዓይ አንቀጽ፣ ሣልሳይ አንቀጽ፣ ዘንድ አንቀጽ እና ቦዝ አንቀጽ ዘርዝረው ሳይናበቡ አገባባትን ያመጣሉ። ሲመጡም አንድና ብዙ ሴትና ወንድ ሩቅና ቅርብ አይለዩም። ቀጥለን በምሳሌ እንመልከተው።


#ቀዳማይ #አንቀጽ
በይኔሁ፣ሎቱ ሲወጡ:- አምላክ ፈጠሮ ኪያኪ ሔዋንሀ ይላል ትርጉሙ ለእርሱ/ስለእርሱ አንቺን ሔዋንን አምላክ ፈጠረ ማለት ነው። አስተውል ፈጠሮ ያለው ዝርዝር ፈጠረው ተብሎ ከመተርጎም ይልቅ ፈጠረ ተብሎ ተተርጉሟል። ባዕድ ያሰኘውም ይህ ነው።
-
ቦቱ፣ላዕሌሁ ሲወጡ:-ንጉሥ አንበሮ ኪያየ አክሊለ ይላል ትርጉሙ በእርሱ/በእርሱ ላይ እኔን አክሊል ንጉሥ አስቀመጠ ማለት ነው።
-
እምኔሁ ሲወጣ:-አብ አፍቀሮ ንዑሳነ ሕጻናተ ይላል ትርጉሙ ከእርሱ ትንንሽ ሕጻናትን አብ ወደደ ይላል።
-
ከማሁ ሲወጣ:-ንጉሥ አክበሮ ሠናያተ አንስተ ይላል ትርጉሙ እንደ እርሱ የሚያምሩ ሴቶችን ንጉሥ አከበረ ማለት ነው።
-
ምስሌሁ ሲወጣ:-ንጉሥ አቅረቦ ምሁረ ኪያክን አንስተ ጊዜ ማዕድ ይላል ትርጉሙ ከእርሱ ጋራ በማዕድ ጊዜ እናንተን ሴቶችን ምሁሩን (የተማረውን) ንጉሥ አቀረበ ይላል።
-
ኀቤሃ፣ እስከኔሃ ሲወጡ:- ንግሥት አብጽሐታ ዘተለወት አመተ ይላል ትርጉሙ እስከ እርሷ/ወደ እርሷ የተከተለች የሴት አገልጋይን ንግሥት አደረሰች ይላል።


#ካልዓይ #አንቀጽ:-
ከላይ ያየነውን ቀዳማይ አንቀጽ መስሎ የሚሄድ ሲሆን ልዩነቱ በቀዳማይ ይተረጎም የነበረውን በካልዓይ እየተረጎሙ መሄድ ነው። ለምሳሌ ከላይ ከማሁ ሲወጣ በቀዳማይ ንጉሥ አክበሮ ሠናያተ አንስተ ያለውን ንጉሥ ያከብሮ ሠናያተ አንስተ ብሎ ማውጣት ማለት ነው። ትርጉሙ እንደ እርሱ የሚያምሩ ሴቶችን ንጉሥ ያከብራል ተብሎ ይተረጎማል። ሌሎችንም አገባባት በዚህ መልኩ እያደረጉ ማውጣት ነው።


#ሣልሳይ #አንቀጽ (ትእዛዝ አንቀጽ)
ይህም አካሄዱ በቀዳማይ አንቀጽ ካየነው ጋር ይመሳሰላል። ለምሳሌ በይኔሁ/ሎቱ ሲወጡ ንጉሥ ይሞቅሖሙ ኪያሁ ፈያተ ቢል ትርጉሙ ስለእርሱ/ለእርሱ እርሱን ሽፍታውን ንጉሥ ይሰር ይላል። ሌላውንም በዚህ መልኩ ማውጣት ነው።


#ዘንድ #አንቀጽ
ዘንድ አንቀጽም በቀዳማይ አንቀጽ ካየነው ጋር ይመሳሰላል። ልዩነቱ ዘንድ መሆኑ ብቻ ነው። ለምሳሌ ለእግዚአብሔር ይምሐሮሙ ኀጥአነ ቢል በአገባብ በይኔሁ/ሎቱ ሲወጣ ለእርሱ/ስለእርሱ ኀጥአንን ይምር ዘንድ ለእግዚአብሔር ይገባል ማለት ነው።


#ቦዝ #አንቀጽ
ይህም ልዩነቱ ቦዝ መሆኑ እንጂ ከላይ ካየናቸው ጋር ተመሳሳይ ነው። ለምሳሌ ነቢያት አእሚሮሃ ምጽአተ ክርስቶስ ተነበዩ ቢል ትርጉሙ በይኔሁን/ሎቱን ሲያወጣ ለእርሱ/ስለእርሱ የክርስቶስን መምጣት ነቢያት አውቀው ተናገሩ ይላል።
3.2K views06:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 20:45:12
3.2K views17:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ