Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የሰርጥ አድራሻ: @orthodoxamero
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 44.89K
የሰርጥ መግለጫ

ዲያቆን ፍፁም ከበደ
ሀሳብ ካሎዎት @Fisumkeb
facebook Link...
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-04-29 20:36:56
2.2K views£itsum, 17:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 11:32:35 #ጌታችን_አርባ_ቀን_ምን_ይሠራ_ነበር?

የጌታችን መዋዕለ ሥጋዌ በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች ይከፈላል፦

1. ቅድመ መስቀል፦ ቅድመ መስቀል የምንለው 33 ዓመት ከ 3ወሩን ነው፤ ይህ ጊዜ ኃጢአት ያልሆነ ማንኛውም ነገር በክርስቶስ የተከናወነበት ልዩ ጊዜ ነው፡፡

2. ድኅረ መስቀል፦ ድኅረ መስቀል የምንለው ደግሞ 40ዎቹን ቀናት ወይም 1 ወር ከ10 ቀናትን ነው፡፡
*(ከዕርገት እስከ ጰራቅሊጦስ ያሉትን 10 ቀናት ለብቻ እናያቸዋለን)*

ጌታችን ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኀላ 40 ቀን በዚህ ምድር ቆይቷል ፡፡ በነዚህ ቀናት ውስጥም በዋናነት 2 ዋና ዋና ሥራዎችን እንደሠራ ሊቃውንት ይናገራሉ፡፡

1. ለሐዋርያት ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን እና መጽሐፈ ኪዳንን ማስተማር፦
ለቅዱሳን ሐዋርያት በጉባኤ የተገለጠላቸው 3 ቀናት ቢሆንም ለእያንዳንዳቸው ለየብቻም 2 ወይም 3 ሆነው ግን ሳይገለጥላቸው የዋለበት ያደረበት ጊዜ አልነበረም፡፡
"ደግሞ አርባ ቀን እየታያቸው ስለ እግዚአብሔርም መንግሥት ነገር እየነገራቸው፥ በብዙ ማስረጃ ከሕማማቱ በኋላ ሕያው ሆኖ ለእነርሱ ራሱን አሳያቸው" እንዲል ሉቃስ ፤ሐዋ 1 : 3፡፡

በተገለጠላቸውም ጊዜ ቤተ ክርስቲያን እንዴትና በምን በማን መተዳደር እንዳለባት አስተምሯቸዋል፡፡ ለምሳሌ ፦
" እርሱም። መረቡን በታንኳይቱ በስተ ቀኝ ጣሉት ታገኙማላችሁ አላቸው። ስለዚህ ጣሉት፤ በዚህም ጊዜ ከዓሣው ብዛት የተነሣ ሊጐትቱት አቃታቸው" ፤ ዮሐ 21 :6 ፤ በማለት ቅዱስ ዮሐንስ እንደጻፈው መረቡ በቀኝ እንዲጣል ማዘዙ የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ሁሉ በቀኝ በክብርና በፍቅር እንደሚፈጸም ያሳያል፡፡ ሐዋርያት እንደ ቃሉ መሠረት ማድረጋቸው ደግሞ ቤተ ክርስቲያን የምትፈጽመው ሥርዓት ሁሉ መሠረቱ የጌታ ቃል እንደሆነ ይህም በማመን የሚፈጸም መሆኑን ያመለክታል፡፡

ዓሣዎቹም በየጊዜው የሚያምኑ የሚጠመቁ ምእመናን ምሳሌዎች ናቸው፤ ቀጥሎ በተዘጋጀው ማእድ በአንድነት መመገባቸውም የሁላችን ማእድ የሚሆነውን ከመላእክት ጋር የምናመሰግነውን የምስጋናችንን አንድነት ያመለክታል፦

" ወደ ምድርም በወጡ ጊዜ ፍምና ዓሣ በላዩ ተቀምጦ እንጀራም አዩ"፤እንዲል ዮሐ 21 : 9፡፡

ይህንም ማእድ መላእክት እንዳዘጋጁት መተርጉማነ ሐዲስ ገልጸዋል፦ ትርጉሙ ኅብረተ መላእክት ወሰብእ ነው፡፡ "ወኅብስተ መላእክቲሁ በልዑ እጓለ እመ ሕያው"( ሰዎች የመላእክትን ምግብ በሉ) የሚለው ትንቢተ ዳዊት የሐዲስ ኪዳን ትርጓሜው በዚህ ፍጻሜውን አግኝቷል፤ መዝ 77፡25፡፡ በዓለም መጨረሻም የሚሆነው ይኸው ነው፤ ከመላእክት ጋር ለዘለዓለም ማመስገን!!!

ከዚህም ቀጥሎ ደግሞ ለጴጥሮስ በጎቹን የመጠበቅ ኃላፊነቱን (ክህነትን) አጠንክሮ አደራ ይለዋል፡፡ ስለዚህ ይህ ሁሉ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ነበር፡፡ ለዚህም መጠበቂያ መመሪያ የሚሆን ጸሎት 7ቱን ኪዳናት አስተምሯቸዋል፡፡

2. ለነፍሳት አህጉራተ ገነትን ማካፈልና ምሥጢረ መንግሥተ ሰማያትን ማሳየት፦

ገነት በ15 አህጉራት እኩል የተከፈለች መሆኗን አበው አስተምረውናል፤ ዓለማችን በሰው ሰራሽ አከፋፈል መሠረት 7 አህጉራት አሏት፤ ገነት ግን የአንዱ አህጉር መጠን ባይታወቅም ቅሉ በ15 አህጉራት የተከፋፈለች ሰፊ መሆኗን ያሳያል፤ ይህች ዓለም የቅጣት ቦታችን ናት (ምድረ ፋይድ) ገነት ግን ጥንተ ርስታችን ናት፡፡ ጌታ በአካለ ነፍስ ወደ ሲኦል ወርዶ ነፍሳትን ካወጣ በኀላ ወደ ገነት አሳልፏቸዋል፤ እርሱ ባወቀም ነፍሳት መኖር በሚገባቸው እያመሰገኑ እንዲኖሩ ቦታ ቦታቸውን አስይዟቸዋል፤ ፍጡር ሆኖ ያለ ቦታ መኖር አይቻልምና፡፡

"በእርሱም ደግሞ ሄዶ በወኅኒ ለነበሩ ነፍሳት ሰበከላቸው" እንዲል ቅ.ጴጥሮስ፤
1ኛ ጴጥ 3 : 19፡፡

ገነት ከገቡ በኀላም ገነት የዘለዓለም መኖሪያቸው እንዳልሆነችና ለዘለዓለም የሚያወርሳቸውን የማታልፈውን የመንግሥተ ሰማያትን ምሥጢር አስተምሯቸዋል፡፡

"ወነበረ አርብዓ መዋዕለ እንዘ ይሜሕሮሙ ምሥጢረ መንግሥተ ሰማያት" እንዲል መቅድመ ወንጌል፡፡
የመንግሥተ ሰማያትን ምሥጢር በዓይነ ሥጋ ማየት፤ በእዝነ ሥጋ መስማት፤ በአእምሮ ጠባዕይ ማወቅ አይቻልም፤ የሚታወቀው በአእምሮ መንፈሳዊ በዓለመ ነፍስ ነውና ለነፍሳት አስተማራቸው፤ ይህም መዓርግ ወይም ደረጃ ነው፤ ምሥጢራትን የምናውቅበት ደረጃ አለ በዓለመ ነፍስ የምንረዳውን በዓለመ ሥጋ አንረዳውም ፦

"ዛሬስ በመስተዋት በድንግዝግዝ እንደምናይ ነን በዚያን ጊዜ ግን ፊት ለፊት እናያለን፤ ዛሬስ ከእውቀት ከፍዬ አውቃለሁ በዚያን ጊዜ ግን እኔ ደግሞ እንደ ታወቅሁ አውቃለሁ፤ እንዳለ ቅ.ጳውሎስ፡፡
1ኛ ቆሮ13 : 12፡፡

ዳግመኛም፦
"ነገር ግን ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀው ተብሎ እንድተጻፈ፥ እንዲህ እንናገራለን"፤ ብሏል፡፡
1ኛ ቆሮ 2 : 9፡፡

እኛም በዚህ በዓለ ሃምሳ ስለ ምሥጢረ ትንሣኤና ስለ ዘለዓለማዊው ሕይወት አብዝተን የምንማርበትና የምንመረምርበት ሊሆን ይገባል፡፡

አምላካችን ምሥጢሩንና ጥበቡን ሁሉ ይግለጥልን!!!

አሜን!
(በድጋሚ የተለጠፈ)

መጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ ከፍያለው



https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebed
2.8K views£itsum, edited  08:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 15:35:12 ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ለንስሓ ልጁ በሰርጓ ቀን መገኘት ባለመቻሉ የላከላት ደብዳቤ
❖❖❖❖
[ አንብቡት ከተማራችሁበት ሳታልፉ ሼር አድርጉት ]

“ልጄ! ለሰርግሽ የነፍስ አባትሽ እኔ ጐርጐርዮስ ይህን ግጥም ስጦታ አድርጌ ልኬልሻለሁ፡፡ አባት ለሚወዳት ልጁ ሊሰጣት የሚችለው የተሻለው ምክርም ይህ እንደ ኾነ አምናለሁ፡፡

“ኦሎምፒያታ ሆይ፥ እውነተኛ ክርስቲያን ለመኾን ያለሽን ፍላጎት ዐውቃለሁና በደንብ አድምጪኝ! እውነተኛ ክርስቲያን እንዲሁ መኾንን የሚመኝ ብቻ ሳይኾን እንደዚያ ለመኾን ሊጥር ይገባዋል፡፡

“ከኹሉም በላይ፥ እግዚአብሔርን ልታከብሪውና ልትወጂው ይገባሻል፡፡ ከእርሱ ቀጥሎም በቅዱስ ወንጌል እንደ ታዘዘው እንደ ጌታችንና መድኃኒታችን [ኢየሱስ ክርስቶስ] አድርገሽ ባልሽን ልታከብሪውና ልትወጂው ይገባሻል፡፡ ስለዚህ እጠይቅሻለሁ! ጌታዋንና ፈጣሪዋን [ኢየሱስ ክርስቶስን] የማታከብርና የማትወድ ሴት በዚህ መንገድ ባልዋን እንዴት አድርጋ ልታከብረውና ልትወደው ትችላለች?

“በጋብቻሽ ውስጥ የትዳር አጋርሽ ይኾን ዘንድ እግዚአብሔር መርጦ ለሰጠሽ ባል ያለሽ መውደድ፣ ስሜትና ፍቅር እጅግ ኃያል ሊኾን ይገባዋል፡፡ ይህ ሰው አሁን የሕይወትሽ ዓይን፣ የልብሽም ደስታ ነውና፡፡

“እግዚአብሔርን እንደምትወጂው፥ ባልሽንም ያለ ቅድመ ኹኔታ ልታከብሪውና ልትወጂው ይገባሻል፡፡ አንቺ ሴት እንደ ኾንሽና ታላቅ የኾነ ዓላማና ግብ እንዳለሽ፥ ኾኖም ዓላማሽና ግብሽ የቤትሽ ራስ ሊኾን ከሚገባው ባልሽ የተለየ እንደ ኾነ ዕወቂ፤ ተረጂም፡፡ ባንቺ ዕድሜ ላይ ያሉት አንዳንዶች ኹለቱም ፆታዎች እኩል [ራስ ናቸው] ብለው የሚሰብኩትን አትስሚ፤ የጋብቻንም ግዴታ [ወይም ዋና ዓላማ] አስቢ፡፡ እነዚህን ግዴታዎች [ወይም ዓላማዎች] ስታውቂ የቤተሰብሽን ተግባራት ለማከናወን እንደ ምን ያለ ትዕግሥትና ጽናት እንደሚያስፈልግሽ ታውቂያለሽና፡፡ እንደ ሚስት እጅግ ጥንካሬን ገንዘብ የምታደርጊውም በዚህ መንገድ ነው፡፡

“ወንዶች እንዴት በቀላሉ የሚቈጡ መኾናቸውን በርግጥ ልታውቂ ይገባሻል፡፡ አይችሉም፤ ብዙ ጊዜም እንደ በረኻ አንበሳ ይኾናሉ፡፡ እንግዲህ ሚስት ጸንታ ልትቆምና የነፍስ ልዕልናዋን ልታሳይ የሚገባት በዚህች ቅጽበት ነው፡፡ አንበሳን የማስለመድ ሥራ መሥራት አለብሽ፡፡ አንበሳን የሚያስለምድ ሰው አንበሳ ሲያገሳ የሚያደርገው ምንድን ነው? ከየትኛውም ጊዜ በላይ ዝም ጸጥ ይላል፡፡ በጸጥታውና በርጋታውም የአንበሳውን ቊጣ ይቈጣጠራል፡፡ በርጋታና በለሆሳስ ኾኖ ያናግረዋል፤ ይደባብሰዋል፤ በቀስታ ያሻሸዋል፤ በጥቂት በጥቂቱም አንበሳው ቊጣውን ይተዋል፡፡

“ባልሽ ስሕተት ሲሠራ በፍጹም ልትነቅፊው፣ ልትንቂው ወይም ልታስነውሪው አይገባም፡፡ በተመሳሳይ መንገድ አንድ መሥራት ያለበትን ነገር ባይሠራና ከዚሁ የተነሣም ውጤቱ ደስ የማያሰኝ ቢኾን፣ ወይም እጅግ የምትፈልጊውና አግባብ ነው ብለሽ የምታስቢውን ባያደርግ እንኳን ባልሽን መናቅ ከአንቺ ልታርቂ ይገባል፡፡ ክፉዎች አጋንንት ዘወትር ቤታችሁን ለማፍረስና የጥንዶች መንፈሳዊ አንድነትን ለመበተን እንደሚሞክሩ ዕወቂ፡፡”

( ከገብረ እግዚአብሔር ኪደ ከትንሿ ቤተክርስቲያን መጽሐፍ የተወሰደ)

https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebed
3.2K views£itsum, edited  12:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 15:35:10
2.7K views£itsum, 12:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 21:01:25 ++‹‹ ሳምራዊቷ ሴት ››++

ውኃን ከዓለት አፍልቆ ያጠጣ ውኃ አጠጪኝ ብሎ ወደ እርሷ ቀረበ በዚህም ውኃን የተጠማ ከሰው እንደ አንዱ አርጋ አየችው ። እርሱም በኋላ ብዙ አሕዛብን እርሱን ወደማመን ምታመጣ ጠፊ ያይደለ መልካም መሬት ብዙ ፍሬን ምትሰጥ መሆኗን ስላወቀ የቃሉን ፍሬ እየዘራ እርሱን አምላክ መሆኑን ወደ ማመን ቀስ እያለ እንድታድግ አደረጋት ። *"ሳምራዊቷን ሴት"* ጌታችን ብቻዋን እንደ ኒቆዲሞስ ነው ያስተማራት (ዮሐ 4-9) ። ዛሬ ዛሬ ሕዝብ ቅጥሩን እስካላጥለቀለቀ ድረስ ያላስተማርን ለሚመስለን አንድም ነብስ ትልቅ ዋጋ እንዳላት ሲያስተምረን ። በእርግጥ ሕይወታቸው ይለያያል *"ኒቆዲሞስ"* የተማረ ምሁረ ኦሪት ስለሆነ በፈሪሳውያን ዘንድ ቦታ ይሰጠው ነበር ። የእርሱ ፍራቻ አዋቂ ተብዬ ስማር ብታይ እናቃለሁ ብሎ ነው ሰው እንዳያየው በማያየው ሰዓት ሌሊት ይማር ነበር ። እርሷ ግን ክብርም የሌላት ከሰው የተገለለች ፍራቻዋም የሰው አፍ እና ፈት የነበረ ሰው በማይኖርበት ሰዓት ውሃን ምትቀዳ የተጠማች ነች ። እርሱ አምላኩን ሰው ሁሉ በሸሸው ሰዓት አምላኩን ከመስቀል አውርዶ መገነዙን ሳስብ ፍቅሩ ልቤን ያባባኛል። እርሷም ሰው እንደራቃት ብቸኝነት እንደጎዳት ሳይ ታሳዝነኛለች ። ኒቆዲሞስ ጌታችን በሚያሳቸው ምልክት ተአምራት ጌታ ከእርሱ ጋር ከሆነ በቀር አንተ የምታደርጋቸውን ተአምራት የሚያደርግ የለም እያለ ነብይ አርጎ አስቦት ነበር ። ሳምራዊታም ሴት እርሷ ብቻ እንጂ ሌሎች ማያውቁትን ሚስጥሯን ሲነግራት ነብይ እንደሆንክ አያለው ብላው ነበር ። ለኦሪት ምሁር አዋቂ ለሆነው ኒቆዲሞስ እርሱን የሚመጥን ትምህርት ሰው ዳግመኛ ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ ወደ እግዚአብሔር መንግስት እንደማይገባ አስተማረው ። ስለ ሚስጢረ ጥምቀት ከመንፈስ ቅዱስ ከማኅፀነ ዮርዳኖስ የተወለደ ወደ ወደ መንግስቱ እንደሚገባ አስተማረው ። ለሳምራዊቷ ሴት ደግሞ በጥምቀት ስለሚሰጠን የልጅ ነት ፀጋ *“እኔ ከምሰጠው ውኃ የሚጠጣ ሁሉ ግን ለዘላለም አይጠማም፥ እኔ የምሰጠው ውኃ በእርሱ ውስጥ ለዘላለም ሕይወት የሚፈልቅ የውኃ ምንጭ ይሆናል እንጂ አላት ። ዮሐንስ 4፥14 ለዘላለም ሕይወት የሚፈልቅ የውኃ ምንጭ ይሆናል ማለቱ ክርስቲያን ለሆነው ሰው የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች በየጊዜው ይጨመሩለታል ሲላት ነው ።ከዚህ ውኃ የሚጠጡ ዳግም አይጠሙም ማለቱም ። ጥምቀት አንድ ጊዜ የምትፈፀም ሰማያዊ መጠጥ በመሆኗ ነው ።

መልአከ ሰላም ዘማሪ እንግዳወርቅ ልብን በሚያረሰርስ ዝማሬያቸው ፦

ምንጭ ስወርድ ገስግሼ ማለዳ
ልቤ ደማ በኅሜቱ ናዳ
ሰዓት ቀየርኩ ውሃ መቅጃዬን
ኩሬ አጠገብ አገኘው ጌታን
ሰው ቢገፍኝ እግዚአብሔር አነሳኝ
ቀን ቢጥለኝ እግዚአብሔር ደገፈኝ
እመካለሁ በእግዚአብሔር
ሰልወደደኝ እሰከ መቃብር


ዲያቆን ፍፁም ከበደ
ሚያዝያ 19 2015 ዓ.ም ኢትዮጵያ


https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede
3.3K views£itsum, edited  18:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 11:26:12 #የሚያዝያ #ድርሳነ #ገብርኤል

አብ ቢወልድ ቢያሠርፅ እንጂ የማይወለድ የማይሠርፅ መሆኑን ዐውቀን ወልድ ቢወለድ እንጂ የማይወልድ የማያሠርፅ መሆኑን ተረድተን መንፈስ ቅዱስም ቢሠርፅ እንጂ የማይወልድ የማያሠርፅ መሆኑን ተገንዝበን የጌቶች ጌታ የነገሥታት ንጉሥ መላእክት የሚያመሰግኑት ስልጣናት ሁሉ የሚገዙለት የቅዱሳንን አማላጅነት ተቀብሎ የልመናቸውን ዋጋ የሚሰጥ አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም በማመን #በሚያዝያ_19 #ቀን #የሚጸለይ የሚነበብ በእግዚአብሔር ፊት የሚቆም #የቅዱስ #ገብርኤል #ድርሳን #ይህ #ነው።

ረድኤቱ ከሁላችን ጋር ለዘለዓለሙ ይኑር አሜን።

ብርሃናዊው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል የጌታን ትንሣኤ ለቅዱሳት አንስት ያበሠራቸው እሱ ነው። አራቱም ወንጌላውያን እንደ ጻፉት ከሳምንቱ በመጀመሪያይቱ ቀን እሑድ ማለዳ በጌታ ህማምና ሞት ልባቸው በሀዘን የጠቆረ እመቤታችን ድንግል ማርያም፣ ማርያም መቅደላዊት እና ሌሎችም ሴቶች መቃብሩን ሊጎበኙ ሥጋውንም ሽቱ ሊቀቡ መጡ።

ያን ጊዜ ብርሃናዊው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል እንደ በረዶ ነጭ የሆነ ልብስ ለብሶ በመቃብሩ አጠገብ ተቀምጦ ታያቸው፤ እነርሱም ባዩት ጊዜ እጅግ ፈሩ። ይህ ቅዱስ መልአክ ፍርሃትን አርቆ ደስታን የሚያጎናጽፍ መልአክ ነውና፥ እነዚህን ቅዱሳት አንስትና እመቤታችንን “እናንተስ አይዟችሁ አትፍሩ የተሰቀለውን ኢየሱስን እንደምትሹ አውቃለሁና እነሆ ተነሥቷል ለደቀ መዛሙርቱ ሂዳችሁ ንገሩ” ብሎ ነገራቸው።

ይህን የደስታ ቃል በሰሙ ጊዜ በፍጹም ደስታ በፍጥነት ሄደው ለደቀ መዛሙርቱ ነገሩአቸው። (ማቴ. 28፥1-8፣ ማር. 16፥1-8፣ ሉቃ. 24፥1-5፣ ዮሐ. 20፥1-18) እንግዲህ ይህ ቅዱስ መልአክ ሀዘንና መከራ የመላውን ልቡና በደስታ የሚመላ በጭንቀትና በፍርሃት ላሉት ሰላምን መረጋጋትን የሚሰጥ የሰላምን የደስታን ዜና ሁልጊዜ ወደሰዎች ይዞ የሚገሰግስ ስለሆነ በጸሎቱ ለተማጸንን በአማላጅነቱ ለተማመን ለፍጹም ሃዘናችን ደስታን ለፍርሃታችን ሰላምን ይስጠን አሜን።

የምሥጢረ ትንሣኤው መልእክተኛ ይሆን ዘንድ እግዚአብሔር በወደደውና በመረጠው በዚህ በመላእክት አለቃ በቅዱስ ገብርኤል ልመና ለኛም ይህን የመሰለ ደስታንና የምስጋና በረከት ለማግኘት ያብቃን።

ጸሎቱ በረከቱ ከሁላችን ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን፤ አሜን።

ምንጭ፦
ትንሿ ድርሳነ ገብርኤል እና መልክአ ገብርኤል በመጋቤ ብሉይ ያሬድ ካሣ፣ 1999ዓ.ም፣ ገጽ 26 – 28


https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede
471 views£itsum, edited  08:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 08:11:49
Facebook Link Follow ያድርጉ
   

https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede

https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede
738 views£itsum, edited  05:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 16:30:17 ከዓመት እስከ ዓመት ግርግር በማያጣትና ሁሌም በሰውና በገበያተኛ በተጨናነቀችው ኢየሩሳሌም ውስጥ እየተጓዝን ነው:: ጥንታዊትዋ የኢየሩሳሌም ከተማ በአሁኑ ሰዓት በአራት ሩቦች ተካፍላ ትተዳደራለች:: የክርስቲያን እርቦ ፣ የሙስሊሞች እርቦ ፣ የአርመኖች እርቦ እና የአይሁድ እርቦ ይባላሉ::

ለሦስቱ አብርሃማውያን እምነቶች (Abrahamic religions) ለአይሁዳዊነት ለክርስትናና ለእስልምና ትልቅ ፋይዳ ባላት ኢየሩሳሌም "አርብ አርብ" ብቻ ሳይሆን ሁሌም ሽብርና ግርግር አለ:: በሁሉም ሩቦች ተሳላሚዎች ፣ ጎብኚዎች ፣ ሻጮች ፣ ገዢዎሽ እስከ እኩለ ሌሊት ይርመሰመሳሉ::

ዘንድሮ እግር ጥሎኝ ከአንድ ወዳጄ ጋር በአይሁድ እርቦ (Jewish quarter) በኩል ሳልፍ አንድ ልብ የሚነካ ሥዕል ዓይኔ ውስጥ ገባ:: ሥዕሉን ሳይ ዕንባ በዓይኔ ሞላ:: የኢሳይያስ 53ቱን የሕማም ሰው ፣ የማይናገረውን በግ በአንገቱ የእሾህ አክሊል ጌጥ አድርገውለት እንዲህ ሆኖ ሳየው ችዬ የማላነበውን ኢሳይያስ 53 በሥዕል ሲያመጣብኝ ከማልቀስ ውጪ ምንም አቅም አልነበረኝም::

ነቢዩ ኢሳይያስ ሳይናገር በፊት የሚቀበለው እንደሌለ አውቆ "የሰማነውን ነገር ማን አምኖአል?" ብሎ የተጨነቀበትን ይህን አስጨናቂ ራእይ እንዴት እንረሳዋለን? ከኢትዮጵያዊው ጃንደረባስ በቀር ኢሳይያስ 53 ን አንብቦ "ማን አምኖአል?" (ሐዋ. 8:26) የእግዚአብሔር ክንዱ የተባለ ክርስቶስስ ለማን ተገልጦአል?

በግርፋቱ ብዛት ፊቱ በደም ተለውሶ "ባየነው ጊዜ እንወደው ዘንድ ደም ግባት የለውም" የተባለበትን ውበቱ ስለ እኛ የጠፋው የሕማም ሰው እንዴት ከሕሊናችን ተሰወረ?

"እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።ተጨነቀ ተሠቃየም በሸላቾቹ ፊት ዝም እንደሚል በግ እንዲሁ አፉን አልከፈተም" የሚለው ቃል ምንኛ ያስጨንቃል? ቆስሎ የሚፈውስ ታምሞ የሚያድን ታስሮ ነፃ የሚያወጣውን የእግዚአብሔር በግ ለመግለፅ ቃላት አቅም ቢያጥራቸው እንዲህ በብሩሽ ኃይል ተሥለው ሳያቸው ሁሉን ነገር ዘነጋሁት::

አንድ ልብሱ በቀለም ያደፈ ሰው በሥዕል ጋለሪው ደጃፍ ቁጭ ብሎ ይፈርማል:: እንደ መታደል ሆኖ ሰውዬው የሥዕሉ ባለቤት UDI MERIOZ ነበረ:: ቀርቤ ስለ ሥዕሉ የተሰማኝን ስነግረው እሱም ስሜቱ ተነካ:: "ይሄንን ሥዕል እኔ ብሥለውም የእኔ ፈጠራ አይደለም:: ሸራውን ወጥሬ በቀለም ላይ የሠራሁት እኔ ነኝ:: ነገር ግን ከመሣሌ በፊት በተደጋጋሚ በሕልሜ አየው ነበር:: የሣልሁትም ያየሁትን ነው" አለኝ:: ሥዕሉንም ፈርሞ ለእኔና ለወዳጄ ሠጠን::

ቅዱስ ኤፍሬም "ጌታ ሆይ ረዥሙን ሥቃይህን ማን ሊገልጸው ይችላል?" እንዳለው የጌታን መከራ የሚገልፅ አንደበት የሚሥለው ብሩሽ ባይኖርም ለአፍታ ግን እንዲህ በየሰዉ ላይ ባሳረፈው ጸጋ ሕማሙን ያስታውሰናል::

ይህ የበገና መዝሙር ግጥም ግን ከሕሊናዬ መጣ

"ያ ሁሉ መከራ እንዴት ይግባ ልቤ
አልበጠስ አለኝ የኃጢአት መረቤ

ተው ልቤን ስበረው ልመንህ አጥብቄ
መቼ ሕይወት ሆነኝ ቃልህን ማወቄ
ቃሉን ተናጋሪ ምግባር የሌለኝ
ተገርፎአል ተሰቅሎአል የምል ብቻ ሆንኩኝ" (ዘማሪት አዳነች አስፋው)


(ዲያቆን ሔኖክ ኃይሌ)


ttps://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede
1.8K views£itsum, edited  13:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 16:30:07
1.5K views£itsum, 13:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 07:41:32 ሩካቤ ሥጋ የማይፈጸምባቸው_ጊዜያት

ሩካቤ ሥጋ፣ በምን ዓይነት ሥርዓት ሊፈጸም እንደሚገባው በሕገ ቤተ ክርስቲያን እንዲህ ተደንግጓል፤ እግዚአብሔር ሩካቤን ለሰው የሠራው ልጅ ለመውለድ ብቻ አይደለም፤ የማይወሰን የማይገታ የፈቲውን ፆር ለማራቅ ጭምር ነው እንጂ፡፡

አንድ ጊዜ የሚከለከሉበትን፣ አንድ ጊዜ ፈቃዳቸውን የሚፈጽሙበትን ሠራ፡፡ ነገር ግን አንድ ወንድ ለአንድ ሴት፣ አንዲት ሴት ለአንድ ወንድ ብለው ዘወትር ሊያደርጉት አይገባም፡፡

አጽዋማትን፣ በዓላትን፣ ኅርስን፣ ትክትን ለይቶ ሊያደርጉት ይገባል እንጂ፤” (ፍት.ነገ.አን.15፥፣ ቍ.
38-58)፡፡
ከላይ እንደ ገለጽነው ሩካቤ ሥጋ በሥርዓት የሚፈጸም እንደ መኾኑ የማይፈጽምባቸው ጊዜያትም አሉ፡፡

እነዚህም የሚከተሉት ናቸው ፦

የእርግዝና እና የንጽሕ ጊዜያት ሚስት በፀነሰችበት ወይም ባረገዘችበት ወቅት

በወር አበባዋ ጊዜ

በመውለጃዋ ጊዜ (ወንድ ከወለደች ከዐርባ ቀን ሴት ከወለደች ከሰማንያ ቀን በፊት) ሩካቤ ሥጋ መፈጸም አይገባም

ዘሌ. (8፥18)፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም “በኅርሷ፣ በደሟ ወራት ሚስትህን አትድረስባት" ፡፡ ግቢህ ከመጽሐፍ ሥርዓት የወጣ እንዳይኾን” በማለት በፅንስ (እርግዝና) እና በንጽሕ ጊዜያት ማለትም በአራስነትና በወር አበባ ወቅት ግንኙነት መፈጸም እንደማይገባ አዝዟል (ፍት. ነገ. አን. 24፣ ቍ. ፷፬)፡፡ በተመሳሳይ መልኩ የሚስት ፅንሷ ከታወቀ በኋላ ለመረዳዳት ካልኾነ በቀር ባሏ ሊቀርባት እንደማይገባ ተደንግጓል (አን. ፳፬፣ ቍ. ፰፻፴፰)፡፡

ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚሔዱባቸው ቀናት እስራኤላውያን እግዚአብሔር ከሙሴ ጋር ሲነጋገር ከመስማታቸው (ሕጉን ከመቀበላቸው) ከሦስተኛው ቀን በፊት እንዲቀደሱ፣ ልብሳቸውን እንዲያጥቡና ሩካቤ እንዳይፈጽሙ ታዝዘው ነበር፡፡ ዛሬም በሐዲስ ኪዳን ባለ ትዳሮች ትምህርተ ወንጌል ለማዳመጥ፣ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለመቀበል፣ ጠበል ለመጠመቅና ለመጠጣት፣ ወይም ለሌላ አገልግሎት ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲሔዱ ከሩካቤ ሥጋ እንዲከለከሉ ታዝዟል (ዘፀ. 19፥10-25 )፡፡ ከዚህም ሌላ በጥምቀት ክርስትና የሚያነሡ (የክርስትና እናት ወይም አባት የሚኾኑ ምእመናን) ክርስትና ከማንሣታቸው በፊትና በኋላ ለሁለት ቀናት ከሩካቤ ሥጋ መከልከል ይገባቸዋል፡፡

ይኸውም መንፈስ ቅዱስን ለማክበር ነው፡፡ ምሥጢረ ጥምቀት ጸጋን፣ ክብርንና ልጅነትን የሚያሰጥ ምሥጢር ስለ ኾነ፡፡ ካህኑ ዘካርያስ የቤተ መቅደሱን አገልግሎት ከፈጸመ ከሁለት ቀን በኋላ ከኤልሳቤጥ ጋር መገናኘቱም ለዚህ ትምህርት ነው፡፡ " ከሁለት ቀን በኋላም ሚስቱ ኤልሳቤጥ ፀነሰች” ተብሎ እንደ ተጻፈ (ሉቃ. 1፥24፤ ፍት. ነገ. አን. 24፣ ቍ. 38)፡፡

በዓላት ቅዳሜ፣ እሑድና በዓበይት በዓላት ሩካቤ ሥጋ መፈጸም የተከለከለ ነው፡፡

ይኸውም በመንግሥተ ሰማያት ጋብቻና ፈቃደ ሥጋን መፈጸም አለመኖሩን ለማጠየቅ ነው፡፡ በዓላት፣ የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌዎች ናቸውና ፡፡

“በትንሣኤስ እንደ እግዚአብሔር መላእክት በሰማይ ይኾናሉ እንጂ አያገቡም አይጋቡምም” እንዲል (ማቴ. 22፥23)፡፡

ሌላው ምክንያት ደግሞ “ንጹሕ የኾነ ነውርም የሌለበት አምልኮ በእግዚአብሔር አብ ዘንድ ይህ ነው … በዓለምም ከሚገኝ እድፍ ሰውነቱን መጠበቅ ነው” በማለት ቅዱስ ያዕቆብ እንደ ተናገረው (ያዕ. ፩፥፳፯)፣ በእነዚህ ዕለታት ወደ ቤተክርስቲያን በመሔድ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን መቀበልና ራስን መጠበቅ ተገቢ ስለ ኾነ ነው፡፡

ፈቃድህን በተቀደሰው ቀኔ ከማድረግ እግርህን ከሰንበት ብትመልስ፣ ሰንበትንም ደስታ፣ እግዚአብሔርም የቀደሰውን ‹ክቡር› ብትለው፣ የገዛ መንገድህንም ከማድረግ፣ ፈቃድህንም ከማግኘት፣ ከንቱ ነገርንም ከመናገር ተከልክለህ ብታከብረው፣ በዚያን ጊዜ በእግዚአብሔር ደስ ይልሃል፤ በምድርም ከፍታዎች ላይ አወጣሃለሁ፤ የአባትህንም የያዕቆብን ርስት አበላሃለሁ” ተብሎ ተጽፏልና (ኢሳ. 48፥13-14)፡፡

#አጽዋማት

“ጸዋሚ ሆይ፥ መላው አካልህ ይጹም፤ አፍህ ክፉ ከመናገር፣ አንደበትህ ከሐሜትና ከስድብ፣ ዓይንህ ሴቶችን ከማየት፣ ጆሮህም ዘፈንና ጨዋታ ከመስማት ይጹም” ተብሎ እንደተነገረን (ርቱዐ ሃይማኖት) ሩካቤ ሥጋም ሰውነት የሚደሰትበት ፈቃድ ስለ ኾነ በጾም ወቅት መታቀብ ይገባል፡፡

በተመሳሳይ መልኩ ባልና ሚስት በንስሓ አባታቸው የተሰጣቸዉን የንስሐ ቀኖና ወይም በራሳቸው ፈቃድ የገቡትን የጾም ሱባዔ እስከሚፈጽሙ ድረስ ከሩካቤ ሥጋ መከልከል ይገባቸዋል፡፡

በአጠቃላይ ባልና ሚስት በፅንስ፣ በአራስነትና በወር አበባ ወቅት፤ እንደዚሁም በበዓላትና በአጽዋማት ቀን ሩካቤ ሥጋ ማድረግ እንደማይገባቸው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታስተምራለች፡፡

ከዚህ በተረፈ ግን ሰይጣን የሚፈትንበትን ክፍተት እንዳያገኝ ባልና ሚስት ሊለያዩ አይገባም፡፡ “ለጸሎት ትተጉ ዘንድ ተስማምታችሁ ለጊዜው ካልኾነ በቀር እርስ በርሳችሁ አትከላከሉ፤ ራሳችሁን ስለ አለመግዛት ሰይጣን
እንዳይፈታተናችሁ ደግሞ አብራችሁ ኹኑ፤” እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ (1ኛ ቆሮ. 7፥5)፡፡

ይህ የሐዋርያው ትምህርት "ሰውነታችሁን ንጹሕ አድርጋችሁ በምትጾሙበት፣ በምትጸልዩበት ጊዜ ነው እንጂ ሥራችሁን ከፈጸማችሁ በኋላ ግን ወደ ፈቃዳችሁ ተመለሱ ይላል፡፡

ይህም ትእዛዝ ባልና ሚስት፣ የጾም፣ የጸሎት፣ የበዓል ወቅት ካልኾነ በቀር ሳይለያዩ ፈቃዳቸዉን መፈጸም እንደሚገባቸው ያስገነዝባል፡፡

ለእርኩሰትና ለበደል ከሚፈፀም ሩካቤ ይጠብቀን።


ttps://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede
2.3K views£itsum, edited  04:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ