Get Mystery Box with random crypto!

በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw

የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw
የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw
የሰርጥ አድራሻ: @betremariyamabebaw
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 20.24K
የሰርጥ መግለጫ

አቀድም አእኵቶቶ ለእግዚአብሔር

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 69

2022-10-04 19:29:15 Watch "ሰአሊ ለነ ቅድስት|አዲስ ስብከት|New Ethiopian Orthodox Tewahdo Preaching 2021|Endalikachewu Neway|መ/ር እንዳልክ ንዋይ" on YouTube


1.2K views16:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-04 19:21:23 __የመልካም ሰው ጸባይ_
፩) ማንንም የሚያስቀይም ንግግር አይናገርም።
፪) ሁልጊዜም ለእኛ ለሕይወታችን መርሕ የሆነውን የእግዚአብሔርን ሕግ ይጠብቃል።
፫) የሰውን ድካም ስለሚያውቅ በማንም ቂም አይዝም። በማንም አያዝንም። ይልቅስ ያንን ይቅር ብሎ ለወደፊቱ መልካም ግንኙነት ያስባል።
፬) ጥፋቱን በንሥሓ እና በይቅርታ ያርማል።
፭) ኃጢዓትን እንጂ ኃጢዓተኛን አይጠላም።
፮) ሰውን በሰውነቱ ያከብራል ይወዳል እንጂ በቀለሙ፣ በጾታው፣ በእድሜው፣ በተወለደበት ሰፈር፣ በዝምድና እና በመሳሰሉት እያለ አይለያይም።
፯) እውነትን ይወዳል።
፰) በእግዚአብሔር እንጂ በሌላ አይመካም።
፱) ንሥሓ እየገባ የክርስቶስን ሥጋውን ደሙን ይቀበላል።
፲) ይጸልያል፣ ይጾማል፣ በሁሉ ነገር ፈጣሪውን ያመሰግናል፣ ሌላውን ሰው እንደራሱ ይወዳል፣ ይመጸውታል።
፲፩) ሥጋዊ ክብርን ከንቱ ውዳሴን እና ተርእዮን ይጠላል።
፲፪) ራሱን የሚመዝነው በእግዚአብሔር ሕግ ነው።
፲፫) ትሑት ነው፣ ታጋሽ ነው፣ ራሱን የገዛ ነው።
፲፬) እግዚአብሔርን ይፈራል።
፲፭) ለሁሉም ሰው መልካም ያስባል፣ መልካም ያደርጋል።

እስኪ በእናንተ እይታስ መልካም ሰው የምትሉት እንዴት ዓይነቱን ነው? ጨምሩበት። እና እንማማር።
። እግዚአብሔር መልካም ሰው እንድንሆን ይርዳን።
1.3K views16:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 15:09:01 ስለ ጸሎት፣ ጾም፣ ተስፋ፣ ስግደት እና የመሳሰሉት የተማማርናቸው በፒዲኤፍ እነሆ ይህን ይመስላሉ። ፒዲኤፉን ያዘጋጀልኝ ዲ/ን ዶ/ር ይታገሱ ነው። እግዚአብሔር ያክብርልኝ። በዚህ ስንማማር ግልጽ ያልሆነ ነገር ካለ በፌስቡክ ገጼ መጠየቅ ይቻላል።
1.2K views12:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 15:06:15 #ተስፋ Hope
ሰው የሚቻለውን ሁሉ እያደረገ እግዚአብሔርን ተስፋ ማድረግ አለበት። ተስፋ መቁረጥ ሰይጣናዊ ሥራ ነው። ሰው ፈጣሪው እስካለው ድረስ በምንም ቢሆን ተስፋ መቁረጥ አይገባውም። ተስፋ በፈጣሪ ላይ ያለን የመታመን ኃይል ነው። ሰው በሰው ተስፋ ማድረግ አይገባውም። ሰው በገንዘቡ፣ በኃይሉ፣ በውበቱ፣ በእውቀቱ እና በመሳሰሉት ተስፋ ማድረግ አይገባውም። እኒህን ሁሉ በሚሰጥ በእግዚአብሔር ተስፋ ማድረግ ይገባል። ለዚያ ነው ማኅሌታዊው ዳዊት "ይኄይስ ተሰፍዎ በእግዚአብሔር እምተሰፍዎ በእጓለ እመሕያው ያለውን በሰው ተስፋ ከማድረግ በእግዚአብሔር ተስፋ ማድረግ ይበልጣል ይላል። ከእግዚአብሔር በላይ የሆነ ምንም ዓይነት ችግር ስለሌለ በማናቸውም ጭንቀትና መከራ ውስጥ ብንሆንኳ እግዚአብሔርን ተስፋ እናድርግ። ተስፋ መቁረጥ እግዚአብሔርን ተስፋ ካለማድረግ የሚመነጭ ክፉ ሐሳብ ነው። እስከ ዕለተ ሞታችን ድረስ በተስፋ ልንኖር ይገባል። ተስፋ ኃይል ነው። ተስፋ ያለው ሰው አይፈራም። ስለዚህ ተስፋን ገንዘብ እናድርግ።

#ንሥሓ
በራሳችን ተስፋ መቁረጥ የለብንም። ሥጋዊ ፈቃድ አሸንፎን ብዙ ጊዜ እግዚአብሔርን በድለነው ይሆናል ነገር ግን ንሥሓ ከመግባት ማቋረጥ የለብንም። ጥሩ ሰዎች እስክንሆን ድረስ በንሥሓ እየታደስን እስከ ዕለተ ሞታችን መቀጠል አለብን። ተስፋ በንሥሓ እና በይቅርታ ይቀጥላል። በበደል ዳዊትን መስለነው ይሆናል። ኑ በሉ በንሥሓም እንምሰለው። የሰይጣን ዋና መደበኛ ሥራ ሰውን ማሳሳት ነው። ሰውም በሰይጣን ተንኮል ይታለልና ይወድቃል። ከዚህ በኋላ ሰይጣን ከዚህ በኋላ ንሥሓ ብትገባም ዋጋ የለህም ትልቅ በደል ሰራህ እያለ ተስፋ ለማስቆረጥ ይሞክራል። ነገር ግን በንሥሓ የማይወገድ ኃጢዓት ስለሌለ ሰይጣን በእኛ ላይ የገነባውን የኃጢዓት ክምር በንሥሓ ማጥፋት እንችላለን። ሰይጣን ራሱ አሳስቶ ተስፋ ለማስቆረጥ ብዙ ይጥራል። ሰይጣንን ማሸነፍ የምንችለው ተስፋ ባለመቁረጥ እና በትሕትና ሆነን ረድኤተ እግዚአብሔርን በመጠየቅ ነው።
1.3K views12:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 10:02:33 #ጥበብ
የእውቀት ፍሬ ጥበብ ነው። የጥበብ መጀመሪያ ደግሞ ነቢዩ እንደተናገረው እግዚአብሔርን መፍራት ነው። እግዚአብሔርን መፍራት ደግሞ መገለጫው ትእዛዙን መስራት እና ማክበር ነው። ሦስት ዓይነት ጥበብ አለ። እነዚህም:-
፩) ጥበብ ሥጋዊ
፪) ጥበብ መንፈሳዊ
፫) ጥበብ ሰይጣናዊ
ናቸው። ጥበብ ሥጋዊ የሚባለው የማረስ ጥበብ፣ የሳይንስ ጥበብ፣ አጠቃላይ ፍጻሜያቸው በዚህ ምድር እስካለን ብቻ የሚጠቅሙንን ነገሮች ብቻ አውቆ በእነዚያ ብቁ ባለሙያ መሆን ነው።

ጥበብ ሰይጣናዊ የሚባለው ሌላውን ለመጉዳት የሚያሴሩት ሴራ እና ሽንገላን የሚያጠቃልል ነው። ወአርዌ ምድር ይጠበብ እም ኩሉ ሲል እባብ ግን ከሁሉ ይልቅ ተንኮለኛ ነበር ማለት ነው። ሰይጣናዊ ጥበብ ሰውን ከፈጣሪው ሕግ ለማውጣት የሚያሴሩት ሴራ ነው። ለምሳሌ አታመንዝር የሚለውን ሕግ ለማስሻር ሰይጣን የአለባበስ ጥበብ ብሎ ለዝሙት የሚያነሳሱ ልብሶችን ያስለብሳል። ሰይጣን ሰውን ከእግዚአብሔር ሕግ ለማውጣት የሚጠቀምባቸው ጥበቦች ሁሉ ሰይጣናዊ ጥበቦች ይባላሉ። ሰይጣን ጽሉመ ገጽ ሆኖ ሳለ የብርሃን መልአክ መምሰል ፣ ምትሐት ማሳየት፣ ምትሐታዊ ተአምር መስራት፣ ሰይጣናዊ ጥበቦች ናቸው።

መንፈሳዊ ጥበብ የሚባሉት ግን ሰውን ለዘለዓለማዊ ሕይወት የሚያበቁ ጥበቦች ናቸው። እነዚህም ጾምን፣ ጸሎትን፣ ስግደትን፣ ምጽዋትን የመሳሰሉ ናቸው።ራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ጥበብ ይባላል። ጥበብሰ መድኃኒነ ውእቱ እንዳለ ቅዳሴ። ጥበብ የሚባለው ፍቅር ያለበት ብልህነት ነው። የጥበብ መሰረት ራሱ ፍቅር ነው። ጥበብ እውነት ነው። አባቶቻችን በጥበብ ኖረዋል። በጥበብ ሃይማኖታቸውን ጠብቀዋል። በጥበብ አስተምረዋል።

#ትጋት & #ጽናት
ትጋት የስንፍና ተቃራኒ ነው። ሰው ባለው ዘመን ሁሉ ተግቶ መስራት ይገባዋል። መንፈሳዊ ሥራዎች ሁሉ የሚሰሩት በትጋት በጽናት ነው። ቅዱሳን እስከ አስረኛው የቅድስና መዓርግ የደረሱት በትጋት ነው። መካከል ላይ ስንፍና አላስገቡም። ከበለጠ ሥራ ወደ በለጠ ሥራ እየተሸጋገሩ ነው የኖሩት። ጥበብ ሥጋዊም ሆነ ጥበብ መንፈሳዊ ከግብ የማያደርሰን ትጋት ካልተለየው ነው። ትጋት የተለየው ጥበብ መጨረሻው ድንቁርና ይሆናል። ብዙ ርቀት የሚያስኬድ መንገድ በአንድ እርምጃ ይጀመራል። ሳንሰንፍ ሁለት ሦስት እያልን ከሄድን ካሰብንበት እንደርሳለን። በመንፈሳዊ ሕይወትም መራመድ ከጀመርን በኋላ ወደ ኋላ ማለትና መቆም አያስፈልግም። በትጋት መራመድ አለብን። ፈተናዎች ሲያጋጥሙን እንኳ እነርሱ ወደኋላ ሊጎትቱን አይገባም። ንሥሓ እየገባን ወደፊት መገስገሳችንን አንተው።
684 views07:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 07:26:37 #ስግደት
ስግደት አክብሮትን፣ መውደድን፣ መታዘዝን፣ እሺ ባይነትን መግለጫ መንገድ ነው። በባሕርይው ክቡር የሆነ እግዚአብሔርን እንደምናከብረው የምንገልጠው ለእርሱ በመስገድ ነው። ስግደት አፈጻጸሙ በሦስት ይከፈላል። እነዚህም:-
፩) አድንኖ
፪) አስተብርኮ
፫) ወዲቅ
ናቸው። አድንኖ የሚባለው ራስን ጎንበስ በማድረግ የምንሰግደው ስግደት ነው። አስተብርኮ የሚባለው ስግደት ደግሞ ጉልበታችንን መሬት እያስነካን የምንሰግደው ስግደት ነው። ወዲቅ የሚባለው ስግደት ደግሞ ግንባራችንን መሬት እያስነካን የምንሰግደው ስግደት ነው። የማይሰገድባቸው ጊዜያት የሚከተሉት ናቸው።
፩) በዕለተ እሑድ
፪) በዕለተ ቅዳሜ (ሰንበት)
፫) በበዓለ ሃምሳ
፬) ከቆረብን በኋላ
፭) በጌታ በዓላት
፮) በድንግል ማርያም በዓላት
፯) በቅዱስ ሚካኤል በዓል
ናቸው። በእነዚህ ጊዜያት አይሰገድም። ነገር ግን በሰሙነ ሕማማት ማንኛውም በዓል ቢውል ይሰገዳል። የስቅለት ቀን በዓለ ማርያምም ቢውል፣ በዓለ ሚካኤልም ቢውል፣ በዓለ እግዚእም ቢውል ይሰገዳል። ስግደት ሁለት ዓይነት ነው። ይኽውም የባሕርይ ስግደትና የጸጋ ስግደት ተብሎ ይከፈላል። የባሕርይ ስግደት ወይም የአምልኮ ስግደት ለፈጣሪ ብቻ የምንሰግደው ስግደት ነው። የጸጋ ስግደት የምንለው ደግሞ እግዚአብሔር ላከበራቸው ቅዱሳን የምንሰግደው ስግደት ነው። ከዚህ በተጨማሪ ለነገሥታት ለተከበሩ ሰዎች ለሽማግሌዎች ታዛዥነታችንን እና አክብሮታችንን ለመግለጽ ጎንበስ በማለት እጅ እንነሳለን። የባሕርይ ስግደት ግን ለፈጣሪ ብቻ ይሰገዳል።
990 views04:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-02 21:40:09 #ጾም
ጾም ለተወሰነ ጊዜ ከምግብ መከልከል፣ ከጥሉላት መከልከል ነው። ጾም ክፉ ፈቃድን ለማስወገድ፣ መልካም ፈቃድን ለማስረጽ፣ ጽሙናን አርምሞን ለመያዝ ይጠቅማል። ጾም ትፌውስ ቁስለ ነፍስ እንዲል ጾም የነፍስን ቁስል ትፈውሳለች፣ ጾም ኃጢዓትን ያስተሰርያል። በመጾም በረከተ ሥጋን በረከተ ነፍስን እናገኛለን። ንጹም ጾመ ወናፍቅር ቢጸነ ወንትፋቀር በበይናቲነ። ጾምን እንጹም፣ ባልንጀራችንንም እንውደድ፣ እርስ በእርሳችንም እንዋደድ እንዲል። ሁለት ዓይነት ጾም አለ። እኒህም የፈቃድ ጾምና የአዋጅ ጾም ናቸው። የፈቃድ ጾም በራስ ተነሳሽነት የሚጾሙት ጾም ነው። ግዴታ የለበትም። ለምሳሌ የጽጌ ጾም የፈቃድ ጾም ነው። ስለዚህ በዚህ ጊዜ የሚበላም ይበላል። የሚጾመውም ይጾማል። ይህ ክርስቲያናዊ ግዴታ አይደለም። ሁለተኛው የጾም ዓይነት የአዋጅ ጾም ነው። ይህም ማንኛውም ኦርቶዶክሳዊ ሰባት ዓመት ከሆነው በኋላ የሚጾመው ጾም ነው። እኒህን አጽዋማት መጾም ክርስቲያናዊ ግዴታ ነው። የአዋጅ አጽዋማት የሚባሉት ሰባት ናቸው። እነዚህም:-
፩) ጾመ ድኅነት (ዓርብ ረቡዕ)
፪) ጾመ ኢየሱስ (ዐቢይ ጾም)
፫) ጾመ ማርያም (ፍልሰታ)
፬) ጾመ ነቢያት
፭) ጾመ ሐዋርያት
፮) የነነዌ ጾም
፯) የገሐድ ጾም (ጋድ)
ናቸው።የዐቢይ ጾም የመጀመሪያው ሳምንት እስከ ፲፪ ሰዓት ይጾማል። ከዚያ ቀጥሎ ያሉ ሳምንታት እስከ ኒቆዲሞስ ዓርብ እስከ ፲፩ ሰዓት ይጾማሉ። ከሆሳእና እስከ ትንሣኤ ያለው ሰሙነ ሕማማት እስከ ምሽቱ ፩ ሰዓት ይጾማል። ሌሎች አጽዋማት እስከ ፱ ሰዓት ይጾማሉ። የልደትም የጥምቀትም ገሐድ አላቸው። ጥምቀት ወይም ልደት ሰኞ ከዋለ ገሐድ እሑድ ቀን ብቻ ይውላል እንጂ ሦስት ቀን ወይም ሁለት ቀን አይጾምም። ፍትሐ ነገሥቱ የበዓሉን ዋዜማ አለ እንጂ የዋዜማውን ዋዜማ አይልምና። ሌላው በዘመነ ዮሐንስም የነቢያት ጾም ህዳር ፲፭ ይጀምራል። እንጂ ፲፬ አይጀምርም። ሁልጊዜም በ፲፭ ይጀመራል። በዓለ ልደቱ ግን በዘመነ ዮሐንስ በ፳፰ ይውላል። {ይህንንም ሲኖዶሱ ተመካክሮ ሁልጊዜም በ፳፱ ቢያደርገው መልካም ነበር}። በዚህ ምክንያት ጠብ ክርክር ሊኖር አይገባም። ሁልጊዜም ቢሆን ሥርዓት ተኮር ጉዳዮችን ሲኖዶሱ ባለው ይጸናሉ።

ንጹም ጾመ
ወናፍቅር ቢጸነ
ወንትፋቀር በበይናቲነ
677 views18:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-02 16:57:38 #ምስጋና
ዘፋኝነት ክርስቲያናዊ ሥራ አይደለም
ዘፋኝነት የዝሙት ፊታውራሪ፣ የስሜታዊነት አባት፣ የእውነት እና የአመክንዮ ጠላት ነው። ዘፋኝነት ኃጢዓት ነው። ይህም ዘፈን ማዳመጥንም፣ መዝፈንንም ያመለክታል። ሰው በተፈጥሮ ከተደነቀ እንኳን የተፈጥሮ ባለቤት የሆነውን እግዚአብሔርን ያመስግን። ሰይጣን ዘፈንን ኪነ ጥበብ በማለት የጥበብ ስም ቢያላብሰውም ነገር ግን ዘፈን መንፈሳዊ ጥበብ አይደለም። ሰው የተፈጠረ ፈጣሪውን አመስግኖ በደስታ ይኖር ዘንድ ነው። ሰው የተፈጠረበትን ዓላማ እየኖረ ነው የሚባለው ፈጣሪውን ሲያመሰግን ነው። በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ እግዚአብሔር በዜማ በማኅሌት ይመሰገናል። የዜማን የማኅሌትን ስልት ስልቱን የሚያስተምሩን ደግሞ አቋቋም እና ድጓ ናቸው። ይህንን ስልት ከመምህራን ስር ቁጭ ብለን እንማረው። ምስጋና ለተደረገልንና ለሚደረግልን መልካም ነገር ለፈጣሪ የምናቀርበው የደስታ እና የፍቅር ስጦታ ነው። ክርስቲያን መከራ ሲደርስበት ይጸልያል። ሁልጊዜም ደግሞ የፈጠረውን ፈጣሪ፣ በመስቀል ተሰቅሎ ያዳነውን ፈጣሪ ያመሰግናል።

ሁልጊዜም ቢሆን እግዚአብሔርን እናመስግን። ንሴብሖ ለእግዚአብሔር ስቡሐ ዘተሰብሐ። ምስጉን ሆኖ የተመሰገነ እግዚአብሔርን እናመስግነው። ምነው ምስጉን ሆኖ ለምን አለ ከተባለ ክፉ ሆነው ባለማወቅ የሚመሰገኑ እና የሚመለኩ አሉና ከዚያ ሲለይ ነው። እግዚአብሔር ግን ፈጥሮ የሚገዛ በባሕርይው ምስጉን የሆነ ስለሆነ ስቡሐ ዘተሰብሐ አለ። ፈጣሪን ለምን እናመሰግነዋለን?
________
፩) ለክብር ስለፈጠረን
፪) ብንሞት ተሰቅሎ ስላዳነን
፫) የንሥሓ እድሜን ሰጥቶ እስካሁን ሰዓት ስላቆየን
፬) ሥጋውን ደሙን ሰጥቶ ሕይወታችንን ስለቀደሰልን
፭) የሚመግበን፣ የሚያኖረን እርሱ ስለሆነ
፮) ዝናሙን የሚያዘንብልን፣ ፀሐይን የሚያወጣ፣ በጠቅላላ ተፈጥሮን ለእኛ የሰጠን እርሱ ስለሆነ
፯)__ወዘተ ብዙ ብዙ መጥቀስ ይቻላል።
1.4K views13:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-02 16:23:10 #ጸሎት
ጸሎት ማለት ምስጋና ያለበት ልመና ማለት ነው። በጸሎት ኃጢዓትን መታመን (ተአምኖ ኃጣውእ) አለ፣ በጸሎት ዕበያተ እግዚአብሔርን መመስከር አለ። በጸሎት እውነትን መመስከር አለ። በጸሎት ይቅርታ አለ። ጸሎት ብሂል ተናግሮ ምስለ እግዚአብሔር። ጸሎት ማለት ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር ማለት ነው። በፈጣሪ ፊት የምንናገረው ንግግር ነው። እርሱም በፍቅር የልጆቹን ንግግር ሰምቶ ምላሽ የሚሰጥበት ነው። ጸሎት ሥርዓት አለው። ይኽውም:-
፩) ቀጥ ብሎ መቆም
፪) ፊትን ወደ ምሥራቅ ማዞር
፫) ወገብን መታጠቅ (በንጽሕና መቆም)
፬) ማማተብ
፭) ዓይንን ከቃሉ ከቃሉ ልብን ከምሥጢሩ አድርጎ መጸለይ
ናቸው። ስንቆም በደንብ ነጠላችንን መስቀለኛ ለብሰን ይሆናል። ከዚህ በኋላ ውዳሴ ማርያምን፣ መዝሙረ ዳዊትን፣ ትምህርተ ኅቡዓትን፣ ወንጌልን፣ የመሳሰለውን መጸለይ ነው። መሻታችንን ለፈጣሪ ማሳወቅ ነው። ይህም እግዚአብሔር አስቀድሞ ፍላጎታችንን የማያውቅ ሆኖ አይደለም። በእኛ መናገር እና በእኛ ፈቃድ መልካሙን ሁሉ ይሰጠን ዘንድ ነው። ማንኛውም ክርስቲያን ቢያንስ በሰባቱ ጊዜያት መጸለይ አለበት። ሰባቱ ጊዜያት የተባሉትም:-
፩) ጠዋት
፪) ሦስት ሰዓት
፫) ስድስት ሰዓት (ቀትር)
፬) ዘጠኝ ሰዓት
፭) ሠርክ
፮) ምሽት ሦስት ሰዓት
፯) ሌሊት ስድስት ሰዓት
ናቸው። ምክንያታቸውን ፍትሐ ነገሥት ስንማማር ስለገለጽነው ከዚያ ይመልከቱ። ሌላው ምግብ ልንበላ ስንጀምር ምግብን የሰጠንን እግዚአብሔርን አመስግነን አቡነ ዘበሰማያት ብለን እንበላለን። በልተን ከጨረስን በኋላም ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ ብለን አቡነ ዘበሰማያት ብለን እንጸልያለን። ከጸሎት ሁሉ አቡነ ዘበሰማያትን እና መዝሙረ ዳዊትን ስንደግም እግዚአብሔር ደስ ይሰኝብናል። ውዳሴ ማርያምን መድገምም ይገባል። መንገድ ስንሄድ፣ ሥራ ስንጀምር ወዘተ ጸልየን ብንጀምር ስራችን ይቀደሳል፣ ጉዟችን ይባረካል። በመከራ ሳለን ብንጸልይ እግዚአብሔር ከመከራው ያወጣናል። በጸሎት በረከተ ሥጋን በረከተ ነፍስን እናገኛለን።
1.4K viewsedited  13:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-02 08:57:07
የደብረ ኃይል ወደብረ ጥበብ በዓታ ለማርያም የአቋቋም ምስክር ጉባኤ ቤት። በማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቭዥን የተላለፈ።
1.8K views05:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ