Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የሰርጥ አድራሻ: @orthodoxamero
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 44.89K
የሰርጥ መግለጫ

ዲያቆን ፍፁም ከበደ
ሀሳብ ካሎዎት @Fisumkeb
facebook Link...
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-05-03 09:22:27 + መጻሕፍት እጅ የሚነሡት መጽሐፍ +

ባለፉት አራት ወራት ውስጥ ሁለት በሰል ያሉ መጻሕፍትን ከመታተማቸው በፊት አንብቤ አስተያየት የመሥጠት አደራ ተጥሎብኝ ነበር:: ከእነዚህ አንደኛው መጽሐፍ የዲያቆን ያረጋል አበጋዝ መድሎተ ጽድቅ ቁጥር ሁለት መጽሐፍ ነበር::

ዲያቆን ያረጋል ለቤተ ክርስቲያን ያደረጋቸውን አስተዋጽኦዎች እጅግ በሳል መጻሕፍቱንና የመምህራን መምህር መሆኑን ለማስተዋወቅ አልደክምም:: በነገረ ቅዱሳን ዙሪያ ከመናፍቃን ክርክር ተላቅቀን ወደ መጽሐፈ መነኮሳትና ዜና አበው ፊታችንን እንድንመልስ ስላደረገችን "ፍኖተ ቅዱሳን" እና "የበረሃ አበው ታሪኮች" : ወደ ነገረ አበው ፊታችንን እንድንመልስ ስላደረጉን "ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሕይወቱና ትምህርቱ" "ቅዱስ አትናቴዎስ ሕይወቱና ትምህርቱ" ስለሚሉ በሳል ሥራዎቹ : የመናፍቃንን ተንኮል የሚያፈራርሱ የዕቅበተ እምነት ሥራዎቹንና በእምነቱ ተከታይ ውስጥም በእውቀት ማነስ የሚያዙ የተሳሳቱ ድምዳሜዎችን የሚያራግፉ መጻሕፍቱና መጣጥፎቹን በጊዜው ራሱን ችሎ ብዙ ሊባልበት የሚችል ነውና ዝርዝሩን እተወዋለሁ::

ዲያቆን ያረጋል መንፈሳዊ መጽሐፍ በጥልቅ ንባብና ምርምር ተደክሞበት በጥንቃቄ ሊሠራ የሚገባው የአቤል መሥዋዕት እንጂ እንደ ቃየን የተገኘውን ግርዶሽ ለቃቅሞ ማሳተም ጥፋት መሆኑን በተግባሩ ብቻ ያሳየ በኦርቶዶክሳዊያን ጸሐፍትና መምህራን ዘንድ የልማድ ፈጣሪነት (trend setting) ሚና ያለው ጸሐፊ ነው:: ለዚህም የእርሱን ተከትለው "ሕይወቱና ትምህርቱ" : በሚል ርእስ የወጡ በርካታ መጻሕፍት ማሳያዎች ናቸው:: ለመናፍቃን መልስ መሥጠት ማለት መሳደብ : የሚሉትን በትክክል እንኩዋን ሳያጤኑ እነሱ ስላሉት ብቻ ሐሰት ነው ማለት አለመሆኑንና ከትምህርቱ ጀርባ ያለውን ዓላማና ታሪካዊ መነሻ መርምሮ ከሥሩ መንቀል መሆኑን መድሎተ ጽድቅ 1 እና ለተሐድሶ ምላሽ የተሠጠባቸው መጻሕፍቱ በሚገባ ያስረዳሉ::

ሁሌም የሚያስደንቀኝ የዲያቆን ያረጋል የትርጉም ጥራት ነው:: በቀደምት አበው የተጻፉ መዛግብትን ሲተረጉም በፍጹም ታማኝነትና በእርግጥም የተባለው አባት ያንን ቃል በትክክል መናገሩን አምነህ እንድታነብ በሚያደርግ እንቅጩነት (exactness) ነው:: አንዳንድ ትርጉሞች የእንግሊዝኛውን ቼክ ማድረግ እንዲያምርህ የሚያደርጉ የተርጉዋሚው ጥላ ያጠላባቸው ሆነው ይገኛሉ:: ወይም ደግሞ በእውነታው ላይ ተመሥርተው የትርጉዋሚውም ማብራሪያ ይበዛባቸዋል:: በዲያቆን ያረጋል ሥራዎች ግን ትርጉሞቹ ከተተረጎመበት Classic English Litrature የሚስተካከሉ መሆናቸው የሚከበሩ ያደርጋቸዋል:: በመድሎተ ጽድቅ ቁጥር 1 ላይ አንድ ቅዱስ ስለመናፍቃን እንከን ፈላጊነት በተመለከተ የተናገረውን በተረጎመበት ቦታ "የቤተ ክርስቲያንን ቁስል እንደ ዝንብ ሕር እያሉ የሚፈልጉ" ብሎ የተረጎመው ትርጉም የትርጉሙን እንቅጩነት ሳስብ ትዝ ያለኝ ምሳሌ ነው:: የዲያቆን ያረጋል ሥራዎችን ለየብቻቸው የሚተነተኑ የትምህርት አሰጣጥና የዕቅበተ እምነት ዘዴያችንን አቅጣጫ ያስያዙ መጻሕፍት ናቸው::
በዲያቆን ያረጋል ደረጃ ያሉ ባለ ብዙ መጻሕፍትና ምርምር ባለቤቶች የሆኑ የቤተክርስቲያን አበውና አኃው እንደሌላው በተራ ምስጋና ብቻ አመስግነናቸው ከማቆም አልፈን ሥራዎቻቸውን በመተንተንና በመወያየት የሚገባውን ሥፍራ መሥጠት ይገባናል:: መጻሕፍት በኪሎ ይመዘኑ ይመስል "ጎሽ ከጻፉ አይቀር እንዲህ ዳጎስ ያለ ነው እንጂ" ብሎ ማወደስ የጸሐፍቱን ልፋት ዋጋ ማሳጣት እንዳይሆን ያሰጋል::

የዲያቆን ያረጋልን መድሎተ ጽድቅ ክፍል 2 ለማንበብ ከተቀበልኩ በኁዋላ ረዥሙን ንባብ ለማድረግ ያሰብኩት የ 17 ሰዓት በሚፈጀው የአውስትራሊያ ጉዞ ላይ ነበር:: መጽሐፉ ግን ይህንን ለማድረግ የሚፈቅድልኝ አልሆነም:: ሰዓቱ ከበቂ በላይ ቢሆንም መጽሐፉ ግን እንደዋዛ እንደ ውኃ እንድጨልጠው አልፈቀደልኝም:: አንዳንድ ትንሽ ገጽ አንብበሃቸው "ሆይ ጉድ!" ማለት የሚፈልጉ መጻሕፍትም አሉ:: ንባብህን ቆም አድርገህ መደሰት : መደነቅ : ማዘን : መሳቅ : መበሳጨት የሚፈልጉ መጻሕፍት አሉ:: መድሎተ ጽድቅ ቁጥር ሁለት እንደዛ ያለች መጽሐፍ ናት:: ታብከነክናለች : አንጀት ታርሳለች : ታስቃለች : እልህ ውስጥ ትከትታለች:: ስለዚህ ከፋፍዬ ለማንበብ ተገደድሁ::

ታስታውሱ እንደሆነ የዲያቆን ያረጋል ቀደምት ጸረ ተሐድሶ መጻሕፍት የመናፍቃኑን ሴራ ማጋለጥ ላይ ያተኮሩ ነበር:: ይኼኛው ግን ከመከላከል ይልቅ ወደ ማጥቃት የተሸጋገረ መጽሐፍ ነው:: ጥቃቱም ጥያቄውን ያነሡ ሰዎችን ጥያቄያቸው ምን እንደነበር እስከማስረሳት የሚደርሱ በጣም የተብላሉ ጽንሰ ሃሳቦችን የሚያስረዳ መጽሐፍ ነው:: አሜን አስብሎ አሳምኖ ከመተውም አልፎ አንዳንዱ የመጽሐፉ ምዕራፍ "በቃ እሺ አመንሁ ተወኝ" የሚልን ሰው እንክዋን “ና ወዴት ትሔዳለህ? ሁለተኛ ይለመድሃል?" የሚል ዓይነት ጥንካሬ ያለው መጽሐፍ ነው::

እውነት ለመናገር በእኔ የንባብ መነጽር ይህ መጽሐፍ ዲያቆን ያረጋል ከጻፋቸው መጻሕፍቱ ሁሉ የሚልቅ የማያዳግም ሥራው (his masterpiece) ነው ለማለት እደፍራለሁ:: ከቀደሙት መጻሕፍቱ የተለየው አዲስ አቀራረብ ልለው የምችለው ደግሞ ማንኛውም አንባቢ ሊያነበው በሚችለው በጣም ማራኪ አጻጻፍ የተዘጋጀ መሆኑ ሲሆን ከያረጋል መጻሕፍት አቀራረብ በተለየ መልኩ በአንዳንድ አመክንዮአዊ ፍሰቱ አዝናኝነትም ያለው መጽሐፍ መሆኑ ነው::

ያልኩት ሁሉ አንዳች ግነት እንደሌለበትና እንዲያውም እንዳነሰ አንባቢ የሆነ ሁሉ አይቶ የሚፈርደው ነው:: ለወገኔ ይጠቅማል በማለት ወይም በከንቱ ውዳሴ የጻፍኩት እንደሌለ አንብባችሁ ትፈርዳላችሁ::

በቤተ ክርስቲያን በዚህ ዘመን የሚታተሙ መጻሕፍትን በሁለት ልንከፍላቸው እንችላለን:: አንደኛው የቤተ ክርስቲያንን ችግር የሚፈታ መጽሐፍ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የጸሐፊውን ችግር የሚፈታ መጽሐፍ ነው::

ጊዚያዊ ችግርን ለመፍታትና ጥቅም ለማግኘት ያም ባይሆን ለስሜ መጠሪያ አንድ ቁና እንክዋን ሳልሰፋ በማለት የሚጻፉ ምንም ችግር የማይፈቱ ተጽፈው ከታተሙ መጻሕፍት ተቀነጫጭበው ያለ ልፋት የተጻፉ ብዙ መጻሕፍት አሉ:: በየደረጃው የሚጠቅሙት ሰው ቢኖርም ተግቶ የሚያነበውን አንባቢ ግን በቃ ምንም የተለየ ነገር የለም ብሎ በማትነጥፈዋ ቤተ ክርስቲያን ላይ ተስፋ እንዲቆርጥ ያደርገዋል::

ዲያቆን ያረጋል ሁሌም ችግር ፈቺ መጻሕፍት ሲጽፍ ኖሮአል:: መድሎተ ጽድቅ ቁጥር ሁለት ግን የተሐድሶ ኑፋቄን ዳግም እንዳይነሣና እንዳያንሠራራ አድርጎ የሚቀብር ሲሆን በዚህ ጉዳይም ድጋሚ መጻፍ እንዳያስፈልግና ሁላችንም ወደ ሌላ ሥራ እንድናተኩር ነጋሪት የመታ "ሠልስት የለም" የሚያሰኝ ቀብር የሆነ መጽሐፍ ነው::

መጽሐፉ 11 አንድ ላይ እንዲታተሙ የሚማጸኑ
ምዕራፎች ያሉት ሲሆን ለአንባብያን እንዳያስቸግር ሲባል ለሁለት ተከፍሎ የመጀመሪያው አምስት መቶ ገጽ ገበያ ላይ ውሎአል:: ሁለተኛው ክፍልም በወር ውስጥ እጃችን ይገባል:: ስለመጽሐፉ በቀጣይ ዳሰሳ ለማቅረብ ቃል የገባሁ ሲሆን ለዛሬ ግን ከነገ በኁዋላ እጃችሁ የሚገባ መሆኑን ለኦርቶዶክሳውያን ሁሉ አብሥሬ አበቃለሁ::

ለወዳጄና ታላቅ ወንድሜ ያረጋል ግን ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ታሪክ መጽሐፍ ምርቃት ላይ ለዶ/ር አክሊሉ የተናገሩትን ቃል ልለው እወድዳለሁ::
1.3K views£itsum, 06:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 09:22:25
1.1K views£itsum, 06:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 19:08:50 ቀኖና ዘኒቅያ (ዘሠለስቱ ምእት)
ኖና ፩:- በሕመም ምክንያት የተሰለበ ወይም ሌሎች በግድ የሰለቡት ሰው በቅቶ ከተገኘ ክህነት ከመሾም አይከልከል። ሳይታመም ወይም ሳያስገድዱት በፈቃዱ ራሱን የሰለበ ሰው ግን ምእመን ቢሆን ክህነት አይሾም። ካህን ቢሆን ከክህነቱ ይሻር።
+
ቀኖና ፪:- አዲስ አማኝን በደንብ ሳይፈትኑት ወደ ክህነት አያምጡት።
+
ቀኖና ፬:- ኤጲስ ቆጶሳትና ሕዝቡ ሁሉ የወደዱት ኤጲስ ቆጶስ ይሾም። በፈቃዳቸው ተሹሟልና ሕዝቡም ይውደዱት። ፫ ኤጲስ ቆጶሳት ይሹሙት።
+
ቀኖና ፭:- ከባድ ምክንያት ሳያጋጥመው ቤተክርስቲያን አልገባም የሚል ካህን ሕዝባዊ ካለ ይገሥጹት። በኤጲስ ቆጶሱ ላይ ክፉ የሚያደርግ ሰው ካለ ይገሥጹት። ኤጲስ ቆጶሱም በቂምና በቁጣ በአንዱ ላይ ክፉ ቢያደርግ ይሻሩት። ኤጲስ ቆጶሳት ወደ ጳጳሳቸው በዓመት ሁለት ጊዜ ይሰብሰቡ።
+
ቀኖና ፮:- ኤጲስ ቆጶስ ያለሕዝቡና ያለጳጳሱ ፈቃድ አይሾም። ከግማሽ በላይ ሕዝብ ከተቃወመው ኤጲስ ቆጶስነትን አይሾም።
+
ቀኖና ፰:- ወደ ትክክለኛዋ ሃይማኖት ካልተመለሱ የከሓድያንን ንስሓቸውን አይቀበሏቸው።
+
ቀኖና ፱:- ሳይመረምሩ የሾሙት ቄስ ቢኖር ከተሾመ በኋላ ቀድሞ የሠራው በደል ቢታወቅ ሹመቱ ተቀባይነት የለውም።
+
ቀኖና ፲፩:- ማንም ሳያስገድደው በፈቃዱ የካደ ሰው ቢኖርና በኋላ ንስሓ ቢገባ ይቀበሉት። ያልተገባው ሆኖ ቢገኝ ግን አይቀበሉት።
+
ቀኖና ፲፪:- ዓለምን ከናቃት በኋላ ወደዓለም የሚመለስ ሰው ቢኖር ቀኖናው 10 ዓመት ይሁን። በተጨማሪም 3 ዓመት ከንኡሰ ክርስቲያን ጋር ይማር።
+
ቀኖና ፲፫:- ለሞት የደረሰ በንስሓ ከምእመናን የተለየ ሰው ቢኖር ሊቆርብ ቢፈልግ ያቁርቡት። ከቆረበ በኋላ ከዳነም ከምእመናን ጋር ይቀላቀል።
+
ቀኖና ፲፬:- ክዶ የተመለሰ ሰው ቢኖር ሦስት ዓመት ከንኡሰ ክርስቲያን ጋር ቆይቶ ወደ ምእመናን ይመለስ።
+
ቀኖና ፲፭:- ቀሳውስት ዲያቆናት የተሾሙባትን ቤተክርስቲያን ትተው ወደ ሌላ ቤተክርስቲያን አይሂዱ። ይህን ያደረጉ ካሉ ሲኖዶስ ያወግዛቸዋል።
+
ቀኖና ፲፮:- ከሌላ ቤተክርስቲያን የመጣን ቄስ ወይም ዲያቆን አይቀበሉት። ወደ ቤተክርስቲያኑ ይመልሱት እንጂ።
+
ቀኖና ፲፯:- አራጣ የሚቀበል ካህን ቢኖር ከሹመቱ ይሻር።
+
ቀኖና ፲፰:- ካህናት ሹመታቸው እንደ ሠራዊተ ብርሃን እንደሆነ ሊረዱ ይገባል። ዲያቆናት ቁርባንን ከቄስ ወይም ከኤጲስ ቆጶስ ይቀበሉ እንጂ በእጃቸው አይቀበሉ። ይህን ሥርዓት ያፈረሰ ቢኖር ከክህነቱ ይሻር።
+
ቀኖና ፲፱:- ከከሓድያን ወደእኛ የተመለሰ ሰው ቢኖር ዳግመኛ ያጥምቁት። የከሓድያን ጥምቀት ከጥምቀት አይቆጠርምና። ከተጠመቀ በኋላ ምግባሩ ያማረ ሆኖ ቢገኝ ክህነት ይሾም። ዲያቆናውያትና መነኮሳይያት ለአገልግሎት ቢለዩም ቁጥራቸው ከሕዝባውያት ነው።
+
ቀኖና ፳:- በሰንበታትና በበዓለ ኃምሳ አይስገዱ።
++++++++++
ይህንን ቀኖና ሠለስቱ ምእት አርዮስን ካወገዙ በኋላ የሠሩት ነው።
+
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
መ/ር በትረማርያም

https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebed
1.6K views£itsum, edited  16:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 12:27:44
#ጠያቂ፦ አንዲት ሴት ጸንሳ ወንድ ልጅ ከወለደች በ40 ቀን ሴት ከወለደች ደግሞ በ80 ቀኗ መጥታ ክርስትና ታስነሣለች። ነገር ግን መንታ (ወንድ እና ሴት) ልጅ ከወለደች እንዴት ነው የምታደርገው??

#መልስ፦ ወንዱ ሕፃን በ40 ቀኑ ይመጣና በሞግዚት ይነሣል። እናቲቱ መግባት ስለማትችል ከውጭ ትቆያች። ክርስትና ተነሥቶ ሥጋ ወደሙ ተቀብሎ የሚወጣ በሞግዚት (በሌላ ሴት እቅፍ) ይሆናል ማለት ነው። ሴቷን ሕፃን ግን በ80 ቀን ይዛ መግባትና ማስነሣት ትችላለች።

#ጠያቂ፦ ምናልባት አንድ ሕፃን ሁለት ጾታ (የወንድም የሴትም ጾታ) ይዞ ቢወለድስ? (ፈናፍንት ቢሆንስ?)

#መልስ፦ ይህ የተፈጥሮ ስጦታ ስለሆነ አክብሮ መቀበል ያስፈልጋል። ሕፃኑ ሽንቱን የሚሸናው በወንድ ብልት ከሆነ በ40 ቀኑ ይነሣል። በሴት የአካል ክፍል (ብልት) የሚሸና ከሆነ ደግሞ በ80 ቀን ማንሣት፣ ማስነሣት ነው።

ይቆየን።
__

Getnet Aytenew


https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebed
1.9K views£itsum, edited  09:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-01 16:25:55
መንፈሳዊ ጉዞ
2.1K views£itsum, edited  13:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-01 16:18:45 ቅዱስ ጳውሎስ ኃጢአታችንን በደሙ ባጠበልን በእርሱ በተሰቀለው በልዑል ክርስቶስ ከአሸናፈዎች እንበልጣለን አለ ። እነርሱ የማይሰሩትን ስራ እኛ እንሰራለን ። ብዙ ታላላቅ ጦር ሜዳ ድል ያደረጉ ጀኔራሎች ( ታላላቅ የጦር ሰዎች ) ልባችንን ማሸነፍ አይችሉም ። ይኸው በቅዱስ ጊዮርጊስ ታውቋል። አንዱን ወጣት የሃይማኖት ገበሬ ቅዱስ ጊዮርጊስን ሰባው ነገስታት ከነሰራዊቶቻቸው ሊያሸንፍት አልቻሉምና ። እርሱ ድል አደረጋቸው እንጂ ፤ በእርሱ ጸሎት ሁሉንም እሳት በላቸው ፣ እርሱ ግን ማንም ድል ሊያደርገው ሊያሸንፈው አልቻለም ። ብዙ መከራ ቢያጸኑበትም ፤ ስጋውን አቃጥለው አመድ አድረገው ቢበትኑበትም ቅሉ ፤ ሃይማኖቱ አስነሳው ። መድኃኔ ዓለም ተገልጦ "ወዳጄ ጊዮርጊስ ሆይ ተነስ " አለው። ቅዱስ ጊዮርጊስ  ድል ያደረገው በወደደው በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል ነው ። ጠላቶቹ ገደልነው ፣ አሸነፍነው ፣ ቆራረጥነው ፣ በተንነው ፣ ጠብስነው ፣ አቃጠልነው ፣ ሲሉ በወደደው በፈጣሪው በኢየሱስ ኃይል ከሙታን ብድግ ይልና ፤ ከጫጉላ ቤት እንደ ወጣ ሰው ታድሶ ፣ ለምልሞ እንደገና ሄዶ ይገጥማቸዋል ። ሶስት ጊዜ ገደሉት ሶስት ጊዜ ተነሳ ፣ በአራተኛው በእግዚአብሔር ፍቃድ ነብሱ ከስጋው ተለየች ። ነገር ግን መጀመርያ አነርሱን አጥፋቶ ነው ፤ እሳት ከሰማይ ወርዶ ጠላቶቹን አጥፍቶ  ሲያበቃ በሰይፍ ተሰየፈ ፤ ከአንገቱም ደም ፣ ውኃ ፣ ወተት ፈሰሰ። (ገድለ ጊዮርጊስ ) ስለዚህ በወደደን በእርሱ በኃያሉ በእግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ከአሸናፈዎች እንበልጣለን ።

ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ በዕብራውያን መልእክቱ (በሃይማኖት የሚሰራ ታላላቅ ስራ) እንዳለ ነግሮናል ። እንግዲህ ምን እላለሁ ? ስለ ጌዴዎን ስለ ባርቅ ስለ ሶምሶን ስለ ዮፍታሔም ስለ ዳዊትና ስለ ሳሙኤልም ስለ ነብያትም እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛል ። እነርሱ በእምነት መንግስታትን ድል ነሱ።" (ዕብ 11:32:33)

       ( ኦርቶዶክስያ ገጽ -94 የመ/ር  ግርማ ከበደ  ትምህርታዊ ስብከቶች ስብስብ )

እንኳን አደረሳቹሁ የሰማእቱ  ምልጃና ጠብቆት አይለየን ።

~ዲያቆን ፍፁም ከበደ~
ሚያዝያ 23 2015 ዓ.ም ኢትዮጵያ

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebed
2.1K views£itsum, edited  13:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-01 16:18:41
1.7K views£itsum, 13:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-01 08:21:51 [ሚያዝያ 23 ዕረፍቱ የኾነው የቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋድሎ በኢትዮጵያ ሊቃውንት]
በመጋቤ ሐዲስ ዶ/ር ሮዳስ ታደሰ
❖ የዚኽም ቅዱስ አባቱ በቀጶዶቅያ መስፍኑ አንስጣስዮስ ሲኾን እናቱ ቴዎብስታ ትባላለች፤ የተወለደውም በልዳ በሶርያ ፍልስጥኤም በ፪፻፹ ዓ.ም. ነው፤ ታናሽ ኾኖ ሳለ አባቱ ዐርፏል፤ ቅዱሳት መጻሕፍትን ፈረስ ግልቢያን ተምሮ ኻያ ዓመት በኾነው ጊዜ ቢሩት ሀገር በመኼድ በዚያ ሀገር ይመለክ የነበረውን መንፈሰ ሰይጣን ያደረበትን የመኰንኑን ልጅ እንዲበላት የተሰጠውን ዘንዶ በክርስቶስ ስም ከገደለው በኋላ እጅ መንሻ ይዞ ወደ ንጉሠ ፋርስ ኼደ፡፡

❖ በዚያ ሀገር ግን ነገሥታቱ ጣዖታትን በማምለክ ክርስቲያኖችን ሲያሳድዷቸው አይቶ ዐዘነ፤ ልቡም በክርስቶስ ፍቅር ነድዶ ወደ ሀገሬ አልመለስም ስለ ክርስቶስ ስም እሞታለኊ አለና “ክርስቲያናዊ አነ ወአአምን በእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ” (እኔ የክርስቲያን ወገን ነኝ እምነቴም በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ነው) በማለት መሰከረ፡፡

❖ ከዚያም ንጉሡ ልብሱን ገፍፈው በዕንጨት ላይ እንዲሰቅሉት፤ ዳግመኛ የዘንባባ እሾኽ የመሳሰሉ ፸ የብረት ችንካሮች ሠርተው በነዚያ እንዲቸነክሩትና ዐጥንቱን ኹሉ እንዲቀጠቅጡት አዘዘ፤ ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን በትዕግሥት በመኾን “እፎ ኢይኄሊ ከመ አምላኪየ ኢየሱስ ክርስቶስ ተሰቅለ ዲበ ዕፀ መስቀል” (ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል እንደተሰቀለ እንዴት አላስብም) አለ፡፡

❖ ዳግመኛም በውስጡ ረዣዥም ችንካሮች ያሉበት የብረት ጫማን ባጫሙት ጊዜ “ሠጠቅዎ ወመተርዎ ዐሥራዊሁ እስከ ውኅዘ ደሙ ዲበ ምድር ከመ ማይ ወሶበ ስዕነ ሠጊረ ድቡተ ሖረ” ይላል ችንካሮቹ ደሙ እንደ ውሃ በምድር ላይ እስኪፈስስ ድረስ እግሩን ዘልቀው ሥሩን በጣጠሱት፤ መኼድም ባልቻለ ጊዜ አጐንብሶ ኼዷል፤ ከዚያም የፈላ የብረት ጋን ውስጥ ከትተው ሰውነቱ በደም እስኪጥለቀለቅ ድረስ ራሱን በመዶሻ ሲመቱት ወደ ጌታችን ጸለየ፤ ያን ጊዜ “ጊዮርጊስ ሆይ ከአንተ ጋር ነኝና ጽና” የሚል ቃል ከሰማይ መጣለት፤ ቅዱስ ሚካኤልም ተገልጾ ከሕመሙ ፈውሶታል፡፡ ይኽነንም ባዩ ጊዜ ብዙዎች በጌታችን አመኑ፡፡

❖ ንጉሡም ይኽነን ባየ ጊዜ እጅግ የሚያስጨንቅ መንኰራኲር ለ፵ ቀን አሠርቶ ለቅዱስ ጊዮርጊስ “እመሰ ትሠውዕ ለአጵሎን ትነሥእ ጌራ መንግሥት ወእመሰ ኊልቊ አንተ ከመ ትትልዎ ለክርስቶስ ነጽር ዘንተ መንኰራኲረ ዘግበርኩ ለከ ከመ እግድፍ በውስቴታ ታማስን ሥጋከ” (ለአጵሎን ብትሠዋ የመንግሥትን ዘውድ ትቀዳጃለኽ፤ ግን ክርስቶስን ለማገልገል የቈረጥኽ ብትኾን ሥጋኽን ትፈጭ ዘንድ በውስጧ ልትጣልባት ያዘጋጀኋትን መንኰራኲር ተመልከት) አለው፤ ይኽ ሲኾን ቅዱስ ጊዮርጊስ ፈጣሪው ክርስቶስን አመሰገነ፡፡

❖ እነርሱም ወደ መንኰራኲሩ በመወርወር ፵ ሰዎች ያዞሩት ዠመር ከዚያም ሰውነቱ ለዐሥር ክፍል ተከፋፈለ፤ እነርሱም ሥጋውን በጒድጓድ ውስጥ ቀበሩት፤ ክብር ይግባውና ጌታችን መላእክትን አስከትሎ በመምጣት እንደገና ከሞት አስነሣውና ባረከው፡፡

❖ ርሱም ከሞት ተነሥቶ እንደገና ወደ ከተማ ገብቶ ስለ ክርስቶስ አምላክነት መሰከረ፤ እነርሱም እጅግ ለመስማት የሚከብዱ መከራዎችን አደረጉበትና ሰውነቱን ጨምቀው አንጀቱን ዘረገፉት፤ ከዚያም ሥጋውን አቃጥለው በዕንጨት ቀፎ በማድረግ ይድራስ ወደተባለ ተራራ ወስደው ዐመዱን በትነውት ተመለሱ፤ ክብር ይግባውና ጌታችን መላእክትን አስከትሎ በመውረድ አራቱን ነፋሳተ ምድር የተበተኑትን የቅዱስ ጊዮርጊስን ሥጋዎች እንዲሰበስቡ አዝዞ እንደገና ከሞት አስነሥቶታል፤ ይኽነንም ባዩ ጊዜ ብዙዎች በክርስቶስ አምነው የሰማዕትነትን አክሊል ተቀዳጅተዋል፡፡

❖ በመጨረሻም ብዙ ተጋድሎዎችን ለሰባት ዓመታት ከፈጸመ በኋላ ንጉሡ የቅዱስ ጊዮርጊስ ራስ በሰይፍ እንዲቈረጥ አዝዞ ወደ መሰየፊያው ቦታ ሲኼድ እሳት ከሰማይ ወርዶ ፸ውን ነገሥታት ያቃጥላቸው ዘንድ መከራውም ከክርስቲያኖች ጸጥ ይል ዘንድ ጸለየ፤ ወዲያውኑም እሳት ከሰማይ ወርዶ ፸ውን ነገሥታት አቃጥሏቸዋል፤ ከዚያም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ብዙ ቃል ኪዳንን ከሰጠው በኋላ በክብር ወደ ሰማይ ወጣ፤ ከዚያም ፊቱን ወደ ምሥራቅ መልሶ ራሱን ዘንበል አድርጎ ሚያዝያ ፳፫ በሰይፍ ቈርጠውት የሰማዕትነትን አክሊል ተቀዳጅቷል፡፡

❖ ከአገልጋዮቹ የቀሩት ሥጋውን ወስደው በንጹሕ ልብስ ጠቅልለው ወደ ሀገሩ ልዳ በመውሰድ ቤተ ክርስቲያን ሠርተው በውስጡ አኖሩት፤ ከርሱም ቊጥር የሌላቸው ብዙዎች ድንቆች ተአምራት ተገልጠዋል፡፡

❖ ሊቁ ቅዱስ ያሬድም፦
"ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወላዕሌነ ይኩን ምሕረት በጸሎተ ጊዮርጊስ ዐቢይ ሰማዕት ወማርያም ወላዲተ አምላክ"
(በሰማያት ለእግዚአብሔር ምስጋና ይኹን፤ አምላክን በወለደች በማርያምና በታላቁ ሰማዕት በጊዮርጊስ ጸሎት በእኛ ላይ ምሕረት ይኹን) ይላል፨

❖ ኢትዮጵያዊዉ ሊቅ አባ ጽጌ ብርሃን በማሕሌተ ጽጌ ድርሰታቸው ላይ፦
“ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ ዘየሐቱ
ዘተጽሕፈ ብኪ ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ
አክሊለ ጽጌ ማርያም ለጊዮርጊስ ቀጸላ መንግሥቱ
አንቲ ኲሎ ታሰግዲ ሎቱ
ወለኪኒ ይሰግድ ውእቱ”

(የስሙና የሞቱ መታሰቢያ ባንቺ የተጻፈብሽ የሚያበራ ከኾነ ዕንቈ ባሕርይ ይልቅ የጠራ ወርቅ ክበብ ያለው የራስ ቊር የተባለ የጊዮርጊስ የመንግሥቱ የራስ ልብስ ጌጥ ሽልማት የአበባ አክሊል ማርያም ሆይ አንቺ ለርሱ ኹሉን ታሰግጅለታለሽ (ታንበረክኪለታለሽ) ርሱ ግን ላንቺ ይሰግዳል) ይሉታል፨

❖ ታላቁ ኢትዮጵያዊ ሊቁ አርከ ሥሉስም የሊቀ ሰማዕታት የቅዱስ ጊዮርጊስን ተጋድሎ፡-
“ሰላም ለከ ሰርዌ ሰማዕታት አእላፍ
ዘሞገሰ ስምከ በጽሐ መንገለ ኲሉ አጽናፍ
በቅድመ ፀሓይ ብሩህ ዘኢየዐርብ ለዘልፍ
ሕማምየ ዝሩ ነሢአከ ወጸዊረከ እስትንፋሰ አፍ
ጊዮርጊስ ቀሊለ ክንፍ ከራድዮን ዖፍ”

(ዘወትር በማይጠልቅ በብሩህ ፀሓይ ፊት በምድር ዳርቻዎች ኹሉ የስምኽ ባለሟልነት የደረሰ የአእላፍ ሰማዕታት አለቃቸው ሰላምታ ለአንተ ይገባል፤ ክንፈ ፈጣን ከራድዮን ዖፍ የተባልኽ ጊዮርጊስ ሆይ የአፍ እስትንፋስን ተቀብለኽና ተሸክመኽ ሕማሜን በትን) እያለ ተማፅኖታል፡፡

❖ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ፦
“ሰላም ለጊዮርጊስ ሰማዕት ዘፀሓየ ጽድቅ
ዘተአምሪሁ ከመ ኆጻ ባሕር
ዘኢይትኌለቊ ኮከበ ክብር
ዘማእከለ ሰማይ ወምድር
ዘአርአየ ኀይለ በዲበ ሰሌዳ መንበር
ብእሲ አዛል ወመስተጋድል
ኀያል ዝሕዙሐ ገድል”፡፡
(ገድሉ የበዛ የተትረፈረፈ ኀያል፤ ተጋዳይ ጐልማሳ (ብርቱ) ሰው፤ በተዘረጋ ዙፋን ላይ ኀይልን ያሳየ፤ በሰማይና በምድር መኻከል ያለ የማይቈጠር የክብር ኮከብ፤ ተአምሩ እንደ ባሕር አሸዋ የበዛ የኾነ፤ የፀሓየ ጽድቅ የኢየሱስ ክርስቶስ ሰማዕት ለኾነ ለጊዮርጊስ ሰላምታ ይገባል) ይለዋል፨

❖ የስብሐተ ፍቁር ዘጊዮርጊስ ደራሲ ኢትዮጵያዊዉ ሊቅ፦
"እምብሩር ወወርቅ ይትበደር ሞገሱ
ለጊዮርጊስ ቅዱስ በዲበ ጸዐዳ ፈረሱ
ለረዲኦትነ ይምጻእ ወያንሶሱ"
(ከወርቅና ከብር ይልቅ ሞገሱ የሚበልጥ ቅዱስ ጊዮርጊስ በነጭ ፈረሱ እኛን ለመርዳት ይምጣ፤ ይመላለስም) ይለዋል፨
[ከመጋቤ ሐዲስ ዶ/ር ሮዳስ ታደሰ] [በድጋሚ ፓስት ያረኩት)
2.6K views£itsum, 05:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 17:22:44 + የአንድ ሰው ውሎና አመሻሽ +

ይህ እስካሁን ምንጩን ያላገኘሁት አንድ ወንድሜ የላከልኝ በፈረንጅ አፍ የተጻፈ የቆየ የአንድ ሰው ገጠመኝ ነው :-

አንድ ወንድም ስልኩን ድምፅ አልባ ማድረግ ረስቶ ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ስብከት ይማራል:: በዚህ መካከል ስልኩ ይጮኃል::

ሰባኪው ስብከቱን አቁሞ በዓይኖቹ ተቆጣው:: ከስብከቱ በኋላ ምእመናን ስብከቱን በመረበሹ ወቀሱት:: አንዳንዶቹም እያዩት ራሳቸውን በትዝብት ነቀነቁ:: ከሚስቱ ጋር ወደ ቤታቸው ሲሔዱም ሚስቱ ስለ ቸልተኝነቱ ምክር መሥጠትዋን ቀጠለች::
እፍረት መሸማቀቅና ውርደት ዘልቆ እንደተሰማው በፊቱ ላይ ይታይ ነበር:: ከዚያች ሰንበት በኋላ እግሩን ወደ ቤተ ክርስቲያን አንሥቶ አያውቅም::

ውስጡ የተረበሸው ይህ ሰው ያንኑ ምሽት ወደ መጠጥ ቤት አመራ:: አእምሮው እንደታወከ ነበር::

ቁጭ ባለበት ድንገት የሚጠጣበት ጠርሙስ ወድቆ ተሰበረና መጠጡም በዙሪያ ተረጨ:: ፍንጣሪው የነካቸው ሰዎች ወደ እሱ መጠጋት ጀመሩ:: ሊጮኹበትና በጥፊ ሊሉት እንደሆነ ታውቆት ቀድሞ ዓይኖቹን ጨፈነ::

ሰዎቹ ግን በተሰበረው ጠርሙስ ስብርባሪ ተጎድቶ እንደሆነ ተጨንቀው ጠየቁት::

አስተናጋጁ መጥቶ የፈሰሰበትን እንዲያደርቅ ማበሻ ሰጠው:: የጽዳት ሠራተኛዋ መሬቱን ወለወለች::

የቤቱ ባለቤት "አይዞህ ያጋጥማል? ዕቃ የማይሰብር ማን አለና?" አለችውና ሌላ መጠጥ አስመጣችለት::
ከዚያች ቀን ጀምሮ ከዚያ መጠጥ ቤት ቀርቶ አያውቅም::

በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ስልክን ክፍት ማድረግና ሥርዓተ አምልኮ መረበሽ መቅደስ ውስጥ ጫማ አድርጎ የመግባት ያህል ስኅተት ነው:: እንኩዋን ቤተ ክርስቲያን ኤምባሲ እንኩዋን ስልክህን ውጪ አስቀምጠህ ትገባለህ:: ሰውዬው ላጠፋው ጥፋት ግን በፍቅር የሚያናግረው ሰው በማጣቱ ከነ ስልኩ ሊጠፋ ወሰነ::

ቤተ ክርስቲያን የድኅነት ሥፍራ ናት:: መጠጥ ቤት ደግሞ የጥፋት ጎዳና ነው:: በዚህ ሰው ታሪክ ውስጥ ግን በድኅነት ሥፍራ ካሉ ሰዎች ይልቅ በጥፋት ሥፍራ ያሉ ሰዎች ለሰውዬው ስኅተት የተሻለ ፍቅር አሳዩ:: አንዳንዴ የአንዳንድ ምእመናን ጠባይ ነፍሳትን ወደ ሲኦል ይሰድዳል::

አንዳችን የአንዳችን ጠባቂ መሆን እንችላለን ዓለምን ለመፈወስ የሚቻለንን እናድርግ:: ነፍሳትን ከማዳን ነፍሳትን ማጥፋት በጣም ቀላል ነው::

መድኃኔዓለም ክርስቶስ የኃጢአተኞች ወዳጅ ነበረ:: እሱ የማንንም ቅስም በክፉ ቃል አልሰበረም:: እኛ ግን ሰው ላይ ስንጨክን መጠን የለንም:: በዚህ ምክንያት እንደ ኒቼ ያሉ ሰዎች "ብቸኛው ክርስቲያን መስቀል ላይ የሞተው ነው" ብለው እስኪዘብቱብን ደርሰዋል::

መጽሐፍ ግን ሰው ሲሳሳት ስናይ ምን ማድረግ እንዳለብን እንዲህ ሲል ይናገራል :-

"ወንድሞች ሆይ፥ ሰው በማናቸውም በደል ስንኳ ቢገኝ፥ መንፈሳውያን የሆናችሁ እናንተ እንደዚህ ያለውን ሰው በየውሃት መንፈስ አቅኑት" ገላ. 6:1

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ Henok Haile
ሐምሌ 26 2014 ዓ.ም.
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ


https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebed
2.5K views£itsum, edited  14:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 20:36:57 .. ከመብረቅ ወይስ ከሊቅ?


(ከማዕበል ፈጠነ)
ሊቀ ጳጳስ ሲሞት ጳጳስ የሚሆን ልጅ ተጸንሶ ያድራል። ንጉሥ ከዙፋን ሲወርድ ንጉሥ ተወልዶ ያድራል። ሊቅ ሲሞት መጻኢው ሊቅ በማሕፀን ተቀርጾ ያድራል ይላሉ አበው በእሳት ዳር ወጋቸው።
"የኔ ሊቀ ሊቃውንት ግን ማን ሲሞት ተወልደው እንዳደሩ አላውቅም። ርሳቸውም ቀለም እንጂ የራቸውን ስዉር ምስጢር ሲናገሩ ሰምቼ አላውቅም።

የኔ ሊቅ ሆይ! ማን ሲያርፍ ተጸነሱ?
ባለ ቅኔው ክፍለ ዮሐንስ?
ያ ፍጹም ባሕታዊ ዮሐንስ ገብላዊ?
ወይስ ጠቢቡ ተዋነይ?
ዶሪ የቅኔው ፈጣሪ ?
ወይስ ግጨው መንክር?
ገብረ ሥላሴ ዘደብረ ኤልያስ? እረ ለመሆኑ በማን እግር ተወለዱ?
ልደትዎ ከሊቅ ወይስ ከመብረቅ?

.. ጊዜው ልጅ እያለሁ ነው። ከቅኔ ቤት ወደ ቅኔ ዘወር ዘወር ስል ድንገት ልቤ ኮበለለ። አውራ እንደ ሌለው ንብ በየደብሩ የተዝረከረኩ የቅኔ ሊቆች ጠቅጥቄ ወደ ትልቁ ሊቅ ወጣሁ። ደጋው ዝናም አዝሏል። የነፋሱ ፉጨት ጆሮ ይጋረፋል። ወደ ሊቀ ሊቃውንት ያሬድ ሽፈራው ቅኔ ቤት ደረስሁ። ጀንበር ጠልቃ ነበር። ወደ ማኅበር ቤቱ ጠጋ ብዬ ቆምሁ። ያ ሁሉ ወፈ ሰማይ ተማሪ ባንዲት ቅጽበት ጸጥ አለ። ወዲያው እንደ ነጎድጓድ የማያዝገመግም ድምፅ ሰማሁ። የደ ቤት ግስ ላይ ደርሰዋል።
አሐደ!
ነደ!
አለደ!
ፈቀደ!
የሚሉ ግሶችን በመብረቃዊ ድምፅ መገሰስ ጀመሩ።
ሊቀ ሊቃውንቱ ነበሩ!!
ድምፃቸው ከነጎጓድ ይቀዳል። ቀለማቱ ኩልልል ብለው በእግራቸው ሲሄዱ አየሁ። ወዲያው ቅኔ ተዘረፈ። ማኅበር ቤቱ ተናወጸ። ጩኽ ጩኽ አለኝ። ውስጤን የፍሥሓ ስሜት ወረረው።
እነሆ የምሽቱ ቅኔ በዚሁ አበቃ። አንድ ተማሪ በእንግዳ ወግ ተቀበለኝ።
በዚች ሌሊት ከሊቀ ሊቃውንት ቤት ታቦት ተሸክሜ ስወጣ አየሁ። ትርጉሙ ከበደኝ። ታቦት ክቡድ ነው። በቃ መሞቴ ነው ስል የልጅነት ሕልሜን ተረጎምሁት። ሕልም እልም ሆነ። እስከ አሁን በሕይወት አለሁ።
ከሊቀ ሊቃውንት ያሬድ ሽፈራው እግር ሥር በዚህ መልኩ በቀልሁ።

ያን ጊዜ ጥሬ ድንጋይ ነበርሁ። ሊቁ ቀደምት ድንጋዮችን በምሥጢር ነበልባል ሲቀቅሉ የጢሱ ወላፈን ነካኝ። አሁን ላይ አያሌ ሊቃውንት በእውቀት እየቀረጹ ይገኛሉ። ጉባኤ ከተከሉበት ጀምሮ እስከ አሁንም ድረስ በዐሥር ሺ የሚቆጠሩ ሊቃውንትን በረቀቀ ቅኔ ወልደው አሳድገዋል። በሥጋም በቀለምም የወለዷቸው ደግሞ በእግራቸው ተተክተዋል።
በቀለምም በልደትም በኩራቸው የቅኔ በኩራችን
መ/ር ቅዱስ ያሬድ እነሆ አለልን!! ስለ እንቆ (ቆ) ባሕርይ ልደት እሱ ቢነግር ደግሞ የረቀቀው ይጎላል። የጎደለው ይሞላል።

በዚህ ቅኔ ቤት ዓመታት ቀርቶ አንዲት ሌሊት ብቻ ያደረ መጻኢ ሕይወቱ የቀለም ቀንድ ይሆናል። ውኃውን የቀመሰ ሕይወቱ ብሩህ ነው። ከዓመት እስከ ዓመት መወድስ የሚፈላበት የሊቀ ሊቃውንት ጥዑም አንደት አሁን ድረስ ይናቀኛል። ገና ዓለም በጨለማ ሳለ ጠቢባንን የወለዱ የሊቀ ሊቃውንት ልዕልና በአደባባይ ይነገር። በቃልም በጽሑፍ ሊቃውንት ይቅደሙ!!

ከሊቅ የተወለደ ሊቅ ሲሆን ከመብረቅ የተወለደ ግን መብረቅ ነው። የኔታ ሆይ! ልደትዎ ከሊቅ ወይስ ከመብረቅ!?

አንባቢያን ሆይ! ስለ የኔታ በፌስ ቡክ ልጽፍ አስብና የትልቁን ሊቅ ክብር እዳፈራለሁ እያልሁ ስፈራ እኖር ነበር። ዛሬ ግን ዝምታዬን ሰብሬአለሁ። እናንተም በገጻቸችሁ የምታውቋቸውን ሊቃውንት ዝክረ ታሪክ ወዲህ በሉ!!


https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebed
2.7K views£itsum, edited  17:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ