ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ — Telegrami kanal

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የሰርጥ አድራሻ: @orthodoxamero
Mitteaktiivne
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 173.79K
የሰርጥ መግለጫ

ዲያቆን ፍፁም ከበደ
ሀሳብ ካሎዎት @Fisumkeb
YouTube
👇👇👇
https://youtu.be/FvQ26dWWEj4?si=TDOpAAm1yXzAdjWR
facebook Link...
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede
TikTok
https://www.tiktok.com/@zdfitsumkebede1?_t=8pguEgtdsVq&_r=1

Kanali statistika
1.4% Kaasatuse määr
2,405 Vaatamisi / postitus
0 Postitusi / päev

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

15 okt 2024
+ የተሳሳቱ የፍቅር ዓይነቶች + PDF.

ዲያቆን ዮሐንስ ጌታቸው "መጽሔተ ወራዙት" በሚል እርዕስ ካዘጋቸው መንፈሳዊ መጽሐፍ የተወሰደ ።


#ኦርቶዶክሳዊ_አእምሮ
5.1K views£itsum, edited  14:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
1 okt 2024
+ በወለደች ትሞታለች +

የእፍኝት (አርዌ ገሞራዊት )ልጆች በእናታቸው ማሕፀን ሲፀነሱ በእናታቸው ምክንያት አባታቸው ተገድሎ ሲሆን እነርሱ ደግሞ ሲወለዱ የእናታቸውን ሆዷን ቀድደው በመብላት ነው ከእናታቸው ማሕጸን የሚወለዱት ። ለዚህም ምክንያታቸው የእናታቸው አፈ ማሕጸኗ ጠባብ በመሆኑ የሚፈጠር ክስተት መሆኑን ሊቃውንት ያስረዳሉ (ምዕላደ ጥበብ ቅጽ ፩) ። በመሆኑም እፍኝትን ልጆቿ የሚበሏት ከውስጥ ከሆዷ ጀምረው ወደ ውጪ ነው ። እንዲህ አድርገው በልተው ሆዷ ሲቀደድላቸው ይወለዳሉ ። የሸረሪት ደግሞ ሲጀመር የሚፀነሱት እንደ ዕንቁላል ባለ ነገር ውስጥ ነው። እንዳንድ ጊዜ በመጨረሻ አካሏ ይዛው ትንቀሳቀሳለች ፣ አንዳንድ ጊዜም አስቀምጣው ስትንቀሳቀስ ትታያለች ።

በመጨረሻም በሚወለዱበት ጊዜ ገስግሰው ሒደው እናታቸውን ይወሩና ይበሏታል ሸረሪት በተፈጥሮ አጥንት የሌላት በመሆኑዋ ምንም ቅሬታ አካል ሳይኖራት ተበልታ ታልቃለች ። ስለዚህ የሸረሪት ልጆች እናታቸውን ሲበሉ ከውጭ ጀምረው ወደ ውስጥ ነው ። እስኪ አሁን ተመልሰን ኢትዮጵያን እናስባትና እንደ እፍኝት ከውስጥ ወደ ውጭ እንደ ሸረሪት ደግሞ ከውጭ ወደ ውስጥ በሁለቱም የአበላል መንገድ አይደለምን ? እየተበላች ያለችው እንዲህም ስተበላ ይህ ዘመን የመጀመሪያዋ አለመሆኑ ከአለፈ ታሪክም መረዳት ይቻላል ። ( ምዕላደ ጥበብ ቁጥር ፪ በመምህር መምህራን በጽሐ ዓለሙ ገጽ 121-122 )


#ኦርቶዶክሳዊ_አእምሮ
3.8K views£itsum, 15:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
23 juuli 2024
Picture 1 from ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ 2024-07-23 17:18:26
ምክር ለሴቶች
830 viewsfikreabe, 14:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
7 mai 2023
የመጽሐፉ ርዕስ፦ አኰቴተ ቍርባን
የመጽሐፉ አዘጋጅ፦ ቀሲስ ዶ/ር መብራቱ ኪሮስ ገብሩ
የመጽሐፉ የገጽ ብዛት፦ 367
የመጽሐፉ ዋጋ፦ 230 ብር
የኅትመት ዘመን፦ 2012 ዓ.ም

የመጽሐፋ ዋና ዓለማ፦
1, የኢትዮጵያዊውን ሥርዓተ ቅዳሴ ውበቱን መግለጽና ጣዕሙን ማስረዳትና
2, ኢትዮጵያዊውን ቅዳሴ ላዘጋጁልን ቀደምት ቅዱሳን አባቶች እውቅና እንድንሰጥ ጥሪ ማቅረብና እውቅና መስጠት ነው።
መጽሐፉ እነዚህን ወርቃማ አላማዎች ይዞ በአራት ታላላቅ ምዕራፎች የተዘጋጀ፥ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ ቅዳሴ መሠረቱን፥ ታሪካዊ እድገቱን እና ይዘቱን የሚያሳይ በመረጃ የዳበረ፥ ጥልቅ ጥናት የተደረገበት ዳጎስ ያለ መጽሐፍ ነው።

ምዕራፍ አንድ፦ ቅዳሴ ምንድነው? በሚል ዐቢይ ርዕስ በመጀመር በአንድ ወቅት (1960ዎቹ) የሩሲያ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ የነበሩት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ አሌክሲ ለአንድ ጋዜጠኛ ቤተክርስቲያናቸውን "ቅዳሴ የምትቀድስ ቤተክርስቲያን" ብለው በገለጹበት ውብ አገላለጽ በመጀመር ቅዳሴ በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ከቃሉ እስከ ይዘቱ እንዴት እንደሚተረጎም፥ እንዲሁም ስያሜው በሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ምን እንደሚመስል በአጭሩ በመግለጽ ይጀምራል። በቀጣይነትም በዚህ ምዕራፍ ውስጥ የቅዳሴ መገለጫ ባሕርያት በሚል ንዑስ ርዕስ አማካኝነት አምስት የሚሆኑ ዋና ዋና የቅዳሴ ባሕርያት ተዳሰውበታል። በተጨማሪም የቅዳሴ ውበት በሚል ርእስ ሥር ቤተክርስቲያን በምድር ያለች ሰማይ መሆኗን፥ በውስጧም የሚከናወነው ሥርዓተ አምልኮም ሰማያዊ መሆኑን በመግለጽ ቅዳሴ በሥጋ፥ በነፍስና በመንፈስ የምንቀደስበት ውብ የሆነ የአምልኮ ሥርዓት ነው በማለት የቅዳሴውን ሰማያዊ ውበት በጥቂቱ ይገልጣል። በመጨረሻም የቅዳሴ መንፈሳዊ ዕሴቶች(ጥቅሞች) በሚል ሰማያዊ ውበት ባለው በቅዳሴው ተሳታፊ በመሆን ስለሚገኘው ጥቅምና ዋጋ፥ እንዲሁም ዘወትር የቅዳሴው ተሳታፊ እየሆንን ነገር ግን ምን መንፈሳዊ ለውጥ ለማይታይብን ደግሞ "ለምን ቅዳሴው አለወጠኝም?" በሚል መነሻ ጥያቄ ሰፊ ማብራሪያ በመስጠት ምዕራፉን በመደምደሚያ አሳብ ይቋጫል።

ምዕራፍ ሁለት፦ የጥንቷ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮ በሚል ዐቢይ ርዕስ በጥንቷ ቤተከርስቲያን የነበረው ሥርዓተ አምልኮና የቁርባን ምሥጋናና ጸሎታት ምን ይመስሉ እንደነበረ በመጠኑ ይዳስሳል። ይሄንንም ለማስረዳት የምሥጢረ ቁርባን አመሠራረት በሚል የጥንቷን ቤተክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮ ለመረዳት የሚያግዙ የአይሁድ ሥርዓተ አምልኮ፥ ወንጌላትና ሐዋርያው ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ሰዎች የላከው መልእክት(ስለ ቅዱስ ቁርባን የተጻፉ ምንባባት)፥ አጋፔ እና ቅዱስ ቁርባን፥ የቅዱስ አግናጥዮስ ዘአንጾክያ መልክታት የሚሉ የጥንቷን ቤተክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮ ለመረዳት የሚያግዙ መንደርደሪያ አሳቦች ተነሥተውበታል። በመቀጠልም የጥንቷ ቤተክርስቲያን ቅዳሴያት በሚል ርዕስ የምዕራፉ ዋና አሳብ ይዘልቅና በአንደኛውና በሁለተኛው ክፍለ ዘመን መጻሕፍተ ሥርዓተ ቤተክርስቲያን ምን እንደሚመስሉና ስለጥንቷ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮ ፍንጭ ይሰጣሉ የተባሉ ከጥንት እስከ አምስተኛው ክፍለ ዘመን የነበሩ መጻሕፍትና ጸሎታት በስፋት ተዳሰውበታል።

ምዕራፍ ሦስት፦ ይህ ምዕራፍ የመጽሐፉ ዋና ክፍል ነው። የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ ቅዳሴ መሠረት እና ታሪካዊ እድገት በሚል ርዕስ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ ቅዳሴ ዕድገቱ ምን እንደሚመስልና ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት የጥንቷን ቤተክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮ መሠረት አድርገው በማስፋፋት ኢትዮጵያዊ መልክ ያለው ሥርዓተ ቅዳሴ እንደሠሩልን ይነግረናል። እንዲሁም የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ ቅዳሴ የዛሬውን መልክ ለመያዝ አራት የዘመናት ሂደቶችን እንዳለፈና እያንዳንዱን የዘመን ለውጥና እድገት በጥቂቱ በመዳሰስ ታሪካዊ እድገቱን ያስቃኘናል። እንዲሁም የግእዝ ሥነ ጽሑፍ ወርቃማ ዘመናት ማለት ከ15 እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ድረስ ባሉ ዘመናት የተነሡ የነገረ መለኮት ክርክሮች ለግእዝ ሥነ ጽሑፍ መስፋፋትና ለሥርዓተ ቅዳሴ እድገት አይተኬ አስተዋጽኦ እንዳበረከተ በተለያዩ ማሳያዎች አስደግፎ ያስቃኘናል። በተጨማሪም በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ቅዳሴ ውስጥ ዓለማቀፍ ተቀባይነትን ባገኙ የቤተክርስቲያን አባቶች ስም የተሰየሙት ቅዳሴያት ስያሜው በተሰየመላቸው አባቶች የተደረሱ ሳይሆኑ የቀደሙት የኢትዮጵያ ቅዱሳን ሊቃውንት ከትሕትናና የድርሰቱን ተቀባይነት ከማጉላት አንጻር በሌሎች አባቶች ስም የተሰየሙ የኢትዮጵያ ሊቃውንት ሥራ መሆኑን የተለያዩ ማሳያዎችን በማስረጃ እያስደገፉ ጥናታዊ በሆነ መንገድ ድምዳሜ ላይ ይደርሳል።
በአጠቃላይ በዚህ ምዕራፍ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮ ዕድገቱ ምን እንደሚመስል ከጥንት እስከ ዛሬ ያለውን ታሪካዊ እድገቱ የተቃኘበትና ቀደምት የኢትዮጵያ ቅዱሳን ሊቃውንት አባቶቻችን የነበራቸውን ዓለማቀፋዊ የቤተክርስቲያን ታሪክና የትምህርተ ሃይማኖት እውቀታቸው ምን ያህል ሰፊ እንደነበረና ያን እውቀታቸውን በመጠቀም ለሥርዓተ አምልኮ እድገት አስተዋጾ በማድረገ ዛሬ የሚገኘውን ውብ ሥርዓተ አምልኮ እንደሠሩልን ያስረዳል።

ምዕራፍ አራት፦ የቅዳሴ አጠቃላይ ይዘት በሚል ርዕስ የሚጀምር የመጽሐፉ የመጨረሻ ምዕራፍ ሲሆን በውስጡም ሦስቱን የቅዳሴ ክፍሎች ማለትም የዝግጅት ክፍል(preparatory service)፥ የትምህርት ክፍል(Lections) እና ፍሬ ቅዳሴ (anaphora) የተሰኙ ክፍሎችና በየክፍሉ የሚገኙ ጸሎታት፥ ዝማሬያት፥ ንባባትና ድርጊቶችን በጥንቷ ቤተክርስቲያን የነበራቸውን ቦታና ሥርዓት እንዲሁም በሌሎች አብያተክርስቲያናት (በኮፕቲክና ሶርያ) ጋር ያለውን ተመሳሳይነትና ልዩነት በማሳየት የጸሎታቱንና የዝማሬያቱን የትመጣነታቸውን በመጠቆምና የኢትዮጵያ ሊቃውንት ለጸሎታቱና ለዝማሬያቱ እንዴት ኢትዮጵያዊ መልክ እንደሰጧቸው በአባቶች መንፈሳዊ ጥበብ በመኩራትና በመደነቅ ከበቂ ማስረጃ ጋር አሰደግፎ ያሳየናል።
በተጨማሪም ቅዱስ ቁርባንን ከመቀበል በፊትና በኋላ ስለሚገኙ ጸሎታትና የጸሎታቱን ምንጮች ከየት እንደሆነ አጭር ዳሰሳ ያቀርባል። በመጨረሻም ስለ ቅድስት ቤተክርስቲያን ሕንጻና በውስጧ ስለሚገኙ ምሳሌያዊና መንፈሳዊ ትርጓሜ ስላላቸው ድርጊቶችና ምልክቶች እንዲሁም በሕንጻው የሚሣሉት ቅዱሳት ሥዕላት ሕንጻ ቤተክርስቲያንን እንዴት በምድር ያለች ሰማይ እንደሚያሰኛት ይነግረንና በቅዳሴው ውስጥ የምናያቸው የሥርዓተ አምልኮ ድርጊቶች የራሳቸው ትርጓሜ እንዳላቸውና ከእነዚህም ውስጥ የተወሰኑ ድርጊቶች በመዳሰስ በእነዚህ ድርጊቶች አማካኝነት በቅዳሴው የሚሳተፉ ምእመናን ሁለተናቸው የቅዳሴው ተሳታፊ በመሆን እንደሚቀደስ ይነግረንና በማጠቃላያ አሳብና መልእክት የምዕራፉና የመጽሐፉ ፍጻሜ ይሆናል።

በአጠቃላይ መጽሐፉ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንን ቅዳሴ ውበቱንና ጣዕሙን፥ የአባቶቻችንን አስተዋጽኦ ከመጠቆም ባሻገር የቤተክርስቲያናችንን ሥርዓተ አምልኮ ታሪካዊ እድገቱ ምን እንደሚመስል ሰፊ ጥናት በማድረግ ለምእመናንና የነገረ መለኮት ደቀመዛሙርት በተለይም Liturgical Theology ውስጥ ላሉት ለተጨማሪ ጥናት በር የሚከፍትና የበለጠ የአባቶቻችን ድካም እንድንረዳና ዋጋ እንድንሰጥ የሚያደርግ በመረጃና በማስረጃ የበለጸገ ግዙፍ ጥናታዊ ሥራ ነው።

ይሄን የመሰለው ድንቅ መጽሐፍ ላበረከቱልን ለመምህራችንና ለአባታችን ለቀሲስ ዶ/ር መብራቱ ኪሮስ እግዚአብሔር ይስጥልን! ከእጅ ቁርጥማት ከደረት ውጋት ይሰውርዎት! ወርቃማ ብዕርዎት ትለምልም!
2.7K views£itsum, 14:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
24 märts 2023
Picture 1 from ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ 2023-03-24 20:13:06
በፍትሐ ነገሥቱ መሠረት አንድ ሰው አራስ ቤት ቢገባ ምን ችግር የለውም። መግባት ይችላል። ያ ብቻ ሳይሆን ለምሳሌ የአንድ ቄስ ሚስት ዛሬ ብትወልድ፣ ቄሱን ደም ካልነካው ነገ ጠዋት ቤተክርስቲያን ገብቶ መቀደስ ይችላል። በግምት የምትናገሩ ሰዎች አደብ ግዙ። ተሳስታችሁ ሌላ ሰው አታሳስቱ። ምእመናንንም ከእንደነዚህ ዓይነት ሰዎች መራቅ አለባቸው። ትክክለኛውን ትምህርት ከተጠያቂ መምህራን እንማር። የማንም መሰለኝ ማራገፊያ አንሁን።

ፍትሐ ነገሥቱን በደንብ ለመማማር እቅድ ይዘን ነበረ። ነገር ግን ኔትዎርክ ስላልተለቀቀ ሁሉም በአንድነት እንዲማር ይቆይ ስላላችሁኝ። ኔትወርክ እስኪለቀቅ ነው እየጠበቅሁ ያለሁት። ሥርዓተ ቤተክርስቲያን ላይ ደካሞች ስለሆንን በደንብ ለማየት ፍትሐ ነገሥቱን በቴሌግራም ቻናሌ በላይቭ እየተጠያየቅን እንማማራለን።

"በትረ ማርያም አበባው " የፍታነገስታ መምሕር።

ይቀጥላል ...
"ወሊድን በተመለከተ" በሚል እርዕስ።

https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

የፌስ ቡክ ገጽ እንድትከታተሉኝ

https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.keb
2.1K views£itsum, edited  17:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
15 veebr 2023
Picture 1 from ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ 2023-02-15 20:28:01
Picture 2 from ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ 2023-02-15 20:28:01
Picture 3 from ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ 2023-02-15 20:28:01
Picture 4 from ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ 2023-02-15 20:28:01
Picture 5 from ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ 2023-02-15 20:28:01
Picture 6 from ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ 2023-02-15 20:28:01
Picture 7 from ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ 2023-02-15 20:28:01
Picture 8 from ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ 2023-02-15 20:28:01
"ሣህል ወርትዕ ተራከባ ጽድቅ ወሰላም ተሰዐማ ፤ ምሕረትና እውነት ተገናኙ ጽድቅና ሰላም ተስማሙ”
መዝሙር ፹፬/፹፭ ፥፲

Gaarummaanii fi amanamummaan wal in argu, qajeelummaa fi nagaan wal in dhungatu.
faarfannaa 85፥10

በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩት በቀድሞ ስማቸው እነ አባ ሳዊሮስ በዛሬው ዕለት በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ተገኝተው የይቅርታ ደብዳቤ አስገቡ ።

https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

የፌስ ቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede
2.1K viewsFitsum, 17:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
17 jaan 2023
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የጥምቀት መዝሙሮችን ይፈልጋሉ ?

ጥር 10 ከተራ፣ ጥር 11 በዓለ ጥምቀት፣ ጥር 12 ቃናዘገሊላ ሁሉንም መዝሙር እዚህ ላይ ያገኛሉ

የጥምቀት መዝሙሮች ስብስብ Over 15 None Stop YeTimket mezmur

"በእደ ዮሐንስ ተጠምቀ" | ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ

ዮሐንስኒ ያጠምቅ - ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን

ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን Mirtnesh

የከተራና የጥምቀት መዝሙሮች ስብስብ 2014E.C

የኛ ነው የኛ - ዘማሪ ዲያቆን እስጢፋኖስ ሳህሌ

ምርጥ እና አዳዲስ የጥምቀት መዝሙሮች ስብስብ 2010 - 2014


ይ ላ ሉን
ይ ላ ሉን
ይ ላ ሉን
113 viewsዲያቆን አቤንዔዘር ሙሉ, 05:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
31 dets 2022
"የክርስቶስ በዓላት 9 ናቸው (አበይት በዓላቱን ማለቱ ነው)፤ የማርያም ግን 33 ናቸው። በምን ያህል እንደሚበልጡ እዩ ወገኖቼ . . ." ይላል አንዱ ፓስተር ዩቲዩብ ላይ። አቤት! ሕዝቡን እንዴት ነው የሚዋሹት?
ሰንበተ ክርስቲያን (የክርስቶስ ትንሣኤ መታሰቢያ በዓል) የማን በዓል ናት? በዓመት ስንት የሰንበት እሁዶች ይከበራሉ? (55) ንዑሳን የጌታ በዓላትስ? በዓመት ስንት በዓለ ወልድ ይከበራል? (12) አማኑኤል? ኢየሱስ?
ውይ! የጌታን በዓላት መቁጠር ጀመርን እንዴ? ወደ እነርሱ ስንፍና አስገቡን! የእመቤታችንን ጨምሮ የቅዱሳን በዓላት ያለ ቅዱስ ቁርባን ይከበራሉ? በፍጹም! ቅዱሳን ሁሉ በራሳቸው በዓላት እንኳ ክብራቸው በመሠዊያው ላይ የሚገለጠው ክርስቶስ መሆኑ ይታወቅ! ክርስቶስ የማይከብርበት የቅዱሳን በዓል የለም! አትዋሹ! ሕዝቡን በድንቁርና እና በውሸት ይዛችሁ መቀጠል የማትችሉበት ጊዜ መጥቷል። የክርስቶስን ቅዱስ ሥጋ እና ክቡር ደም ወደሚቀበልባት፣ ከቅዱሳን ጋር ኅብረት ወደሚፈጥርባት ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሚመለስበትን ጊዜ ብታስረዝሙት እንጂ አታስቀሩትም!
***
"የመንጋዬም ቅሬታ ካባረርኋቸው ምድር ሁሉ ወደ በረታቸው ሰብሰቤ እመልሳቸዋለሁ፤ እነርሱም ያፈራሉ ይበዙማል። የሚጠብቋቸውን እረኞች አስነሣላቸዋለሁ፥ ዳግመኛም አይፈሩምና አይደነግጡም፥ ከእነሱም አንድ አይጐድልም፥ ይላል እግዚአብሔር።" (ኤር. 23÷3-4)

~በረከት አዝመራው~

https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
1.2K viewsሞቱማ ቸርነት, edited  16:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
19 dets 2022
~ኃጢአተኛዋ ሴትና ፈሪሳዊው ስምዖን~

ዘማዊቷ ሴት እግሮቹን ስማ ከእግሮቹ በኅቡዕ ጸጋን ተቀበለች። በጉዞ ከደከሙት እግሮቹ የኃጢአት ሥርየት አገኘች።በነጻ ከሕመሟ የምትድንበትን መድኃኒት ይሰጣት ዘንድ ይህቺ ሴት የአዳኟን በጉዞ የደከሙ እግሮች በነጻ መልካም መዓዛ ባለው ዘይት በመቀባት ዘና አደረገቻቸው።....ርሃቡን ለማስታገስ አልነበረም ጌታችን እንግዳ ሆኖ ከስምዖን ቤት መገኘቱ። ነገር ግን ኃጢአተኞችን ይቅር የሚለው እርሱ ንስሐ ስለምትገባው ስለዚህች ኃጢአተኛ ሴት ሲል ግብዣው ቤት ተገኘ። የፈሪሳዊውን የቅንጦት ማዕድ አልነበረም ጌታችን ራቡ፤የዚያች የኃጢአተኛ ሴት እንባ እንጂ።እርሱ ከተራበው ከእንባዋ ከረካና ከተጽናና በኋላ ነፍሳትን ሊረዳ ወደዚህ ምድር እንደመጣ፣ ሓላፊ የሆነውን ምግብ ሽቶ በእንግድነት ወደ እርሱ እንዳልመጣ ያስገነዝበው ዘንድ ጌታችን ለግብዣ የጠራውን ስምዖንን ወደ መገሰጽ ተመለሰ።

~ኅብረ ወንጌል ዲያቴሳሮን ትርጓሜ በቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ገፅ 132 ከህዳግ ማስታወሻ ~።

~ትርጉም በመ/ር ሽመልስ መርጊያ።~
3.7K views✞£iŧsûm✞, edited  16:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ

Korduma kippuvad küsimused

Levinumad küsimused ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ kohta

ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ on Telegrami kanal, millel on 173.79K tellijat. Sellel lehel saate lugeda viimaseid postitusi, vaadata arvustusi ja üksikasjalikku statistikat.
Klõpsake sellel lehel nuppu „Mine kanalile" või otsige @orthodoxamero Telegrami rakenduses. Samuti saate kanali kasutajanime kopeerida ja Telegrami otsinguribale kleepida.
Jah, ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ on tasuta Telegrami kanal. Saate tellida ja lugeda kõiki postitusi tasuta.
Kanalil ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ on praegu 173.79K tellijat. Tellijate arvu uuendatakse regulaarselt.
ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ avaldab sisu peamiselt አማርኛ keeles. Saate viimaseid sõnumeid sellel lehel eelvaadata.
Jah, sarnaseid ሃይማኖት kanaleid leiate allpool jaotisest „Sarnased kanalid". Näitame ka seotud Telegrami gruppe, botte ja kleebiseid.
Saate sellel lehel kontrollida kasutajate arvustusi ja hinnanguid. Kanali hinnang on 3.7 5-st, mis põhineb 3 arvustusel.
Jah, saate ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ viimaseid sõnumeid eelvaadata siin Telegram Store'is ilma kanalit Telegramis tellimata.
ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ avatar
ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ @orthodoxamero
Ava Telegramis