Get Mystery Box with random crypto!

በትረማርያም አበባው

የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው
የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው
የሰርጥ አድራሻ: @betremariyamabebaw
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.25K
የሰርጥ መግለጫ

አቀድም አእኵቶቶ ለእግዚአብሔር

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-06-12 09:33:33 ለልጅዎ የግእዝ ስም ማውጣት ከፈለጉም እነሆ
ግእዝ__አማርኛ
፩) መዓርዒር__ጣፋጭ
፪) አሜር__ፀሐይ
፫) አርያም_ሰማይ
፬) አምኃ_እጅ መንሻ
፭) ብሥራት___የምስራች
፮) ሰሎሜ_ሰላም
፯) አሜን__እውነት/ይሁንልኝ
፰) ሠዊት__እሸት
፱) ጸገየ___አበበ
፲) አስካል____ፍሬ
፲፩) ልዑል____ከፍ ያለ
፲፪) ሣህሉ____ይቅርታው
፲፫) ቀጸላ_አክሊል
፲፬) ሐመልማል___የለመለመ
፲፭) ከሃሊ_የሚችል ቻይ
፲፮) ጸዳሉ_መብራቱ
፲፯) ፈትለ ወርቅ____የወርቅ ፈትል
፲፰) ፊደል_ፊደል
፲፱) ማኅተም____ማተሚያ
፳) ሥዩም__የተሾመ ሹም
፳፩) ስብሐት____ምስጋና
፳፪) ስቡሕ_ምስጉን
፳፫) ተቅዋም_መቅረዝ
፳፬) ንጹሕ_የነጻ
፳፭) ሰላማ__ሰላም
፳፮) አዳም__ያማረ
፳፯) ዳግም_የደገመ
፳፰) ግሩም_ተፈሪ
፳፱) ጥዑም____የሚጣፍጥ
፴) ፍጹም__የተቀባ
፴፩) ይኄይስ____ተሻለ
፴፪) ሐዳስ/ሐዲስ___አዲስ
፴፫) ሕዳሴ__መታደስ
፴፬) ሰንኮሪስ_መምህር
፴፭) መቅደስ_ማመስገኛ
፴፮) ሞገስ__ባለሟል የተወደደ
፴፯) ትዕግሥት_መቻል
፴፰) ንጉሥ__የነገሠ
፴፱) ወራሲ__ወራሽ
፵) ውዳሴ__ምስጋና
፵፩) ጌራወርቅ____የወርቅ ሥራ
፵፪) ማኅደር_ማደሪያ
፵፫) ምሕረት_ይቅርታ
፵፬) መሓሪ__ይቅር ባይ
፵፭) ሠምረ__ወደደ
፵፮) ሥሙር_ተወዳጅ
፵፯) ሥምረት____መወደድ
፵፰) ነጸረ__ተመለከተ
፵፱) ምሥጢሩ____ምሥጢሩ
፶) መራሒ____መሪ
፶፩) ፍሥሓ_ደስታ
፶፪) አእመረ____አወቀ
፶፫) አእምሮ____እውቀት
፶፬) ፍቅር__መውደድ
፶፭) ክቡር__የከበረ
፶፮) ደብሩ__ተራራው
፶፯) ተግባር_ሥራ
፶፰) ረቂቅ__ረቂቅ
፶፱) መብረቁ____መብረቁ
፷) ነጸብራቅ__ነጸብራቅ

፷፩) ይባቤ___እልልታ
፷፪) ጥበቡ___ብልሃቱ
፷፫) መሠረት__መሠረት
፷፬) ብሑት___ስልጡን
፷፭) ትሕትና___ትሕትና
፷፮) ተከሥተ__ተገለጠ
፷፯) ሃይማኖት_ሃይማኖት
፷፰) በየነ__ፈረደ
፷፱) መኰንን____ገዢ
፸) በጽሐ__ደረሰ
፸፩) መስፍን____የሚገዛ
፸፪) ምስፍና____ግዛት
፸፫) ክርስቲያን____ክርስቲያን
፸፬) ወሰን__ድንበር
፸፭) መዋዒ_አሸናፊ
፸፮) ትንሣኤ_መነሳት
፸፯) ነቅዐ ሕይወት_የሕይወት ምንጭ
፸፰) ገዛኢ__ገዢ
፸፱) ምሕርካ ክርስቶስ___የክርስቶስ ምርኮ
፹) ባራኪ____የሚባርክ
፹፩) መልአክ____አለቃ
፹፪) በረከት____በረከት
፹፫) ህላዌ_መኖር
፹፬) ኂሩት_ቸር የሆነች
፹፭) ልባዌ_ማስተዋል
፹፮) ቤዛዊት_ያዳነች የምታድን
፹፯) ስርጋዌ____ሽልማት
፹፰) ስርጉት____የተሸለመች
፹፱) ተስፋ_ተስፋ
፺) ኬንያ__ብልሃተኛ
፺፩) ኖላዊ__ጠባቂ
፺፪) መርዓዊ____ሙሽራ
፺፫) ማዕዶት____መሻገሪያ
፺፬) ወልታ____መከታ/ጋሻ
፺፭) ሐዋዝ____ያማረ
፺፮) ግእዛን____ነጻነት
፺፯) ሕሊና____ሕሊና
፺፰) ማኅሌት____ምስጋና
፺፱) ኅሩይ__ምርጥ
፻) ሲሳይ__ምግብ
፻፩) ሠናይ____ያማረ
፻፪) ፈታሒ____የሚፈርድ
፻፫) ሐሴት____ደስታ
፻፬) ትርሲት_ሽልማት
፻፭) ተዋናዪ_ተጫዋች
፻፮) ዐቢይ___ከፍ ያለ
፻፯) ትውፊት_ስጦታ
፻፰) ኃያል_የበረታ
፻፱) ጽጌ__አበባ
፻፲) ፍሬሕይወት____የሕይወት ፍሬ
፻፲፩) ምዕዳን_ምክር
፻፲፪) ንኡድ___ያማረ
፻፲፫) ነገደ___ሄደ
፻፲፬) ነጎድጓድ____ነጎድጓድ
፻፲፭) ጸዓዳ_ነጭ
፻፲፮) ሠረጸ_በቀለ
፻፲፯) ደምፀ____ተሰማ
፻፲፰) ሮሐ_ወለወለ/አራገበ/አናፈሰ
፻፲፱) ናርዶስ_ሽቱ
፻፳) እፀ ሕይወት___የሕይወት እንጨት

በትረማርያም አበባው (በነገራችን ላይ በትረ ማርያም ማለት የማርያም ወገን ማለት ነው። በትር ወገን ተብሎ እንደሚተረጎም አስተውል)
1.0K views06:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 09:33:33 Reposted
_ ስም____ትርጉም
1 ፊላታዎስ፦የአምላክ ወዳጅ
2 ሮብዓም፦ሕዝብ ይብዛ
3 ቴዎድሮስ፦የእግዚአብሔር ስጦታ
4 ሮቤል፦እነሆ ወንድ ልጅ
5 ማራናታ፦ጌታ ሆይ ና
6 ቤቴል፦የእግዚአብሔር ቤት
7 ቄርሎስ፦የተመረጠ ምርጥ
8 እስጢፋኖስ፦አክሊል
9 ሳውል/ሳኦል፦ከእግዚአብሔር የተለመነ
10 ሴዴቅያስ፦የእግዚአብሔር ጽድቅ
11 ፊቅጦር፦ኀዘኔን አራቀልኝ
12 ንፍታሌም፦ታጋይ የሚታገል
13 ዮርዳኖስ፦ወራጅ
14 ዮአስ፦እግዚአብሔር ሰጥቷል
15 ገነት፦የአትክልት ስፍራ
16 ፊልድልፍያ፦የወንድማማች ፍቅር
17 ዲና፦ፈረደ
18 ማኑሄ፦እረፍት
19 መልሕቅ፦ከብረት የተሠራ የመርከብ ማቆሚያ
20 ራማ፦ከፍታ
21 ኤርምያስ፦እግዚአብሔር ከፍ ያደርጋል
22 ሐና፦ ስጦታ
23 ሕርያቆስ፦ኅሩይ
24 ፊልጶስ፦ወንድም ወዳጅ
25 ቶማስ፦ፀሐይ
26 ጎርጎርዮስ:-ንቁሕ የተጠበቀ
27 ማትያስ፦ፀሐይ
28 ቀሌምንጦስ፦ግንብ
29 አቤል፦በግ ወይም ደመና
30 ኖኅ፦ደስታ
31 ሴም፦ተሾመ
32 ይሥሐቅ፦ደስታ አንድም
33 ሙሴ፦የውሃ ልጅ
34 አሮን፦የእግዚአብሔር ተራራ
35 ጌዴዎን፦እግዚአብሔር ኃያል ነው
36 እሴይ፦ዋጋየ
37 አሚናዳብ፦መንፈስቅዱስ
38 ዳዊት፦የተወደደ ልበ አምላክ
39 ዕንባቆም፦ጠቢብ አዋቂ አስተዋይ
40 ሄኤሜን፦ምኞቴን አገኘሁ
41 አሞጽ፦እግዚአብሔር ጽኑ ነው
42 ዮናስ፦ርግብ
43 ሐጌ፦የእግዚአብሔር መልእክተኛ
44 ራኄል፦በግዕት
45 ዕዝራ፦ረዳቴ
46 ሔርሜላ፦ከክብር ዘመድ የተገኘች
47 መርቆሬዎስ፦የአባት ወዳጅ
48 ኤጲፋንዮስ፦ምስጢር ገላጭ
49 ሜሮን፦የተባረከ ሽቱ
50 ሱላማጢስ፦ሰላማዊት
51 ሶምሶን፦ፀሐይ
52 ብንያም፦የቀኝ እጄ ልጅ
53 ማርታ፦እመቤት
54 ሊዲያ፦ፈራሂተ እግዚአብሔር
55 ኤፍሬም፦ፍሬያማ ፍሬው
56 ኤፍራታ፦ክብርት የተከበረች
57 ታዴዎስ፦ተወዳጅ
58 ኢየሩሳሌም፦የሰላም ሀገር
59 ሄኖስ፦ሰው
60 ሰሎሜ፦ሰላም
61 ሩሐማ፦ምሕረት
62 ዮዳሔ፦እግዚአብሔር ያውቃል
63 ቴዎፍሎስ፦የእግዚአብሔር ወዳጅ
64 ኑኃሚን፦ደስታየ
65 ናትናኤል፦የእግዚአብሔር ስጦታ
66 አዛሄል፦እግዚአብሔር ያያል
67 ኢዮስያስ፦እግዚአብሔር ይደግፋል
68 ኢዩኤል፦እግዚአብሔር አምላክ ነው
69 በርናባስ፦የመጽናናት ልጅ
70 ሶፎንያስ፦እግዚአብሔር ሰውሯል/ጠብቋል
71 ሕዝቅኤል፦እግዚአብሔር ብርታትን ይሰጣል
72 ኬልቅያስ፦እድል ፈንታየ እግዚአብሔር
73 ሳሙኤል፦እግዚአብሔር ሰማኝ
74 ሚኪያስ፦ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው!
75 ሆሴዕ፦እግዚአብሔር ያድናል
76 ሔዋን፦የሕያዋን ሁሉ እናት
77 ሕዝቅያስ፦እግዚአብሔር ኃይሌ ነው
78 መልከጼዴቅ፦የሰላም ንጉሥ
79 ሚልኪያስ፦መልእክተኛየ
80 ሣራ፦ልዕልት
81 ስምዖን፦ሰማ
82 ብንያም፦የቀኝ እጄ ልጅ
83 ናሆም፦መጽናናት ማለት ነው።
84 ናታን፦ እግዚአብሔር ሰጥቷል
85 አልዓዛር፦ትርጉሙ እግዚአብሔር ረድቷል
86 አስቴር፦ኮከብ
87 አቤሜሌክ፦የንጉሥ አገልጋይ
88 አቤሴሎም፦አባቴ ሰላም ነው
89 አብድዩ፦የእግዚአብሔር አገልጋይ
90 አብራም፦ታላቅ አባት
91 አብርሃም፦የብዙዎች አባት
92 አኪያ፦እግዚአብሔር ወንድሜ ነው
93 አክዐብ፦የአባት ወንድም
94 ባሮክ፦ቡሩክ
95 አዳም፦መልካሙ
96 ኢሳይያስ፦ እግዚአብሔር ደኅንነት ነው
97 ባርቅ፦መብረቅ
98 ኢያሱ፦እግዚአብሔር አዳኝ ነው
99 ኢዮሳፍጥ፦እግዚአብሔር ፈርዷል
100 ኢዮራም፦እግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ
101 ኢዮርብዓም፦ሕዝቡ እየበዛ ይሄዳል
102 ቤተልሔም፦የእንጀራ ቤት
103 ኢዮአስ፦እግዚአብሔር ሰጥቷል
104 ኢዮአቄም፦እግዚአብሔር አቆመ
105 ኢዮአብ፦እግዚአብሔር አባት ነው
106 ኢዮአታም፦እግዚአብሔር ፍጹም ነው
107 ኢዮአካዝ፦እግዚአብሔር ይዟል
108 ኤልሳዕ፦እግዚአብሔር ደኅንነት ነው
109 ኤልያስ፦እግዚአብሔር አምላክ ነው
110 ኤልያቄም፦እግዚአብሔር ያስነሳል
111 ኤዶም፦ቀይ/የገነት ሌላ ስም ነው
112 እስራኤል፦ከእግዚአብሔር ጋር ይታገላል ያሸንፍማል
113 ኤልሳቤጥ፦እግዚአብሔር መሐላየ ነው
114 ኤልሻዳይ፦ሁሉን ቻይ አምላክ
115 ሀሌሉያ፦እግዚአብሔርን አመስግኑ
116 ሰሎሞን፦ሰላማዊ
117 ኬብሮን፦ኅብረት
118 አዛርያስ፦እግዚአብሔር ረድቷል
119 ኤደን፦ደስታ
120 ዖዝያን፦እግዚአብሔር ኃይሌ ነው
121 ዘካርያስ፦እግዚአብሔር ያስታውሳል
122 ይሳኮር፦ ዋጋዬ
123 ይዲድያ፦በእግዚአብሔር የተወደደ
124 ዮሐናን፦እግዚአብሔር ጸጋ ሰጪ ነው
125 ዮሐንስ፦እግዚአብሔር ጸጋ ነው
126 ዮሴፍ፦ይጨምር
127 ዮናስ፦ርግብ
128 ዮናታን፦እግዚአብሔር ሰጥቷል
129 ዮአኪን፦እግዚአብሔር ያቆማል
130 ዮካብድ፦እግዚአብሔር ክብር ነው
131 ምናሴ፦ማስረሻ
132 ዮፍታሔ፦እግዚአብሔር ይከፍታል
133 ዲቦራ፦ንብ
134 ዳንኤል፦እግዚአብሔር ፈራጅ ነው
135 ጎዶልያስ፦እግዚአብሔር ታላቅ ነው
136 ጽዮን፦አምባ
137 ጳውሎስ፦ብርሃን ማለት ነው።
138 ሴት፦ምትክ ማለት ነው።
139 ጴጥሮስ፦አለት ማለት ነው።
140 ሄኖክ፦ታደሰ ማለት ነው።

ምንጭ:-ቅዱሳት መጻሕፍት ከመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት እንዲሁም የአንድምታ ትርጓሜ መጻሕፍት

በትረማርያም አበባው
1.1K views06:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 21:08:27
የቤተክርስቲያንን ዶግማና ቀኖና የመጠበቅና የማስጠበቅ ተግባር ለጳጳሳት ብቻ የሚሰጥ ጉዳይ አይደለም። የማንኛውም አማኝ መንፈሳዊ ግዴታ ነው። የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ባለቤት እግዚአብሔር ነው። ጳጳስም ቢሆን፣ መነኵሴም ቢሆን፣ ምእመንም ቢሆን እግዚአብሔር የገለጠውን እውነት ከተቃወሙ ያለምንም ፍርሀት በአደባባይ ሊቃወሟቸው ይገባል።

እግዚአብሔር ያለው ይተግበር።
ቅዱሳን ሊቃውንት ያሉት ይተግበር።
ቀኖና ይከበር።

የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ በሰፊው አቀርባለሁ። ኑ እንጠያየቅ።

የዩቲይብ ቻናሌ:-
ንሕነ ዘክርስቶስ
https://www.youtube.com/@edenawizechristos ነው።

የፌስቡክ ገጼ
Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።
2.3K views18:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 07:58:33
ይህ የየኔታ ሊቀ ብርሃናት ኤልያስ አድማሴ የዩቲይብ ቻናል ነው። ሰብስክራይብ አድርጋችሁ ቃለ እግዚአብሔርን ከምንጩ ተማሩ። ሊንኩ https://youtube.com/@nolawi8059 ነው።

ቢያንስ 1000 ሰብስክራይብ እንዲሞላ ሼር ሰብስክራይብ እናድርግ።
2.9K viewsedited  04:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 07:44:11

2.8K views04:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 07:44:11 ሊቀ ብርሃናት ኤልያስ አድማሴ
2.4K views04:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 22:38:50
ተዘከሩ መኳንንቲክሙ ዘነገሩክሙ ቃለ እግዚአብሔር። የእግዚአብሔርን ቃል የነገሯችሁን መምህሮቻችሁን አስቡ።
የአንዳንድ መምህራን ከሚያስተምሩት ትምህርት በተጨማሪ ሕይወታቸው ራሱ ትልቅ የሕይወት ትምህርት ይሆናል።

የኔታ ዲበኩሉ መኮንን (የድጓ መምህር)
ለየኔታ ረጅም እድሜን ይስጥልኝ።
2.9K views19:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 22:00:04
የኔታ ሊቀ ብርሃናት ኤልያስ አድማሴ
የመጻሕፍተ ብሉያት አንድምታ ትርጓሜን ያስተማሩኝ መምህሬ ናቸው። የኔታ የጎንደር ደብረ መድኃኒት ዐቢየ እግዚእ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ወቅዱስ መርቆሬዎስ የብሉያትና የሐዲሳት ትርጓሜ ጉባኤ ቤት መምህር የነበሩና እና በተጨማሪም የቅኔ መምህር ናቸው። ረጅም እድሜና ጤናን ይስጥልኝ።
2.9K viewsedited  19:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 12:27:58 በስባሳ እና ጨምላቃ መንግስት

ሰውዬው በመንግስት ተግባር እየተብሰለሰለ ነበር ሲጠጣ የነበረው። ከጠጅ ቤት ጥግብ ብሎ መንገድ ላይ እየተንገዳገደ፣

"ይሄ በስባሳ ጨምላቃ ሀጠ*ው መንግስት። በስባሳ የበሰበሰ ጨምላቃ መንግስት" እያለ ፖሊስ ያዘው።

ፍርድቤት ቀርቦ ክሱ ሲነበብ፣

"የኢፌድሪን መንግስት ‘በስባሳ እና ጨምላቃ‘ በማለት ተሳድበሃል" ይላል።

የእምነት ክህደት ቃል ሲጠየቅ

ወንጀሉን አልፈፀምኩም ይላል።

አቃቢህጉ ይጠይቀዋል:–

"በስባሳ እና ጨምላቃ መንግስት ማለትህን ትክዳለህ?"

"ብያለሁ አልክድም"

"ታዲያ የመንግስትን ስም በማጥፋት ወንጀል መፈፀምህን ለምን አታምንም?"

"እርግጥ ነው፣ ይሄ በስባሳ እና ጨምላቃ መንግስት ብያለሁ። ነገርግን የትኛው መንግስት በስባሳና ጨምላቃ እንደሆነ በስም አልጠቀስኩም"

"እንዴት?"

"ክቡር ፍርድቤት፣ በአለማችን ላይ ከሁለት መቶ በላይ መንግስታት አሉ። ከእነዚህ መንግስታት ውስጥ በስባሳ እና ጨምላቃ መንግስት የትኛው እንደሆነ በስም አልጠቀስኩም። ስለዚህ እኔ ይህ የኢትዮጵያ መንግስትን በስባሳና ጨምላቃ ነው ስለማለቴ ምንም ማስረጃ የለም"

ዳኛው መነፅራቸውም ዝቅ አድርገው እንዲህ አሉት፣

"በአለማችን ላይ ካሉ ከሁለት መቶ በላይ ሀገራት በስባሳውና ጨምላቃው የኛ መንግስት መሆኑን አንተም እኛም የቀረውም አለም ያውቃል። ምናለ ጊዜ ባንፈጅ?"

ምን ለማለት ነው?

ባለቤቱ ስሙን ከሩቅ ያውቃል

(ይህች ልጅት ሀሳቧን በሜካፕ ገለፀች። ስርዓቱ በህገመንግስቱ እና በአለማቀፍ የሰው ልጀች መብት ስምምነት መሰረት ሀሳብን በነፃነት መግለፅ ይፈቅዳል። ልጅቷ ይህን መብቷን በመጠቀም የራሷን ሀሳብ ገለፀች። ይኸው ተሰደብኩ ብሎ የጉማ ሽልማት አዘጋጅን አሰረ። ልጅቷ ላይም የእስር ማዘዣ አወጣ። ማንም የማይሳደድበት፣ አሳዳጅ ተሳዳጅ የሌለበት ስርዓት እንመሰርታለን ተብለን ነበረ። ቃል ታጠፈ)
3.5K views09:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 08:31:30 መስከረም አካባቢ ላይ "ቴዎድሮስ 2015 ዓ. ም ላይ ይነግሣል" ያላችሁት መች ነገሠ የት አለ?! ብየ ፖስት አድርጌ ነበር። አንዳንዶቹ ዓመቱኮ ገና እየተጀመረ ነው ተረጋጋ እንጂ ብለው ጻፉልኝ። እንግዲህ አሁን ሠኔ ወር ላይ ነን። እንግዲህ የቀሩን ሁለት ወራት ናቸው። በዚህ ሁለት ወር ውስጥ ሰርፕራይዝ ሊያደርገን አስቦ ይሆን?!

ይህ ማኅበር (ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን) ጥቂት ሰዎችን አጃጅሏል። ከሆነ ጉባኤ ቤት ሐዲስ ኪዳን የተማረ ሰውየ ኮብልሎ እንደ እሽኮኮ ዋሻ ለዋሻ እየተንከራተተ ነው። እና የሐዲስ ኪዳን ማኅተም ከመምህሩ ሲጠይቅ መምህሩ ና መጥተህ ውሰድ ይሉታል። ይህን ጊዜ ጎንደር 2013 ላይ ትጠፋለች ብለውኛል የበረሃ አባቶች አልመጣም አለ። መምህሩም የሚቀርህ ትምህርት ስላለ ማኅተም አልሰጥህም አሉት። ይኽው ጎንደርም አለች። ያ ባሕታዊም ዋሸ።

ውስጥ ለውስጥ ከመርመጥመጥ እውነት ያለው ባሕታዊ ካለ ይምጣ ከሊቃውንቱ ጋር ይነጋገር። ውሸቱ እንዳይታወቅበት ወቅታዊ ችግሮችን እየተነተነ እንዲህ ይሆናል እያለ የሚያሞኝን ጅል መከተል ግን ፈጽሞ አይገባም።

በነገራችን ላይ ቴዎድሮስ የሚባል ሰው አሁን በአባቶች ተቀብቶ የሆነ ገዳም ላይ እንዳለ አንድ አባላቸው ነግሮኛል። ያ ሰው ቴዎድሮስ መሆኑን በምን አረጋገጥክ ስለው መልስ የለም። ማንም እየተነሣ ቴዎድሮስ ነኝ እያለ የሚያጃጅለው ምእመን ሊኖር አይገባም።

ሳታውቁ በየዋህነት የተከተላችኋቸው ምእመን ካላችሁ ሊቃውንትን ጠይቁ፣ ንስሓ ግቡና ሥጋውን ደሙን ተቀበሉ። ይህንን ባታደርጉ ግን ሰይፍን ብትመረኮዙ ራሳችሁን ትጎዱታላችሁ።

የፌስቡክ ገጼ
Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።
3.8K views05:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ