Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የሰርጥ አድራሻ: @orthodoxamero
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 44.89K
የሰርጥ መግለጫ

ዲያቆን ፍፁም ከበደ
ሀሳብ ካሎዎት @Fisumkeb
facebook Link...
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-05-12 18:14:58
ምጣድ ላይ ነጭ እንጂ
ጥቁር አይጋገር ፤
ልስበው አልቻልኩም
ይልብኛል እርር ።
ጥሱን መቼ እሆናለሁ
ሰማይ አልማለሁ ፤
ብዙ መሮጥ ብቻ
መሬት እገኛለሁ ።
ፈላጭ ያወላግደኝ
ወይ ጣለኝ ፤
ላልነድ አትጫነኝ ።
ጋጋሪ ቀጠሩ
አይቀመስ ቅጥሩ ፤
እጎቻ እየበላን
ላይፈታ እስሩ ።
እመደር ባልታጣ
የሚለቀም ማገድ
እላይ እየዋኘሁ፡
ከታች ነኝ አመድ ።
እሳት ነው ጩሀቱ
ኩርፍያ በትር ምቱ ።
ጩህ አንተ ኅፃን
አምጪልኝ ፡ አንቀልባ
ውስጧን እየበላት የነገሩ ደባ ።
ጎንበስ ለማገዶ
ስትነጅ ለጎጆ
እያፈመሽ ፍሙ ፤
ፀልመሻል የነበርሽው ቆጆ ።

ዲያቆን ፍፁም ከበደ
ግንቦት 4 2015 ዓ.ም


Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.keb
1.3K views£itsum, edited  15:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 21:50:42 ቤተ ክህነቱ ለምን እንዲህ ቁጣ የተሞላበት መልእክት አስተላለፈ?
***
የኪራይ ቤት ሊቀይሩ ሲሉ ቀድመው የሚቆጡ እና አከራይ ጋር ክፉ የሚናገሩ ተከራዮች አሉ። ሌላ አከራይ ሲያገኙ (ወይም ያገኙ ሲመስላቸው) የቀድሞው አከራይ ጽድቅ ራሱ ኃጢአት ይመስላቸዋል። እንደዚያ . . .
ቤተ ክህነቱ የምዕመናኑን ጥንካሬ ተማምኖ 'ሰውዬው' እያለ መግለጫ ሲሰጥበት ለነበረው ንጉሥ ለመገበር ተዘጋጅቶ ይሆናል። (በቤተ ክርስቲያን ቀኖናዊ ሥርዓትና ጥቅም ላይ ባይሆን ቢገብሩ ምን ቸገረን?) በእነዚህ ጥቂት ቀናት ጀሮ ጭው የሚያደርግ ውሳኔዎችን ሊያሰሙን ይችላሉ። ስለዚህ ቀድሞ አቧራ ማስነሣት እና ጠንካራ ትችት ይሰነዝራሉ ከሚሏቸው ሰዎች ጋር መተናነቅ ፈልገዋል። እስኪ መጨረሻውን እናያለን። በኋላ ለሚሆንባችሁ ነገር ባንስቅ እንኳ ማዘን የምንችል አይመስለኝም። You are trying to tame an advanced Machiavellian politics! It will finally eat you up!
ወዳጄ በቤተ ክርስቲያን ያለው 'High Christology' ብቻ እንዳይመስልህ! 'High Conspiracy' አለ። ሰይጣን ብዙ ጊዜውን የሚያሳልፈው ቤተ ክርስቲያን አካባቢ መሆኑን አትርሳ።
እኛ ግን ከፍ ሲል የእምነታችን ሐዋርያ ክርስቶስን ዝቅ ሲል የጸኑትን ቅዱሳን አባቶች እንከተላለን እንጂ በቤተ ክርስቲያናችን ተስፋ ቆርጠን ወደኋላ አንልም! እንዲያውም ግፍ ያበዛችሁባትን ያህል የበለጠ እንወዳታለን! የበለጠ እናገለግላታለን! መልካም አባቶች ይበዙ ዘንድ የበለጠ እንተጋለን! በሀገር እንደሚሟረተው በቤተ ክርስቲያን ላይ ማሟረት አይቻልም! ቤተ ክርስቲያን ማንም አንደማይነቀንቃት እናውቃለን! ጌታዋ ኃያል ነውና!

(በረከት አዝመራው)


https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.keb
1.9K views£itsum, edited  18:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 21:19:41
(ዲያቆን ሔኖክ ኃይሌ)

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ በጸሎት ተጀምሮአል:: የሁላችንም ጭንቀትና ሃሳብ የቤተ ክርስቲያን ቀጣይ ህልውና ጉዳይ ነው:: በዚህ ዓመት የገጠመንን ጊዜያዊ ችግር ወደ ዘላቂ ችግርነት የሚያሳድግ ውሳኔ እንዳይወሰን የሁላችንም ሥጋት ነው:: በጾመ ነነዌ ከዕንባ እስከ ደም የፈሰሰለትን የቤተ ክርስቲያን ክብር በዘለቄታው የሚያፈርስ መንገድ እንዳይኬድ ቅዱስ ሲኖዶስ በነበረው ጽናት እንደሚታገልና የሚበጀንን እንደሚወስን በጸሎት እንጠብቃለን:: ሹመትን አጥብቆ መፈለግ ለሹመት ብቁ ያለመሆን አንዱ ምልክት መሆኑን የምታስተምር ቤተ ክርስቲያን እንደ ጌታዋ "ታላቅ ሊሆን የሚወድ ቢኖር ታናሽ ይሁን" ብላ ሁሉን መስመር እንደምታስይዝም እንጠብቃለን:: ጊዜው በሀገሪቱ ብዙ እሳት የሚነድድበት ምሕላ የሚያስፈልግበት ፣ ብዙዎች በአስተዳደራዊ ስኅተቶችና ከቤተ ክርስቲያን አስተዳደር የሚጠብቁትን ባለማግኘታቸው ልባቸው ቆስሎ ቤተ ክርስቲያንን ተቀይመው ሃይማኖት የለሽ የሆኑበት ነው:: በመሆኑም ጊዜው ብዙ ነገር የሚስተካከልበት እንጂ የሹመትና ሽልማት ጊዜ አለመሆኑ ከአስተዋይ አባቶቻችን እንደማይሰወር ተስፋ እናደርጋለን:: ከቤተ ክርስቲያን የማይለየው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ከአባቶቻችን ጋር ይሁንልን::


Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.keb
2.3K views£itsum, edited  18:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 17:22:18 ማኅበረ ቅዱሳን ለቅዱስ ፓትርያርኩና ለብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ደብዳቤ አስገባ።

በጻፈው ደብዳቤም ቤተ ክርስቲያን አስቀድማ የጀመረችውን ስልታዊ እቅድ፣ የመዋቅር እና የአስተዳደራዊ ማሻሻያ ሰነዶችን ተመልክቶ ውሳኔ እንዲሰጥ ጠይቋል።

ከማንኛውም ሹመት በፊት የእጩ ኤጲስ ቆጶሳት የምርጫና የመመዘኛ ሥርዓት ሁሉን በአሳተፈ መንገድ ለውይይት ቀርቦ እንዲጸድቅም ሃሳብ ሰጥቷል ።

ቅዱስ ሲኖዶስ ጊዜ የማይሠጡ የቤተ ክርስቲያን ጉዳዮች በጥልቀት ተመልክቶ ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች እንደሚሰጥ ተስፋ አለን ያለው ማኅበሩ በ4 ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ትኩረት ሰጥቶ እንዲወያይ እንደልጅነታችን እንጠይቃለን ብሏል።

1ኛ. ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ቤተ ክርስቲያን የሚያጋጥሟት ፈተናዎች ዋነኛ ምክንያት የቤተ ክህነት አስተዳደር ዘመኑን የዋጀ አለመሆን ነው፡፡ ይህንንም ብፁዓን አባቶቻችን ከፍተኛ የመንግሥት ባላሥልጣናት እና የሚመለከታቸው አካላት ባሉበት ባደረጋችሁት ስምምነት አንቀጽ 8 እና 9 ላይ በግልጽ የተቀመጠ ሲሆን “ለትውልድ አርአያ የሚሆን ቤተ ክህነት እንዲኖር ለማድረግ አሠራራችንን በጥናት አሻሽለን ቤተ ክርስቲያንን ለትውልድ እናሻግራለን፡፡” በማለት ስምምነት ላይ መድረሱ ይታወሳል፡፡ በዚሁ መሠረት ቤተ ክርስቲያን አስቀድማ የጀመረችውን የመሪ እቅድ እና የዘላቂ አስተዳደራዊ መፍትሔ ጥናቶች ውጤት መሠረት የተዘጋጁትን ስልታዊ እቅድ፣ የመዋቅር እና የአስተዳደራዊ ማሻሻያ ሰነዶችን ተመልክቶ ውሳኔ ቢሰጥ፡፡

2ኛ. ቤተ ክርስቲያናችን በ2009 ዓ.ም ኤጲስ ቆጶሳትን ከሾመች በኋላ በልዩ ልዩ ምክንያቶች በተፈጠሩ ክፍተቶች የተነሣ በብፁዓን አባቶች ተደርበው የተያዙ ሀገረ ስብከቶች እንዳሉ ይታወቃል፡፡ ለዚህም ባደረጋችሁት ውይይትና ሰምምነት አንቀጽ 4 ላይ #… በቀጣይ የግንቦት ርክበ ካህናት ተወስኖ እንዲሾም በማለት መስማማታችሁ ይታዋሳል፡፡ በዚሁ መሠረት ተደርበው ለተያዙ ሀገረ ስብከቶች የኤጲስ ቆጶሳትን መሾም አስፈላጊነትን በመወሰን አፈጻጸሙ በቤተ ክርሰቲያን ቀኖና መሠረት በጥንቃቄ ለማከናወን በዐቢይ ኮሚቴው ተጠንቶ የቀረበውን ወቅቱ የሚጠይቀውን የእጩ ኤጲስ ቆጶሳት የምርጫና የመመዘኛ ሥርዓት ላይ ተወያይቶ በማጽደቅ እና ሁሉን አካታች የሆነ ግልጽና ተጠያቂነት ባለው አሠራር የሚመራ አስመራጭ ኮሚቴ በመሰየም፣ የሢመቱ ሂደትም ግልጽ፣ ምእመናንና ካህናት በንቃት ተሳታፊ የሚሆኑበት ለማድረግ በጥንቃቄ እንዲታይና በሚጸድቀው መሥፈርትና ስምምነት መሠረት ሁሉም ኦርቶዶክሳውያን በአባትነት በሙሉ ልባቸው የሚቀበሏቸው ኤጲስ ቆጶሳት ለመሾም የምርጫ ሂደቱ ቢጀምር፡፡

3ኛ. ባለፉት ሁለት ዓመታት በተከሰተው ጦርነት ምክንያት በትግራይ ክልል የሚገኙ ሀገረ ስብከቶች ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጋር ያላቸው አስተዳደራዊ ግንኙነት ተቋርጦ መቆየቱ ይታወቃል፡፡ በዚህ ሁኔታ የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ቢከናወን በቀጣይ የቤተ ክርስቲያን ጎዞ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ያሳድራል፡፡ በመሆኑም ይህ ችግር ተወግዶ የቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ አንድነት እንዲጠናከር ቅዱስ ሲኖዶስ ጉዳዩን በትኩረት ተመልክቶ አስፈላጊውን ውሳኔና አቅጣጫ ቢሰጥ፡፡

4ኛ. ቤተ ክርሰቲያን ያጋጠማትን ወቅታዊ ችግር ምክንያት በማድረግና እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመጠቀም አብያተ ክርሰቲያናትን በኃይል ሰብሮ በመግባት፣ ታሪካዊ ቅርሶችን በመዝረፍና በማውደም፣ ምእመናን ላይ የአካልና የሕይወት ጉዳት በማድረስ ላይ የሚገኙ ሕገወጥ አካላትን መንግሥት ሕግ የማስከበር ኃላፊነቱን እንዲወጣ ቅዱስ ሲኖዶስ ከሚመለከተው አካል ጋር በመነጋገርና በመመካከር የቤተ ክርስቲያን መብትና ሕልውና እንደያስከብር ቢያደርግ፡፡

በመጨረሻም ወደ ፊት ቤተ ክርስቲያን ፈተና እንዳይገጥማት ማድረግ ባትችልም እንኳ ለትውልድ መሻገር የምትችለው የውስጥ አስተዳደራዊ አቅሟን ማሳደግ ስትችል ነው፡፡ ይህንን አስተዳደራዊ ጥንካሬ እና ተቋማዊ ልዕልና መፍጠር የሚቻለው ደግሞ በቤተ ክርስቲያን ሊቃውንትና በየዘርፉ ባሉ ባለሙያዎች የሚቀርቡ ጥናቶችንና ምክረ ሐሳቦችን በበጎ ሕሊናና በሠለጠነ አስተሳሰብ በመቀበል ጥናቶቹ በውይይት እንዲበለጽጉ አድርጎ ለታለመው ዓላማ መጠቀም ሲቻል ነው፡፡
በመሆኑም ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተ ክርስቲያንን ሊቃውንትና የየዘርፉ ባለሙያዎች የሆኑ የቤተ ክርስቲያንን ልጆች በተናጠልና በጋራ በበጎ ፈቃድ የሚያቀርቡትን አስተዳደራዊ ማሻሻያዎች ለቤተ ክርስቲያን ተልእኮ መሳካትና ተቋማዊ ልዕልና ጥቅም ላይ የሚውሉበትን መንገድ አቅጣጫ እንዲሰጥበት እየጠየቅን ማኅበረ ቅዱሳንም ቅዱስ ሲኖዶስ በሚወስነው ውሳኔ መሠረት የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ለመወጣትና በልጅነት ለመታዘዝ ዝግጁ መሆኑን በዚህ አጋጣሚ ለመግለጽ እንወዳለን፡፡
2.3K views£itsum, 14:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 17:22:16
1.7K views£itsum, 14:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 10:30:19
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና መሠረት ከበዓለ ትንሣኤ በኋላ በ፳፭ ተኛው ቀን የሚካሄደው የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት በጸሎት እና በቅዱስነታቸው የመክፈቻ መልዕክት ጉባኤው ተጀምሯል !
2.0K views£itsum, 07:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 20:21:45 ይነበብ !!

ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን ዘመኑን የዋጀ መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት ለመስጠት ያላትን ሁለንተናዊ ዐቅም በእጅጉ ሊያሳልጥ የሚችል ጥናት ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ከመቅረቡ በፊት ሚያዚያ መጨረሻ ላይ ቀርቦ ነበር፡፡ ይህ የስትራቴጂክ (መሪ ዕቅድ) ጥናት በዘርፉ አሉ በሚባሉ ከፍተኛ የምጣኔ ሀብትና የስልታዊ ዐቅድ ባለሞያዎች እንዲሁም በቤ/ክ ሊቃውንት ብዙ ተደክሞበት የተሠራ ነው፡፡

ይህ የተዘጋጀው የመንፈሳዊ ልማት እና የማኅበራዊ ልማት ዕቅድ ይኸንኑ አገልግሎት በሥራ ላይ ለማዋል ከሚያስፈልገው የአደረጃጀት አወቃቀር ጋር የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጁ ብፁዕ አቡነ አብርሃም እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ባሉበት ቀርቦ ነበር፡፡ ሆኖም እነዚህ ብፁዓን አባቶች የቀረበውን የመንፈሳዊና ማኅበራዊ ልማት ዕቅድ ቢያመሰግኑትም የሚተገበርበትን የመዋቅር (አሠራር) ጉዳይ ግን እንደማይቀበሉት ገልጸዋል፡፡ ዕቅድ የሚተገበርበት መንገድ ከሌለ ጥናት ብቻውን ምን ፋይዳ አለው? በዚህ ሁኔታ ጥናቱ ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ የመቅረብ ዕድሉ ሩቅ ሊሆን ይችላል ማለት ነው፡፡

ከዚሁም ጋር የቤተ ክርስቲያን ችግሮችን በየዘርፉ እያጠና ዘላቂ መፍትሔዎች ላይ እንዲሠራ በቅርብ ጊዜ የተቋቋመውና በጣም ብዙ ሥራዎችን እየሠራ ያለው ግብረ ኃይልም በአዎንታ እንደማይታይና ሥራዎቹ የሚተገበሩ የመሆን ዕድላቸው ሩቅ መሆኑን በግልጽ እየሰማን ነው፡፡ ከዚህ የተነሣም አሁን ባለው የቤተ ክህነት አስተዳደር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መዋቅራዊ አሠራር በተለያዩ ውስጣዊና ውጫዊ ምክንያቶች የተነሣ ከገባበት የተወሳሰበ ችግር የመውጣትና ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት የሚፈጽም አካል የመሆን ዕድል እንደማይኖረው ቁርጡን አሳውቀዋል (አሁን ባለው መዋቅር እስካሁን ያልቆረጠላቸው ካሉ ለማለት ነው እንጂ ብዙዎቻችንስ ቁርጣችንን ካወቅን ዘመናት ተቆጥረዋል)፡፡

በዚሁ የዘላቂ መፍትሔ ግብረ ኃይል ሥር ባለ አንድ ክፍል በጥሩ ጥናት ተዘጋጅቶ የቀረበው የኤጲስ ቆጶሳት አመራረጥ ሂደት ረቂቅ መመሪያንም በመልካም እንዳልተቀበሉት ተሰምቷል፡፡ በየዘርፉ ብዙ መሥራት የሚችሉ ልጆች እያሏት ግን ቤተ ክርስቲያኒቱ የእነርሱ ብቻ የግል ድርጅት በምትመስላቸው አካላት ምክንያት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ይህን ሁሉ ከባድ ዋጋ እየከፈለች የምትቀጥለው እስከ መቼ ይሆን? አሁን የቤተ ክርስቲያናችን አስተዳደራዊ መዋቅር ያለበት ሁኔታ የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በ1940ቹና 50ዎቹ የነበረችበትን የተመሰቃቀለ ሁኔታ የሚመስል ነው፡፡

በዚሁም ላይ በአሁኑ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ የኤጲስ ቆጶሳት አመራረጥ ሂደቱ የሚፈጸምበት መመሪያ አስቀድሞ ሳይጽድቅ ወደ ኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ የሚገባ ከሆነ፣ ቤተ ክርስቲያንን እጅግ በጣም ለከፋሰ አደጋ አሳልፈው መስጠታቸው ነው፡፡ በዚያውም ላይ ከሕገ ወጦቹ እናካትታለን የሚባል ከሆነ ደግሞ የቤተ ክርስቲያኒቱን አንድነት ለማፍረስ በሚደረገው ክፉ ሥራ ላይ የስምምነት ፊርማ እንደ ማስቀመጥ ነው፡፡ በአጠቃላይ ያለው ሂደት መቃብሯን እንደ ሙሴ መቃብር መሰወር እንዳይሆን በእጅጉ ያስጨንቃል!

ክርስቶስን ብቻ የተሸከማችሁና እርሱን ብቻ የምታስቀድሙ እውነተኛ ብፁዓን አባቶቻችን ሆይ፤ የአሁኑ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባዔ፣ በእግዚአብሔርም በሕዝብም በታሪክም ፊት የሚያስመሰግንና ተጠቃሽ የሆነ መልካም ሥራ (አለዚያም ደግሞ [አያደድርገውና] የማይሽር ተወቃሽ ጠባሳ ታሪክ) የምትጽፉበት ወቅት ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን እነ ቅዱስ አትናቴዎስን፣ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅን፣ ቅዱስ ዲዮስቆሮስን፣ ቅዱስ ሳዊሮስ ዘንጾኪያን፣ . . . በእጅጉ የምትፈልግበት ወቅት መሆኑ ግልጽ ነው፡፡

ብፁዓን አባቶቻችን ሆይ፣ እኛ ልጆቻችሁ በዚህ ምልዐተ ጉባኤ ቤተ ክርስቲያን በላይዋ ላይ ያንዣበቡባትን ከባባድ ፈተናዎች፣ በጌታ መቃብር ላይ አይሁድ ጭነዋቸው እንደ ነበሩት ድንጋዮች ገለባብጣችሁ የቤተ ክርስቲያን አሠራር ከገባበት ውስብስብ ችግር የሚወጣበትን ትንሣኤ ታሳዩናላችሁ ብለን እንጠብቃለን!

ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ

https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.keb
2.1K views£itsum, edited  17:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 09:22:17 ++‹‹ የሊባኖስ ሙሽራ ››++

በመጀመርያ በክንፍ ላይ ስሎ ለመላእክት ሲገልጣት የጠባቂነት መዓረግን መስጠቱ ነበርና ከማኅፀን ጀምሮ እንዲጠብቃት አደራ በተሰጠው መልአክ በኩል እንደተናገረው በዘመድ በኩል ቢሆንም ቅሉ ለምትወለደዋ ሕፃን ዘመዶቿ የሰማይ መላእክት ነበሩና በእነርሱ ተከባ ወደ ምትወልድበት ስፍራ እንዲሄዱ ተነገራቸው ።

እራሷ ከዓለም አይደለችምና በመወለዷ በቤት ውስጥ የነበሩ ሰዎች ዓለማዊ ተድላ ደስታን እንዳያደርጉ በመንፈሳዊያን ዘመዶቾ በመላእክት ታጅባ ከቤት ወጣች ። ከቤቱ ወጥቶ ሕገ እግዚአብሔርን ስቶ የነበረ አዳምን የሚፈልግ ጌታ እናቱ ናትና ከቤት ወጥታ ቀድሞ አባቶቿ ነብያት እርሷን በራዕይ ወደ ተመለከቱበት ታላቅ ስፍ ወደ ሊባኖስ ተራራ ተጓዘች ። በሊባኖስ ተራራ ጉያ ስር በእንበሶች ጉድጓድ እንደምትወለድ ትንቢት የተነገረላት የሊባኖስ ሙሽራ እርሷ ናትና ።

ከጉሩማኑ አናብስት ከነዳዊት ከነሰሎሞን ፤ ከተላላቁ ተራሮች ከነ አብርሃም ፣ ይስሐቅ ፣ ያዕቆብ አብራክ የተገኘችው እመቤታችን ሰው በማይኖርበት ስፍራ ልትወለድ ተወሰነ። በዚያም ሳሉ ክብሯ ከአድባራት ሁሉ በላይ የሆነ ከቀደሙትም ከኋለኞቹም በላይ ስሟ የገነነ ፣ ከፀሐይ ይልቅ የምትደምቅ እመቤታችን በግንቦት አንድ ቀን ተወለደች ።

እሷ የሁሉ ፍጥረት ናት እንጅ የሐናና የኢያቄብ ብቻ ባለመሆኗ በአንድ ሰው ቤት ውስጥ እንዳትወለድ መንፈስ ቅዱስ ከለከለ ።

( ሕይወተ ማርያም ገጽ 85-87 ሊቀ ሊቃውንት ስምዓ ኮነ መልአክ )

አማላጅነቷ የእናትነት ፍቅሯ ይጠብቀን ።

ዲያቆን ፍፁም ከበደ
ግንቦት 1 2015 ዓ.ም

https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.keb
2.4K views£itsum, edited  06:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 21:48:22 የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል በሀገራችን ኢትዮጵያ ብሔራዊ በዓል ሆኖ ሊከበር እንደሚገባ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ አስታወቁ!

ብፁዕ አቡነ ሔኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል እና የኢቲ አርት ሚዲያ የበላይ ጠባቂ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን የልደት በዓልን በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የመልዕክቱ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል!

"ወሶበ አኮ እግዚአብሔር ጸባኦት ዘአትረፈ ለነ ዘርዐ ከመ ሰዶም እምኮነ ወከመ ገሞራ እመሰልነ ፤ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ፥ እንደ ሰዶም በሆንነ እንደ ገሞራም በመሰልነ ነበር።”
— ኢሳይያስ ፩፥፱

በመላው ዓለም የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልጆች ምዕመናንና ምዕመናት

በባሕርዩ ሞት በመንግስቱ ሽረት የሌለበት ቅዱስ እግዚአብሔር አምላካችን በንጽሕና በቅድስና ያጌጠች ፣ መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ ያልነካት፣ የድኅነታችን ምክንያት ፣ የንጽሕናችን መሠረት ንጽሕት የሠርግ ቤት ለሆነችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ ልደት እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ !

አዳም በኃጢአት ከወደቀ በኋላ ፣ ንስሐ በገባ ጊዜ እግዚአብሔር አምላካችን የድኅነት ቃል ኪዳን ገባለት፡፡
አዳም አምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም የሕይወት ምክንያት የሆነች የልጅ ልጁ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከአብራኩ ከተከፈሉ ቅዱሳን ልጆቹ የምትወለድበትን ቀን ተስፋ እያደረገ ኖረ።

ለድኅነተ ሰብእ ምክንያት የሆነች እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ከቅዱስ ኢያቄም እና ከቅድስት ሐና ነሐሴ ፯ ቀን ተፀንሳ ግንቦት ፩ ቀን ተወልዳለች፡፡
እርስዋም ስትፀነስ ጀምሮ መንፈስ ቅዱስ ከአዳም የውርስ ኃጢአት (ጥንተ አብሶ) ጠብቋት የአዳም አበሳ አልነካትም፡፡ ይህንንም ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ ፈጽሞ በኃጢአት በተከበበ፣ መርገም በሞላበት ዓለም ውስጥ ከኃጢአት ከበደል ተለይታ ንጽህት መሆኗን ሲያስረዳ "የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ እንደ ሰዶም በሆንን እንደ ገሞራም በመሰልን ነበር (ኢሳ ፩፡፱)" በማለት ተናግሯል፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን
ምዕመናንና ምዕመናት

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መዝሙረኛው ዳዊት እንደተናገረ "መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው (መዝ ፹፮ ፥ ፩) እንዳለ ከቤተ መንግስት እና ከቤተ ክህነት የተቀደሱ ተራሮች ከተባሉት ከእሴይ ሥር እና ከአሮን ወገን የተገኘች ናት።

ይህች ዕለት በሊቃውንቱ አንደበት ትልቅ ሕንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀባት ዕለት መሆኗ ይነገራል (ቅዱስ እንድርያስ እንደተናገረ)። ይኸውም የሆነው ከሞት ወደ ሕይወት ከጥፋት ወደ ድኅነት መንገድ ለመጓዝ በበጉ በክርስቶስ ደም ለመታጠብ እና ምድር ከዚህ የጨለማ ሕይወት እንድትወጣ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም መወለድ አስፈላጊ ስለሆነ ነው።

ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም ሐዋርያትና ሐዋርነ አበው እንዳስተማሩን የንጽሕናችን መሠረት ወላዲተ አምላክ እናታችን ከእሴይ ግንድ በትር ይወጣል፥ ከሥሩም ቍጥቋጥ ያፈራል (ኢሳ ፲፩፥፩) ተብሎ ትንቢት የተነገራለትን እመቤት የድንግል ማርያምን በዓለ ልደት በፍፁም ደስታ እና በልዩ ሥነ ሥርዓት ታከብረዋለች።

የእናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መወለድ የነቢያቱ ትንቢት የተፈፀመበት ፣ የብሉይ ኪዳን ማብቂያ የሐዲስ ኪዳን መጀመሪያ ናትና ልደቷ ለሰው ልጆች ሁሉ ታላቅ የደስታ ቀን ነው፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም የቅድስት ድንግል ማርያምን ልደት የምታከብረው ከዚህ ታላቅ በዓል በረከት ረድኤትን እንድናገኝበት ነው፡፡

በመሆኑም በመላው ዓለም የሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን ልጆቻችን በዓሉን በፍፁም ደስታ ካለንበት የትንሣኤ በዓል ጋር ሊያከብሩት እና ልናከብረው ይገባል።

በተለይም ደግሞ በዓሉ እንደ ሀገራችን ኢትዮጵያ ብሔራዊ በዓል ሆኖ የሚከበርበት እና የአበውን ትውፊት በጠበቀ መልኩ እንደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓትም በየአቢያተ ክርስቲያናቱ በልዩ ልዩ ሥነ ሥርዓት ከማክበር በተጨማሪ በማዕከል ደረጃ ለቤተ ክርስቲያንም ሆነ ለሀገር በሚጠቅም መልኩ የሚከበርበት ሁኔታ እንዲመቻች የሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ተነሳሽነት እና የጉዳዩን አስፈላጊነት መረዳት በእጅጉ ያስፈልጋል።

በመጨረሻም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን የልደት በዓል በምናከብርበት ወቅት የሰላም አለቃ የተባለ ክርስቶስን የወለደች (ኢሳ ፱፥፮) እመቤታችን መሆኗን በመረዳት በሀገራችን ኢትዮጵያ የራቀንን ሰላም እና ፍቅር በወንድማማችነት እና በመተሳሰብ መንፈስ ላይ ተመሥርተን ልንመልሰው እና በየአካባቢው የሚታየውን ጭካኔ የተሞላበት የመጠፋፋት አካሄድ ቆም ብለን ልናስብበት እና ወደ ውይይት መመለስ እና ሰላምን ለማጽናት ቁርጠኛ መሆናችንን በማረጋገጥ ሊሆን ይገባል። እንዲሁም ለተራቡ እና ለተቸገሩ ወገኖቻች ቸርነትን በማድረግ ክርስትናችንን በተግባር በመግለጽ ጭምር በዓሉን ማክበር እንደሚገባ እናሳስባለን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
አሜን !

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን እና ሕዝቧን ይባርክ

አባ ሄኖክ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ የተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከልና የኢቲ አርት ሚዲያ የበላይ ጠባቂ

ሚያዝያ ፴ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

#Ethiopia
#Tewahedo_Media_Center
#TMC_Addia_Ababa

ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል
እውነተኛ የተዋሕዶ ድምፅ

https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.keb
2.8K views£itsum, edited  18:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 21:47:58
2.3K views£itsum, 18:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ