__ ባሕረ ሐሳብ ክፍል ፫ __
የበዓላትና የአጽዋማት ተውሳክ።መባጃ ሐመር 29 እንደመጣ ክፍል ፪ ላይ አይተናል።ይኽውም ጥር 29 ቀን የነነዌ ጾም ትገባለች ማለት ነው።ሌሎቹ መቼ እንደሚውሉ ለማወቅ ይህን መባጃ ሐመር ከተውሳኮቻቸው ጋር እየደመርን እናገኘዋለን።የአጽዋማትና የበዓላት ተውሳክ እነሆ
የዐቢይ ጾም ተውሳክ 14
የደብረ ዘይት ተውሳክ 11
የሆሳእና ተውሳክ 2
የስቅለት ተውሳክ 7
የትንሳኤ ተውሳክ 9
የርክበ ካህናት ተውሳክ 3
የዕርገት ተውሳክ 18
የጰራቅሊጦስ ተውሳክ 28
የጾመ ሐዋርያት ተውሳክ 29
የጾመ ድኅነት ተውሳክ 1
ነው።ስለዚህ እኒህን ተውሳኮች ከመባጃ ሐመሩ ጋር እየደመርን በአላቱ አጽዋማቱ መቼ እንደሚውሉ ያሳውቁናል።ስለዚህ
ዐቢይ ጾም=14+መባጃ ሐመር
=14+29
=43
ስለዚህ ዓቢይ ጾም የካቲት 13 ይውላል ማለት ነው።መጥቅእ ጥቅምት ውሎ ስንደምረው ከ30 በላይ ከሆነ በ30 ገድፈን መጋቢት ላይ ይውላል።በ2015 ዐቢይ ጾም የካቲት 13 ይውላል።
ደብረ ዘይት=11+መባጃ ሐመር
=11+29
=40
መጋቢት 10 ደብረ ዘይት ይውላል ማለት ነው።መጥቅእ ጥቅምት ውሎ ይህ ድምር ከ30 ከፍ ካለ ግን በ30 ገድፈን ሆሳእና ሚያዝያ ላይ ይውላል ማለት ነው።
ሆሣዕና=2+መባጃ ሐመር
=2+29
=31
ሚያዝያ 1 ሆሳእና ይውላል ማለት ነው።
ስቅለት=7+መባጃ ሐመር
=7+29
=36
ሚያዝያ 6 ስቅለት ይውላል ማለት ነው
ትንሳኤ=9+መባጃ ሐመር
=9+29
=38
ሚያዝያ 8 ትንሳኤ ይውላል ማለት ነው።
ርክበ ካህናት=3+መባጃ ሐመር
=3+29
=31
ግንቦት 1 ቀን ርክበ ካህናት ይሆናል ማለት ነው
ዕርገት=18+መባጃ ሐመር
=18+29
=47
47 ከ30 በላይ ስለሆነ በ30 ስንከፍለው አንድ ደርሶ 17 ይተርፋል።ይህም ዕርገት ግንቦት 17 ይሆናል ማለት ነው።
ጰራቅሊጦስ=28+መባጃ ሐመር
=28+29
=57
ይህ ከ30 በላይ ስለሆነ በ30 ስናካፍለው 1 ደርሶ 27 ይተርፋል።ስለዚህ ጰራቅሊጦስ ግንቦት 27 ይውላል ማለት ነው።
ጾመ ሐዋርያት=29+መባጃ ሐመር
=29+29
=58
ይሆናል በ30 ስንገድፈው 1 ጊዜ ደርሶ 28 ይተርፋል።ስለዚህ ግንቦት 28 ጾመ ሐዋርያት ይገባል ማለት ነው።
ጾመ ድኅነት=1+መባጃ ሐመር
=1+29
=30
ስለዚህ ጾመ ድኅነት ግንቦት 30 ይጀምራል ማለት ነው።
።
__ ኢየዐርግ እና ኢይወርድ
__
እነዚህ በዓላት ኢየዐርግ (አይወጣም) ናን ኢይወርድ (አይወርድም) አላቸው ለምሳሌ የነነዌ ጾም ቢወርድ ቢወርድ ጥር 17 ይሆናል እንጂ ጥር 16 አይሆንም።እንዲሁም ቢወጣ ቢወጣ የካቲት 21 ይሆናል እንጂ የካቲት 22 ሊሆን አይችልም።ይህ ማለት የነነዌ ጾም ከጥር 17 እስከ የካቲት 21 ባለው ብቻ ይውላል ማለት ነው።በዚህ መሰረት የሌሎችንም እንመልከት
ኢይወርድ.......ኢየዐርግ
የነነዌ ጾም.............ጥር 17........የካቲት 21
ዓቢይ ጾም..............የካቲት 1......መጋቢት 5
ደብረ ዘይት.............የካቲት 28....ሚያዝያ 2
ሆሳእና....................መጋቢት 19...ሚያዝያ 23
ስቅለት...................መጋቢት 24....ሚያዝያ 28
ትንሳኤ..................መጋቢት 26.....ሚያዝያ 30
ርክበ ካህናት.........ሚያዝያ 20.......ግንቦት 24
ዕርገት..................ግንቦት 5..........ሰኔ 9
ጰራቅሊጦስ............ግንቦት 15.......ሰኔ 19
ጾመ ሐዋርያት...........ግንቦት 16.......ሰኔ 20
ጾመ ድኅነት.............ግንቦት 18..........ሰኔ 22
የበዓላትና የአጽዋማት ኢየዐርግና ኢይወርድ ይህንን ይመስላል።
።
የዘመን መለወጫ መስከረም ወይስ ጥር
በነገራችን ላይ የእኛ የዘመን መለወጫ መስከረም 1 ቀን ነው። እስራኤላውያንን በኦሪት እንደተጻፈው ጌታ ከግብጽ የወጣችሁበት ወር ሚያዝያ የዘመን መለወጫ ይሁናችሁ ብሏቸዋል። በእስራኤል ጥር የካቲት መጋቢት ክረምት ነው።ሚያዝያ የክረምት መውጫ ነው።የእኛ ክረምት ግን ሰኔ ሐምሌ ነሐሴ ነው። ክረምት የሚወጣበት መስከረም ስለሆነ
የዘመን መለወጫችን መስከረም ነው። ፈረንጆቹ ደግሞ ጌታ የተወለደበትን ታህሣስ 29 ጀምረው ዘመንን ይለውጣሉ። ያም ሆነ ይህ በአቡሻኽር ትምህርት እንደምናገኘው በዓለም ላይ በጣም ብዙ የዘመን አቆጣጠሮች አሉ። ስለዚህ የሁሉንም ከመቀበል ውጭ ይህ ስህተት ነው ይህ ልክ ነው ማለት አንችልም።ጌታ ግን የዘመን መለወጫ በሚያዝያ ይሁን ብሎ ስለዘመን መለወጫ የተናገረው ብቸኛው ቃል በኦሪት ይገኛል።
ይህ ሁሉ መደከሙ የዘመናትን ባለቤት እግዚአብሔርን ዘመኑን እያስታወስን ለማመስገን (ለአሥርቆት) ነው።ሁልጊዜ ቢሆን ጸሎታችንን የምንጀምረው ከዚህ በኋላ በሚገኘው መንገድ ነው። ውዳሴ ማርያምም ይሁን ሌላ ጸሎት ከአሥርቆት በኋላ ነው።አሥርቆቱም ይህ ነው።
ሃሌ ሉያ በዘንዜከር ሐሳባተ ሕጉ ወትእዛዛቲሁ ለእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ሐሳበ ነቢያት ወሐዋርያት ሐሳበ ጻድቃን ወሰማእት ሐሳበ ደናግል ወመነኮሳት ሐሳበ ኄራን መላእክት እንዘ ሀሎነ በዘመነ ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ (አስተውል ሉቃስ ጸሎት እያደረግክበት ያለው ዘመን ነው) ቡሩክ ያብጽሐነ እስከ ዘመነ ዮሐንስ ዜናዊ።ካልክ በኋላ ያለህበትን ዘመን ዓመተ ምህረት ዓመተ ዓለም አስበህ በ፸፻ወ፭፻፲፭ ኮነ ዓመተ ዓለም።በ፶፻ወ፭፻ ኮነ ዓመተ ኩነኔ ዓመተ ፍዳ።በ፳፩፲፭ ኮነ ዓመተ ምሕረት።ትልና በመቀጠል ያለህበትን ወር አንስተህ ለቀጣዩ ወር በሰላም ያድርሰኝ ለማለት ዮም ሠረቀ ለነ ወርኀ መስከረም (በመስከረም ወር ከሆነ እየጸለይክ ያለኽው) ቡሩክ ያብጽሐነ እስከ ወርኀ ጥቅምት በሰላመ እግዚአብሔር አብ አሜን ትላለህ።በመቀጠል የእለቱ ሠርቀ መዓልት ሠርቀ ሌሊት እና ሠርቀ ወርኅ አስበህ እንዲህ ትላለህ።መስከረም 1 ላይ ከሆነ እየጸለይክ ያለኽው አሚሩ (፩) ሠርቀ መዓልት። አሡሩ ወአሚሩ (፲፩) ሠርቀ ሌሊት (11ን ያገኘነው አበቅቴ+ሠርቀ መዓልት+ሕጸጽ አድርገን ነው) አሡሩ ወኀሙሱ (፲፭) ሠርቀ ወርኅ።ሠርቀ ወርኅን ያገኘነው ሠርቀ ሌሊት ላይ 4 በመጨመር ነው።ከዚያ እየጸለይክ ያለኽው እሑድ ከሆነ ኀሙሱ ጥንተ ዖን አሚሩ ጥንተ ዕለት ሰዱሱ ጥንተ ቀመር
336 views04:57