Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የሰርጥ አድራሻ: @orthodoxamero
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 44.89K
የሰርጥ መግለጫ

ዲያቆን ፍፁም ከበደ
ሀሳብ ካሎዎት @Fisumkeb
facebook Link...
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-04-21 13:19:57 የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በቴክኖሎጂ በመታገዝ የርቀት እና የኦንላይን ትምህርት ምዝገባ የፊታችን ሰኞ እንደሚጀምር አስታወቀ!!
++++++++++++++++++

(ሚያዝያ 13 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ- ኢትዮጵያ)

የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በሀገር ውስጥ እና በውጪ ሀገራት ለሚገኙ ምዕመናን በቴክኖሎጂ በመታገዝ በርቀት እና በኦንላይን ትምህርት ሊሰጥ ዝግጅቱን አጠናቆ ምዝገባውን የመጪው ሰኞ ሚያዝያ 16 ቀን 2015 ዓ.ም እንደሚጀምር ገልጿል።

ዩኒቨርስቲው በልዩ ልዩ የሥራ መስክ ላይ ተሰማርተው በጊዜ እና በቦታ ርቀት ትምህርት መማር ላልቻሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን በርቀት እና በኦንላይን ትምህርታቸውን እንዲማሩ በማሰብምዝገባውን ሊጀምር መሆኑን ነው የገለጸው።

የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በርቀትና በኦንላይን ትምህርት የሙሉ ጊዜ ሙያዊ ሰራተኞችን
፣ሀገርን በመከላከል ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ወታደሮችን፣በስደት ምክንያት በአንድ ቦታ ነዋሪ መሆን ያልቻሉ ሰዎችና በተለያዩ የሥራ መስክ ላይ የሚገኙ ባለሙያዎችን ያላቸውን ሥራ እና ማኅበራዊ ግንኙነት እንዲሁም የአኗኗር ዘይቤ ሳይቀይሩ ካላቸው እውቀትና ጥበብ በተጨማሪ ከፍተኛ የኦርቶዶክሳዊ ነገረ መለኮት ትምህርት ማግኘት ያስችላልም ነው የተባለው።

በርቀት እና በኦንላይን ትምህርት ዘርፍ የሚሰጣቸው የትምህርት መስኮችም፦

በነገረ መለኮት የትምህርት ዘርፍ በዲግሪ መርሐ ግብር፦

1.የዶግማ ትምህርት
2.የቅዱሳት መጻሕፍት ትምህርት
3.የቤተክርስቲያን ታሪክ ትምህርት
4.የሥርዓተ አምልኮና ትምህርተ ኖሎት
5.ሥነ ምግባርና ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነት

በኢትዮጵያ ጥናት ትምህርት ዘርፍ በዲግሪ መርሐግብር
1.የኢትዮጵያ ታሪክ
2.የግእዝ ቋንቋና ሥነ ጽሑፍ
3.የሥነ ጥበብና ባህል ጥናት በተጨማሪም በዲፕሎማ የነገረ መለኮት ትምህርት እና በሠርተፊኬት የነገረ መለኮት ትምህርት መሆኑ ተገልጿል።

ትምህርቱን ለመማርም ከአጥቢያ ቤተክርስቲያን የአባልነት ማስረጃ፣ከትምህርት ተቋማት የተማሩበት ማስረጃ (መልቀቂያ)እና 4 ጉርድ ፎቶ በመያዝ መመዝገብ እንደሚችል ተገልጿል።

ይህም ተማሪዎች በአነስተኛ ወጪ ትምህርት እንዲያገኙ እና ዩኒቨርስቲው ለትምህርት የሚያወጣውን ከፍተኛ ወጪ በዝቅተኛ ደረጃ እንዲሆን እና የገቢ መጠኑም እንደሚጨምርም ዩንቨርስቲው አሳውቋል።

ለተጨማሪ መረጃ የሀገረ ስብከቱ ማኅበራዊ ድረ-ገጾችን ይጎብኙ:-

1. ድረ-ገጽ:- www.addisababa.eotc.org.et

2. ፌስ ቡክ ገጽ:- አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት/Addis Ababa Diocese

4.ትዊተር :-www.Twitter.com/AddisDiocese

5.መረጃዎችን በክፍሉ መረጃ መቀበያ ሞባይል ቁጥር #09 -09 -84-94-80 በቴሌግራም ይላኩልን፣
1.5K views£itsum, edited  10:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 13:19:46
1.2K views£itsum, 10:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 12:54:13 ምሳሌያት እና የተራዘሙ አመክንዮአዊ ሐተታዎች
***
በክርስትና አስተምህሮ ምሳሌያትን (analogies) እና የተራዘሙ አመክንዮአዊ ሐተታዎችን (speculative reasonings) መጠቀም የትውፊታችን አካል ነው። ነገር ግን አስፈላጊ በሚሆኑባቸው ጊዜያት እንጂ ባገኘነው አጋጣሚ ሁሉ ከተጠቀምናቸው በመገለጥ የተሰጡንን ክቡራን ትምህርቶች አስፈላጊ ወዳልሆነ ማወሳሰብ እና ሰው-ሰራሽ ፍልስፍናዎች እንዳናወርዳቸው ልንጠነቀቅ ይገባል። ምሳሌያት (analogies) እና የተራዘሙ አመክንዮአዊ ሐተታዎች (speculative reasonings) አስፈላጊ የሚሆኑት መቼ ነው?
1. በቅዱሳት መጻሕፍት በቀጥታ ያልተብራሩ ነገሮች ክርክር ሲያስነሡ ለማብራራት (ለምሳሌ የመለኮትና ሰውነትን ተዋሕዶ በጋለ ብረት መመሰል - ክርስቶስን ሁለት አካላት የሚሉ ንስጥሮሳውያን ከመጡት ሁከት ምዕመናንን ለመጠበቅ)
2. በቅዱሳት መጻሕፍት የማያምኑ ሰዎችን ለማሳመን (ቅድስት ሥላሴን በፀሐይ መመሰል - ቀድሞ የግሪክ ፈላስፎችን በኋላም ሙስሊሞችን ለማስረዳት)፣
3. በመንፈሳዊ መራቀቅ ብቻ ልንረዳቸው የምንችላቸውን (mystical) ጉዳዮች በቀላሉ ለመረዳት (በተለይ በሥርዓተ አምልኮ የቅዱሳን መላእክትን ምሥጋና በሿሿቴዎች፣ የእጣኑን መዓዛ በቅዱሳን ጸሎት ወዘተ...)
***
ጠቅለል ሲደረግ ምሳሌያት (analogies) እና የተራዘሙ አመክንዮአዊ ሐተታዎች (speculative reasonings) የታወቁ እና የተወሰኑ ጥቅሞች አሏቸው፤ በዚያ አግባብ መጠቀም ይገባል። ካልሆነ ግን አላግባብ ወደሆኑ መወሳሰቦችና ስህተቶች ይመራሉ። ሲብስም ሰዎች ከቅዱሳት መጻሕፍት ገለል እንዲሉ ሊያደርጉ ይችላሉ። የትምህርታችን ዋና ምስክሮች ግን ነቢያትና ሐዋርያት የጻፏቸው ቅዱሳት መጻሕፍት ናቸው ።


(በረከት አዝመራው)


https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede
1.3K views£itsum, edited  09:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 08:33:34
አዳምን ያሳሳተው እባብ፥ ይኽ በግንዱ ላይ የተጠመጠመው አይደለም።

ሠዓሊዎቹ፥ እባብ ከተረገመ በኋላ ያለውን መልክ ነው እየሣሉ የሚያሳዩን።
  ከመረገሙ በፊት የነበረው መልክ የግመል ቁመና ነበር።
ይኼውም ይታወቅ ዘንድ ግመል ከአንገቱ እስከ አፉ የእባብ መልክ አለው ዛሬም።
 
   "ወይሤኒ ራእዩ እምኵሎን አራዊት ዘገዳም፤መልኩም ከዱር አራዊት ሁሉ ያማረ ነበር" እንዲል ሥነፍጥረት።

ዲያብሎስና የእሱ ማደርያ የሆነው እባብ የቀደመ "መልካቸው" ሳይመለስ፥ አዳም ግን ወደቀደመ ክብሩ ወደቀደመ ቦታውና መዓርጉ ተመልሷል።


(ሊቀ ሊቃውንት ስሙር አላምረው)


https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede
1.7K views£itsum, 05:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 23:40:54 እነዚህን ሰዎች ይራቁ ( ያስወግዱ ) ፤  እውነት ነው የምላችሁ ከዚህ ውሳኔ በዋላ በሕይወታችሁ   ደስተኛ ትሆናላችሁ።   

ልዩ ማስታወሻ

ይሄን  ሃሳብ  ለ16 ሰዎች በምክር መልክ  ሰጥቼ  አሁን  16ቱም  ደስተኛ ናቸው  እናም እናተም ተጠቀሙ  ብሄ  ነው። 

አስታወሱ እግዚአብሔር እንካን ከማይሆኑ ሰዎች ሽሹው  ይላል ሁሌም ቢሆን ውሳኔው የእናንተ ነው

ተፆፋ  በሥነልቦና ባለሞያ Bini Girmachew


የእኔ  ቻናል ነው  በስነልቦና ዙሪያ የተለያዩ ትምህርቶችን ታገኛላችሁ

መልካም ንባብ  ለማንበብ ይጫኑ


https://t.me/+-E61ZVXcb0ExODRk
https://t.me/+-E61ZVXcb0ExODRk
https://t.me/+-E61ZVXcb0ExODRk
1.9K viewsዲያቆን አቤንዔዘር ሙሉ, 20:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 11:10:40 ክርስቲያኖች ምን ይመገቡ ?

ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፲፯
ቀጽ ፳፫ ለክርስቲያኖች ስለሚገቡ ምግቦች፣ ልብሶች፣ ስለ ቤት እና ስለ ተግባረ እድ ይናገራል።
፩) በወንጌል የተከለከሉ ምግቦች ደም፣ ጥሬ ሥጋ፣ ታንቆ የሞተውን፣ ለጣዖት የተሠዋውን፣ የአውሬውን ትራፊ፣ ሙቶ የተገኘውን፣ ሲያርዱ አንገቱን ቆርጠው የጣሉትን ናቸው። ለጣዖት የተሠዋውን አትብሉ የተባለበት ምክንያት ምእመናን ወደ ጣዖት አምልኮ እንዳይሳቡ ነው።
_
፪) ርኵስ ፍጥረት እንደሌለ እግዚአብሔር የፈጠረው ፍጥረት ሁሉ ንጹሕ እንደሆነ ተጽፏል። መጽሐፍ ከከለከለው በቀር ከምግብ ሁሉ እንዳንከለከል መሆን ይገባናል።
_
፫) አእምሮ ወደማጥፋት የሚያደርስን ምግብ፣ አራቱን ባሕርያትን የሚያነዋውጽን ምግብ፣ አካል የሚያጎድልን ምግብ መብላት አይገባም። ይኽውም መርዝ እንዳላቸው እንስሳትና እፀዋት ያሉትን ነው።
_
፬) አትብሉት ከተባለው የምግብ ወገን ደህነኛውን የሚገድል ድውዩን የሚፈውስ ቢሆን ደህነኛው ከመብላት ይከልከል። ድውዩ ግን የሚያድነው ከመሆኑ የተነሣ መብላት ይገባዋል።
_
፭) ሁሉን ሊበሉት እንዲገባ የሚያምን ሰው ሁሉን ይብላ። የሚጠራጠር ሰው ግን እህል ይብላ። ሁሉን የሚበላ አረማዊም ሁሉን የማይበላ አይሁዳዊን ሃይማኖተ ግብዝ ብሎ አይንቀፈው። ሁሉን የማይበላ አይሁዳዊም ሁሉን የሚበላ አረማዊን ይህ ሁሉ በአፌ ብሎ አይንቀፈው።
_
፮) ለሰው ክፉ ነገር እየተጠራጠሩ መብላት ነው። በሃይማኖት የማይሠራው ሥራ ሁሉ ኃጢአት ነው። ለጣዖት የተሠዋውንኳ አምነው ቢበሉት ጉዳት አያመጣም።
_
፯) በመብል ምክንያት ወንድምህ የሚጎዳ ከሆነ የተፈቀደውን እንኳ ስለእርሱ ብለህ አትብላ።
_
፰) በገበያ የሚሸጠውን ሁሉ ብሉ። ፍጥረቱ ሁሉ የእግዚአብሔር ገንዘብ ነውና። እያመሰገኑ ቢቀበሉት ሁሉም በስመ እግዚአብሔር ይከብራል።
_
፱) ካላመኑ ሰዎች ወገን የጠራችሁ ሰው ቢኖር እና ልትሄዱ ብትወዱ ሳትመራመሩ ያቀረቡላችሁን ሁሉ ብሉ። ለጣዖት የተሠዋ ነው ቢላችሁ ግን አትብሉ።
_
፲) በቀለም ያስጌጧቸውን ልብሶች ከመልበስ መጽሐፍ ከለከለ። ቤተመቅደስ ገብተው እግዚአብሔርን ሲያገለግሉ የሚለብሱት ልብስ ነጭ ሊሆን ይገባል።
_
፲፩) ሴቶች የወንድ ልብስ አይልበሱ አለ። እጀ ሰፊ ቀሚስ፣ ሱሪ አይታጠቁ። አርዓያ መለወጥ ሥርዓት ማፍረስ ነውና። ወንዶችም የሴቶችን ልብስ አይልበሱ። ይኽውም እጀ ሰብስብ ቀሚስ አይልበሱ።
_
፲፪) ወንዶች ከጣታቸው ቀለበት አያግቡ የምንዝር ጌጥ ነውና። ሴቶች በወርቅ የተጌጠ የሚያስመካ ልብስ አይልበሱ። ሹማምንት ግን ያጌጠ ልብስ ቢለብሱ ይገባቸዋል።
_
፲፫) መነኮሳት ከፀምር ወገን ደጓሳ ልብስ ይልበሱ።
_
፲፬) ማንኛውም ሕዝብ የወደደውን መልበስ ይገባዋል። ዘመን ያስገኘውን መልበስ ዘመን ባስገኘው ማጌጥ ይገባቸዋል። ከሕዝባውያን ወገን ብዙዎቹ ሰዎች ያገኙትን መልበስ ይገባቸዋል።
_
፲፭) ካህናት የወታደር ልብስ አይልበሱ። ካህናት የአናፂ ልብስን አይልበሱ።
_
፲፮) ወጠቢብኒ ቅዱስ ባስልዮስ ይቤ ይደሉ ለነ ከመ ንሥራዕ ልብሰነ በዘንከድን ዕርቃነነ። ዕርቃናችንን እንሠውር ዘንድ ልብስ መሻት ይገባናል። ወንድኃን እምቍር ወዋዕይ። ከቀን ሐሩር ከሌሊት ቁር ለመዳን ልብስ ያስፈልጋል [ቁጥር ፰፻፲፬]።
_
፲፯) ለሚኖሩበት ሰዎች ይጠቅም ዘንድ፣ ይሠውራቸው ዘንድ፣ ምግባቸውን ንብረታቸውን ያስቀምጡበት ዘንድ፣ ይሰበሰቡበት ዘንድ፣ ቤት መሥራት ይገባል።
_
፲፰) ጌታ ለወልደ እጓለ እመሕያውሰ አልቦቱ ኀበ ያሰምክ ርእሶ ተብሎ እንደተነገረው ቤት እንዳልነበረው ሁሉ ለባሕታውያንም በዚህ አብነት ቤት የላቸውም።
_
፲፱) የእንግዳ መቀበያ ይሆን ዘንድ ቤት ያስፈልጋል።
_
፳) ከሥራይ፣ ከጥንቆላ፣ ጣዖትን ከመሥራት፣ ከመዝፈን፣ ከተውኔት በስተቀር ክርስቲያን ሥራን ሁሉ መሥራት ይገባል።
_
፳፩) አንጥረኛ ሁሉ ጣዖት ከመሥራት ይከልከል። ከአመነ ከተጠመቀ በኋላ ይህን የሚያደርግ ቢኖር ንስሓ ይግባና ይተወው።
_
፳፪) ለጣዖት በገና የሚደረድር፣ የሚዘፍን ቢኖር በቀኖና ይለይ። ያም ባይሆን በውግዘት ይለዩ።
_
፳፫) ለክርስቲያኖች የሚገቡ ሥራዎች ግብርና፣ ማስገር፣ ልብስ መስፋት፣ ልብስ መሥራት፣ ቤት መሥራት፣ ሕክምና፣ አንጥረኝነት፣ ጠራቢነት፣ ጸሓፊነት፣ እንጀራ ጋጋሪነት ወጥ ሠሪነት፣ መምህርነት፣ ነጋዴነት፣ መርከብ መሥራት እና የመሳሰሉት ናቸው። ንግድ ከአንዱ ሀገር ያለውን ወደ አንዱ ሀገር ለመውሰድ በግድ ያለውድ ያሻል [ቁጥት ፰፻፳፬]።
_
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
ክፍል ፲፰ ይቀጥላል
መ/ር በትረማርያም አበባው


https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede
3.7K views£itsum, edited  08:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 06:59:19 ዕለተ አዳም (የአዳም ሐሙስ)
-------------------†-----------------
ክርስቶስ ተንስአ እሙታን ……… በዓቢይ ኃይል ወስልጣን
አሰሮ ለሰይጣን ………….አግአዞ ለአዳም
ሰላም ………………………እም ይእዜሰ
ኮነ………………………………ፍስሐ ወሰላም
••••••••••••••••••• † •••••••••••••••••
ከትንሳኤ በኋላ ያሉ ሰባቱ ዕለታት ስያሜ እንዳላቸው፡ ሰኞ ማዕዶት፣ ማክሰኞ ቶማስ ፣ ረቡዕ ደግሞ አልዓዛር እንደሚባሉ ተመልክተናል።

ነገ ደግሞ አዳም (የአዳም ሐሙስ) በመባል ይታወቃል። በዚህ ዕለት መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ አዳምን ለማዳን መጸነሱ ፣ መወለዱ ፣ መሰቀሉ ፣ መነሳቱና ማረጉ ይነገራል። በዕለቱ ሕጻናቱ "ስለ አዳም" የሚል ባሕላዊ ዜማ እያዜሙ በዓሉን ያዘክራሉ።

አዳም ማለት ትርጉሙ፡-
፩ኛ.  የሰው ሁሉ አባት ፣ የሥጋው ተፈጥሮ ከአፈር ከመሬት ስለሆነ አዳም መባልን ከአዳም ወስዷል፡፡ [ ዘፍ ፪፥፲፤ ፲፱፥፳፯ ]

፪ኛ.  አዳም ማለት እንሰሳዊና መልአካዊ ሁለት ባሕርያት ስላሉት በሥጋው መዋቲ፣ ድኩም፣ ፈራሽ፣ በስባሽ፤ በነፍሱ ነባቢ፣ ልባዊ፣ ሕያው፣ ባለ አእምሮ ይባላል፡፡ [ዘፍ ፪፥፯]

፫ኛ. አዳም በ፮ኛ ቀን መጀመሪያ ከምድር የፈለቀ የሰው ሁሉ ምንጭ ስለሆነ፤ በዘር በሩካቤ ከእርሱ እየተቀዳ ሞትና መቃብር የሚጠጡት ምድራዊ ሰው ሁሉ በእርሱ ስም በምንጩ ስም አዳም አዳሜ ይባላል፡፡ [ዘፍ ፫፥፲፱]

ስለዚህም አዳም የመጀመሪያ ሰውና የሰው ሁሉ አባት ነው፤ በ፮ኛው ቀን የተፈጠረ የሰው ሁሉ ምንጭ ስለሆነ የሰው ዘር ሁሉ ከእርሱ ተገኝቷል፡፡ በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው የተስፋ ቃል ስለመፈጸሙ፤ [ዘፍ. ፫÷፲፭]  አዳም ከነልጆቹ በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ነጻ ስለመውጣቱ ይታሰብበታል፡፡

ክርስቶስ በተነሳበት በአምስተኛው ቀን ሐሙስ  አዳም ይባላል፤ ጌታችን አዳምን ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ  አድንሃለሁ ብሎ  ቃል ገብቶለት  እንደነበር በቀሌምንጦስ ተጽፏል፡፡

አዳምና ሔዋን በገነት ፯ ዓመት ከቆዩ በኋላ ትእዛዙን በመተላለፋቸው ከኤደን ገነት አስወጣቸው [ ኩፋ. ፬፥፲፮ ፤ ዘፍ.፫፥፳፫ ] «ብዙ ተባዙ» ያለው ቃል እንዳይቀር በምድር ላይ ወርደው ልጆችን ወለዱ ይላል፡፡ የተወለዱትም ልጆችም በቁጥር ፷ እንደሆኑ [ ፩መቃ. ፳፰፥፮] የተወለዱት ልጆች ደጎችና ክፉዎች እንደ ነበሩ በአቤልና በቃየል ታውቋል። [ ዘፍ. ፬፥፰]። አዳም በዚህ ዓለም ፱፻፴ {930} ዓመት ኑሮ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በ፵፻፭፻፸ ሚያዚያ ፮ አርፏል፡፡

አባታችን አዳም:- የመጀመሪያው ፍጥረት (በኩረ ፍጥረት) ነው። በኩረ ነቢያት ፣ በኩረ ካኅናት ፣ በኩረ ነገሥትም ነው::

በእርሱ ስሕተት ዓለም ወደ መከራ ቢገባም ወልድን ከዙፋኑ የሳበው የአዳም ንስሃና ፍቅር ነው። አባታችን ለ100 ዓመታት የንስሃ ለቅሶን አልቅሷል። ስለዚህ አባታችን አዳም ቅዱስ ነው። ከሌሎቹ ቅዱሳን ቢበልጥ እንጂ አያንስም።

ለአዳም አባታችን የተናገርነው ሁሉ ደግሞ ለእናታችን ሔዋን ገንዘቧ ነውና አብረን እናስባታለን። እናከብራታለን። አምላከ አዳም ወሔዋን ጸጋ ክብራቸውን ፣ ረድኤት በረከታቸውን ያሳድርብን።

በክርስቶስ በሰማያዊ ሥፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አባት ይባረክ። ዓለም ሳይፈጠር በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን። (ኤፌ. 1:3)

   ወስብሐት ለእግዚአብሔር!


https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede
2.8K views£itsum, edited  03:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 13:07:44
በጥንታዊው የሶደሬ ፈለገ ሰላም መድኃኔዓለም ገዳም ላይ የታጠቁ ኃይሎች የቦንብ ጥቃት እና እገታ ፈፀሙ!

በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ከአዳማ 25 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኘውና በቀዳማዊ አጼ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ፖትርያሪክ የተመሠረተው የሶደሬ ፈለገ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ትናንት ከምሽቱ 3:30- 4:00 ሰዓት ከ50 በላይ የሚሆኑ የታጠቁ ኃይሎች ቤተክርስቲያኑን ሰብረው በመግባት ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል ፡፡

የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የደረሰውን ጉዳት ለማጣራት ልዑካንን የላከ ሲሆን ወደ ቦታው ያቀኑ ልዑካንም ክቡር መልአከ ሳሕል ቀሲስ ነጋሽ ሀብተወልድ የሀገረ ስብከቱ ም/ሥራ አስኪያጅ ፡ ክቡር መጋቤ ጥበባት ቀሲስ ጌቱ ሞቲ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ልዩ ፀሐፊ : ሊቀ ስዮማን ዋሲሁን የሀገረ ስብከቱ የካህናት አስተዳደር ክፍል ኃላፊ ሊቀ ትጉሓን ቀሲስ ፀጋ ተገኝ የሀገረ ስብከቱ ሕዝግ ግንኙነት ፡ ሊቀ ካህናት ቀሲስ ዋካ የአዳማ ዙሪያ ወረዳ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ ሲሆኑ የደረሰው ጉዳት ተመልክተዋል ከልብ ማዘናቸውን በመግለጽ የአካባቢውን ምዕመናን በቃሉ አጽናንተው ተመልሰዋል፡፡

በሩ ጠንካራ በመሆኑ የታጠቁ ኃይሎች ቦንብ በማፈንዳት ሰብረው ለመግባት የቻሉ ሲሆን በቤተክርስቲያኑ ንዋየ ቅድሳት ላይ ከፍተኛ የቃጠሎ ጉዳት ደርሷል ፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የቤተክርስቲያኑን አስተዳዳሪ ቤት ሰብሮ በመግባት በወቅቱ አስተዳዳሪው ባይኖሩም በቤት እቃዎች ላይ ጉዳት አድርሰዋል ፡፡ በካህናት ላይ ከፍተኛ ማዋከብ የተፈጸመ ሲሆን ይኸው የታጠቀ ኃይል የደብሩን ገንዘብ ያዥ የሆኑትን አቶ ተስፋዬን አፍነው መውሰዳቸውንና እስካሁን ሰዓትም የታገተው አቶ ተስፋ እንዳልተለቀቁ ተገልጿል ፡፡

ሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ
3.8K views£itsum, 10:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 19:14:13
"ሰማዕታት የዚህችን ዓለም ጣዕም በእውነት ናቁ ፤ ደማቸውን ስለ እግዚአብሔር አፈሰሱ ፤ ስለ መንግስተ ሰማያት መራራ ሞትን ታገሱ" ውዳሴ ማርያም ዘሐሙስ ቁ፮

ከዓመታት በፊት በአሽብርተኛው አይኤስ ቡድን በሊቢያ ስለሃይማኖታቸው ሰማዕታት የሆኑ ኢትዮጵያውያን ልጆቻችን ሚያዝያ ፲፩ ቀን መታሰቢያቸው ነው።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም ባሳለፈው ውሳኔ መሠረት በሊቢያ ሰማዕትነት የተቀበሉ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም በዚያው ዓመት በወርኃ የካቲት በሃይማኖታቸው ምክንያት የተጨፈጨፉ ግብጻውያን የኮፕቲክ ክርስቲያኖች የ፳፩ ኛው ክፍለ ዘመን ሰማዕታት ተብለው እንዲጠሩ መወሰኑ ይታወሳል።

የሰማዕታቱ በረከት አይለየን !

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን እና ሕዝቧን ይባርክ !


https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede
4.1K views£itsum, 16:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 16:45:57
በእድሜ ትንሹ ትልቅ ሰው በእድሜ ትልቁ ትንሽ ሰው ። ብዙ ዓመት ኖረናል ማለት ብዙ እናውቃለን ማለት አይደለም ትንሽ አመትም ኖረው ብዙ ሚያውቁ ስላሉ ።
ያ ወራጅ ውኃ
ምንድን ያስጮህዋል ።
ለካ እንዲህ ሚያስጮህው
ውስጡ ድንጋይ ኖሯል ።
ለባርጩሜዎቹ (ለትንንሾቹ)
ቦታውን ልቀቁ
አትወረወሩም
በእድሜያቹ መርቁ ።


ያ-ባለ በገና እንዲህ ብሎ ነበር።


(ዲያቆን ፍፁም ከበደ)

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede
3.3K views£itsum, 13:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ