Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የሰርጥ አድራሻ: @orthodoxamero
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 44.89K
የሰርጥ መግለጫ

ዲያቆን ፍፁም ከበደ
ሀሳብ ካሎዎት @Fisumkeb
facebook Link...
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-05-07 17:36:11 እኛም መጽሐፉን በማንበብና በማስነበብ እንዲህ ያሉ የእውቀት አድባር የሆኑ መምህራንን ልናበረታታ ልናግዝ ይገባል!

መጽሐፉን እናንብብ እናስነብብ!


(ዲያቆን ወሰንየለው በሐሩ)
2.8K views£itsum, 14:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 17:36:11 የመጽሐፉ ርዕስ፦ አኰቴተ ቍርባን
የመጽሐፉ አዘጋጅ፦ ቀሲስ ዶ/ር መብራቱ ኪሮስ ገብሩ
የመጽሐፉ የገጽ ብዛት፦ 367
የመጽሐፉ ዋጋ፦ 230 ብር
የኅትመት ዘመን፦ 2012 ዓ.ም

የመጽሐፋ ዋና ዓለማ፦
1, የኢትዮጵያዊውን ሥርዓተ ቅዳሴ ውበቱን መግለጽና ጣዕሙን ማስረዳትና
2, ኢትዮጵያዊውን ቅዳሴ ላዘጋጁልን ቀደምት ቅዱሳን አባቶች እውቅና እንድንሰጥ ጥሪ ማቅረብና እውቅና መስጠት ነው።
መጽሐፉ እነዚህን ወርቃማ አላማዎች ይዞ በአራት ታላላቅ ምዕራፎች የተዘጋጀ፥ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ ቅዳሴ መሠረቱን፥ ታሪካዊ እድገቱን እና ይዘቱን የሚያሳይ በመረጃ የዳበረ፥ ጥልቅ ጥናት የተደረገበት ዳጎስ ያለ መጽሐፍ ነው።

ምዕራፍ አንድ፦ ቅዳሴ ምንድነው? በሚል ዐቢይ ርዕስ በመጀመር በአንድ ወቅት (1960ዎቹ) የሩሲያ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ የነበሩት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ አሌክሲ ለአንድ ጋዜጠኛ ቤተክርስቲያናቸውን "ቅዳሴ የምትቀድስ ቤተክርስቲያን" ብለው በገለጹበት ውብ አገላለጽ በመጀመር ቅዳሴ በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ከቃሉ እስከ ይዘቱ እንዴት እንደሚተረጎም፥ እንዲሁም ስያሜው በሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ምን እንደሚመስል በአጭሩ በመግለጽ ይጀምራል። በቀጣይነትም በዚህ ምዕራፍ ውስጥ የቅዳሴ መገለጫ ባሕርያት በሚል ንዑስ ርዕስ አማካኝነት አምስት የሚሆኑ ዋና ዋና የቅዳሴ ባሕርያት ተዳሰውበታል። በተጨማሪም የቅዳሴ ውበት በሚል ርእስ ሥር ቤተክርስቲያን በምድር ያለች ሰማይ መሆኗን፥ በውስጧም የሚከናወነው ሥርዓተ አምልኮም ሰማያዊ መሆኑን በመግለጽ ቅዳሴ በሥጋ፥ በነፍስና በመንፈስ የምንቀደስበት ውብ የሆነ የአምልኮ ሥርዓት ነው በማለት የቅዳሴውን ሰማያዊ ውበት በጥቂቱ ይገልጣል። በመጨረሻም የቅዳሴ መንፈሳዊ ዕሴቶች(ጥቅሞች) በሚል ሰማያዊ ውበት ባለው በቅዳሴው ተሳታፊ በመሆን ስለሚገኘው ጥቅምና ዋጋ፥ እንዲሁም ዘወትር የቅዳሴው ተሳታፊ እየሆንን ነገር ግን ምን መንፈሳዊ ለውጥ ለማይታይብን ደግሞ "ለምን ቅዳሴው አለወጠኝም?" በሚል መነሻ ጥያቄ ሰፊ ማብራሪያ በመስጠት ምዕራፉን በመደምደሚያ አሳብ ይቋጫል።

ምዕራፍ ሁለት፦ የጥንቷ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮ በሚል ዐቢይ ርዕስ በጥንቷ ቤተከርስቲያን የነበረው ሥርዓተ አምልኮና የቁርባን ምሥጋናና ጸሎታት ምን ይመስሉ እንደነበረ በመጠኑ ይዳስሳል። ይሄንንም ለማስረዳት የምሥጢረ ቁርባን አመሠራረት በሚል የጥንቷን ቤተክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮ ለመረዳት የሚያግዙ የአይሁድ ሥርዓተ አምልኮ፥ ወንጌላትና ሐዋርያው ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ሰዎች የላከው መልእክት(ስለ ቅዱስ ቁርባን የተጻፉ ምንባባት)፥ አጋፔ እና ቅዱስ ቁርባን፥ የቅዱስ አግናጥዮስ ዘአንጾክያ መልክታት የሚሉ የጥንቷን ቤተክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮ ለመረዳት የሚያግዙ መንደርደሪያ አሳቦች ተነሥተውበታል። በመቀጠልም የጥንቷ ቤተክርስቲያን ቅዳሴያት በሚል ርዕስ የምዕራፉ ዋና አሳብ ይዘልቅና በአንደኛውና በሁለተኛው ክፍለ ዘመን መጻሕፍተ ሥርዓተ ቤተክርስቲያን ምን እንደሚመስሉና ስለጥንቷ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮ ፍንጭ ይሰጣሉ የተባሉ ከጥንት እስከ አምስተኛው ክፍለ ዘመን የነበሩ መጻሕፍትና ጸሎታት በስፋት ተዳሰውበታል።

ምዕራፍ ሦስት፦ ይህ ምዕራፍ የመጽሐፉ ዋና ክፍል ነው። የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ ቅዳሴ መሠረት እና ታሪካዊ እድገት በሚል ርዕስ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ ቅዳሴ ዕድገቱ ምን እንደሚመስልና ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት የጥንቷን ቤተክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮ መሠረት አድርገው በማስፋፋት ኢትዮጵያዊ መልክ ያለው ሥርዓተ ቅዳሴ እንደሠሩልን ይነግረናል። እንዲሁም የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ ቅዳሴ የዛሬውን መልክ ለመያዝ አራት የዘመናት ሂደቶችን እንዳለፈና እያንዳንዱን የዘመን ለውጥና እድገት በጥቂቱ በመዳሰስ ታሪካዊ እድገቱን ያስቃኘናል። እንዲሁም የግእዝ ሥነ ጽሑፍ ወርቃማ ዘመናት ማለት ከ15 እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ድረስ ባሉ ዘመናት የተነሡ የነገረ መለኮት ክርክሮች ለግእዝ ሥነ ጽሑፍ መስፋፋትና ለሥርዓተ ቅዳሴ እድገት አይተኬ አስተዋጽኦ እንዳበረከተ በተለያዩ ማሳያዎች አስደግፎ ያስቃኘናል። በተጨማሪም በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ቅዳሴ ውስጥ ዓለማቀፍ ተቀባይነትን ባገኙ የቤተክርስቲያን አባቶች ስም የተሰየሙት ቅዳሴያት ስያሜው በተሰየመላቸው አባቶች የተደረሱ ሳይሆኑ የቀደሙት የኢትዮጵያ ቅዱሳን ሊቃውንት ከትሕትናና የድርሰቱን ተቀባይነት ከማጉላት አንጻር በሌሎች አባቶች ስም የተሰየሙ የኢትዮጵያ ሊቃውንት ሥራ መሆኑን የተለያዩ ማሳያዎችን በማስረጃ እያስደገፉ ጥናታዊ በሆነ መንገድ ድምዳሜ ላይ ይደርሳል።
በአጠቃላይ በዚህ ምዕራፍ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮ ዕድገቱ ምን እንደሚመስል ከጥንት እስከ ዛሬ ያለውን ታሪካዊ እድገቱ የተቃኘበትና ቀደምት የኢትዮጵያ ቅዱሳን ሊቃውንት አባቶቻችን የነበራቸውን ዓለማቀፋዊ የቤተክርስቲያን ታሪክና የትምህርተ ሃይማኖት እውቀታቸው ምን ያህል ሰፊ እንደነበረና ያን እውቀታቸውን በመጠቀም ለሥርዓተ አምልኮ እድገት አስተዋጾ በማድረገ ዛሬ የሚገኘውን ውብ ሥርዓተ አምልኮ እንደሠሩልን ያስረዳል።

ምዕራፍ አራት፦ የቅዳሴ አጠቃላይ ይዘት በሚል ርዕስ የሚጀምር የመጽሐፉ የመጨረሻ ምዕራፍ ሲሆን በውስጡም ሦስቱን የቅዳሴ ክፍሎች ማለትም የዝግጅት ክፍል(preparatory service)፥ የትምህርት ክፍል(Lections) እና ፍሬ ቅዳሴ (anaphora) የተሰኙ ክፍሎችና በየክፍሉ የሚገኙ ጸሎታት፥ ዝማሬያት፥ ንባባትና ድርጊቶችን በጥንቷ ቤተክርስቲያን የነበራቸውን ቦታና ሥርዓት እንዲሁም በሌሎች አብያተክርስቲያናት (በኮፕቲክና ሶርያ) ጋር ያለውን ተመሳሳይነትና ልዩነት በማሳየት የጸሎታቱንና የዝማሬያቱን የትመጣነታቸውን በመጠቆምና የኢትዮጵያ ሊቃውንት ለጸሎታቱና ለዝማሬያቱ እንዴት ኢትዮጵያዊ መልክ እንደሰጧቸው በአባቶች መንፈሳዊ ጥበብ በመኩራትና በመደነቅ ከበቂ ማስረጃ ጋር አሰደግፎ ያሳየናል።
በተጨማሪም ቅዱስ ቁርባንን ከመቀበል በፊትና በኋላ ስለሚገኙ ጸሎታትና የጸሎታቱን ምንጮች ከየት እንደሆነ አጭር ዳሰሳ ያቀርባል። በመጨረሻም ስለ ቅድስት ቤተክርስቲያን ሕንጻና በውስጧ ስለሚገኙ ምሳሌያዊና መንፈሳዊ ትርጓሜ ስላላቸው ድርጊቶችና ምልክቶች እንዲሁም በሕንጻው የሚሣሉት ቅዱሳት ሥዕላት ሕንጻ ቤተክርስቲያንን እንዴት በምድር ያለች ሰማይ እንደሚያሰኛት ይነግረንና በቅዳሴው ውስጥ የምናያቸው የሥርዓተ አምልኮ ድርጊቶች የራሳቸው ትርጓሜ እንዳላቸውና ከእነዚህም ውስጥ የተወሰኑ ድርጊቶች በመዳሰስ በእነዚህ ድርጊቶች አማካኝነት በቅዳሴው የሚሳተፉ ምእመናን ሁለተናቸው የቅዳሴው ተሳታፊ በመሆን እንደሚቀደስ ይነግረንና በማጠቃላያ አሳብና መልእክት የምዕራፉና የመጽሐፉ ፍጻሜ ይሆናል።

በአጠቃላይ መጽሐፉ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንን ቅዳሴ ውበቱንና ጣዕሙን፥ የአባቶቻችንን አስተዋጽኦ ከመጠቆም ባሻገር የቤተክርስቲያናችንን ሥርዓተ አምልኮ ታሪካዊ እድገቱ ምን እንደሚመስል ሰፊ ጥናት በማድረግ ለምእመናንና የነገረ መለኮት ደቀመዛሙርት በተለይም Liturgical Theology ውስጥ ላሉት ለተጨማሪ ጥናት በር የሚከፍትና የበለጠ የአባቶቻችን ድካም እንድንረዳና ዋጋ እንድንሰጥ የሚያደርግ በመረጃና በማስረጃ የበለጸገ ግዙፍ ጥናታዊ ሥራ ነው።

ይሄን የመሰለው ድንቅ መጽሐፍ ላበረከቱልን ለመምህራችንና ለአባታችን ለቀሲስ ዶ/ር መብራቱ ኪሮስ እግዚአብሔር ይስጥልን! ከእጅ ቁርጥማት ከደረት ውጋት ይሰውርዎት! ወርቃማ ብዕርዎት ትለምልም!
2.7K views£itsum, 14:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 17:35:44
2.2K views£itsum, 14:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 20:26:49 "ኦርቶዶክሳዊ አስተሳሰብ" የሚለው አገላለጽ ጥንቃቄ የሚያስፈልገው ይመስለኛል። (በቅርብ ዘመናት ደግሞ በብዛት እየተነገረ ይገኛል።) ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ የሰውን አስተሳሰብ በእውነተኛ ክርስትና እንደሚቃኝ ይታወቃል። ነገር ግን ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ማዕከሉ እምነት፣ መገለጥ እና አንድነት (communion) ሆኖ ከእሳቤዎች (thoughts) ከፍ ያለ ነው። ሁሉን ነገር በእሳቤ ደረጃ ማቅረብ የዘመነ-አብርሆት (Enlightenment) መንገድ ነው። I am afraid we may unknowingly subscribe to the thought paradigm of the Enlightenment. We must steadfastly keep the revelatory, eschatological, and mystical aspect of Christianity in our teachings. Just to inspire second thoughts.

በረከት አዝመራው

https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebed
2.7K views£itsum, edited  17:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-05 20:59:18 + ድንግል ማርያም የሊባኖስዋ ድልድይ +

በቤሩት በክርስቲያኖችና ሙስሊሞች ዘንድ ብዙ ልዩነቶች አሉ::  ከየትኛውም ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ሕግ በላይ ግን ሙስሊሞቹንና ክርስቲያኖቹን  አንድ የሚያደርግ የጋራ ጉዳይ አለ:: ክርስቲያኖች ከሙስሊሞች ጋር እየተጋፉ ሰልፍ ይዘው የሚውሉበትና የሚጎበኙት ታላቅ ሥፍራ አለ: : ሁሉም አንድ ስም ከአፋቸው በፍቅር ሲጠራ የሚውልበት ጊዜ አለ:: ይህች ሁለት ታላላቅ ወገን የምታስተሳስር ድልድይ ቅድስት ድንግል ማርያም ናት::

የሊባኖስ ክርስቲያኖች  በመጽሐፋቸው በቅዱስ ገብርኤል የብሥራት ቃለ ብሥራት ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስን የወለደችው ቅድስት ድንግል ማርያም እጅግ ትወደዳለች:: የሊባኖስ ክርስቲያኖች  ቅዱስ ገብርኤል ያበሠረበትን ዕለት በታላቅ ደስታ ያከብራሉ::

የሊባኖስ ሙስሊሞች ደግሞ በመጽሐፋቸው "መልአኩ ገብርኤል ለማርያም ነቢዩ ኢሳን እንደምትወልድ ነግሮአታል:: ይህ ብሥራትም በቁርዓን ሁለት ቦታ የተገለጸ ሲሆን አንደኛው ሱራህ 3 አል ዑምራን እና ሱራህ 19 ሱራህ አል መርየም እንደሆነ ይገልጻሉ:: 

ሙስሊሞቹ እንዲህ ይላሉ:-  "በቅዱስ ቁርዓን በስም የተጠቀሰችው ብቸኛ ሴት ማርያም ብቻ ናት:: የማርያም ነገር በቅዱስ ቁርዓን 30 ጊዜ የተነሣች ሲሆን እርስዋ የተጠቀሰችበት መጠንም ቁጥርም ከነቢዩ መሐመድ እናት እኅቶችና ሚስትና ሴት ልጆች በላይ ነው" በዚህ የተነሣ በሙስሊሞቹም ዘንድ ያላት ሥፍራ የክብር ሥፍራ ነው::

በሊባኖስ የገብርኤል ብሥራት በዓል (Feast of annunciation) ቀን ማርች 25 ከዓለም በተለየ መልኩ የክርስቲያኖችም እና ሙስሊሞችም በዓል ቀን ሆኖ በብሔራዊ በዓል ቀን  ይከበራል:: ሊባኖሳውያን ሙስሊሞችና ክርስቲያኖች በብዙ ነገር ይለያያሉ:: አንድ ነገር ላይ ግን ይስማማሉ::

ማርያምን በመውደድ!

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
2013 ዓ.ም አዲስ አበባ ተጻፈ
Source :- Lorient Today /March 26 2019/
                 Agenzia Fides/March 25 2020/

https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebed
3.1K views£itsum, edited  17:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-04 09:12:13 ለሁሉም ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ


‹‹በመምህር አምላክ ክፍል ሁለት››
ለሁሉም ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ በዚህ ዓመ ሢመተ ጵጵስና እንዳይደረግ ስለመጠየቅ
ደፋሮች ከመብዛታቸው የተነሳ ቤተ ክርስቲያንን ሳይቀር መዳፈር ከጀመሩ ውለው አድረዋል፤ ጉዳዩ ከሕዝብ ሳይደርስ ይፈታል በሚል ተስፋ ብዙ ዓመታት ታግሰን ቆይተናል፡፡ ዘንድሮ ግን ችግሩ ሊሰወር ከማይችልበት ደረጃ ላይ ደርሶ እንደ ተራራ ላይ መንደር፤ መቅረዝ ላይ እንዳለ መብራት ለሁሉ የሚታይ ሁኗል ከዚህ በኋላ እንደ ቀድሞው በዝምታ ማለፍ ግን ለተመልካቹ ምእመን ይህ ስህተት ትክክል ነው ብሎ እንደ ማስተማር የሚቆጠር ድፍረት ስለሆነ እውነትና ሐሰቱን በአደባባይ ለመናገር ተገደናል፡፡
ባለፈው ጽሑፌ አሁን ለጵጵስና ሲመት አጣዳፊ ሁኔታ እንደሌለ እና ሢመቱም ከተፈጸመ ቤተ ክርስቲያን ወደማትወጣው ከባድ ችግር እንደምትገባ ለመጠቃቀስ ሞክሬ ነበር፡፡ ዛሬ ደግሞ ሹመት ይገባናል ባይች ምን እያደረጉ እንደ ሆነ ምእመናን አውቀው ለቤተ ክርስቲያን ዘብ እንዲቆሙ ለማነቃቃት ተመልሻለሁ፡፡ ሹመት ፈላጊ መነኰሳት ከሀገር ውስጥ እስከ ውጭ ሀገር ተሰባስበው በጠቅላይ ቤተ ክህነት እና በየሀገረ ስብከቱ ግቢ ገንዘባቸውን ማፍሰሱን ተያይዘውታል፡፡ ቤተ ክርስቲያን ከየገዳማቱ ከየመናኞቹ ይሆናል ያለችውን በጸሎት እና በሕጋዊ ምርጫ መምረጥ እንዳትችል በሴት ወይዘሮ፣ በወንድ መኰንን፣ በአማላጅ በአጓዳጅ፣ ለመሾም የሚደረገውን ሩጫ ለተመለከተ ሰው ውነትም ከዘመኑ መጨረሻ ደርሰናል አሰኝቶ ተስፋ ያስቆርጣል፡፡
ለመሆኑ እነዚህ ግለሰቦች ይህንን ሹመት ምን ሊሠሩበት አስበው ነው የሚሽቀዳዳሙለት?
 ገንዘብ ያልጠገቡት ገንዘብ እናገኝበታልን ብለው፤
 አንዳንዶቹ ሃይማቱ ሳይኖራቸው ቤተ ክርስቲያንን የፖለቲካ ማስፈጸሚያ ለማድረግ የተመለመሉ ናቸው፡፡
 ገንዘብ የሞላቸው ምድራዊ ርካሽ ክብር (ስብሓት ብጡል) እናገኝበታልን ብለው ነው፡፡ እንጂ እንጸድቅበታልን ቤተ ክርስቲያንን እናግዝበታለን ብለው እንዳል ሆነ ምንም ጥርጥር የለኝም፡፡ ምክንያቱም እንጸድቅበታለን ባዮቹ፤ ቤተ ክርስቲያንን እንረዳበታለን ባዮቹ ሹመቱ ፈልጎ ተማጽኖ ያገኛቸዋል እንጂ እነ አርሱ ሹመቱን ሲፈልጉት አይገኙም ይገባናል ብለውም አያስቡም፡፡
ማስጠንቀቂያ ለምእመናን
በሀገር ልጅነት፣ በግል ትውውቅ፣ በመንፈሳዊ አባት እና ልጀነት፣ ወይም በሀብታችሁ በሥልጣናችሁ ታዋቂ ስለሆናችሁ ወደየጳጳሳቱ ለሹሙልን ምልጃ የምትሄዱ ቤተ ክርስቲያንን ከሚያቃጥሉት ሰዎች እኩል እየበደላችሁ መሆኑን ዕወቁ፡፡
በተጨማሪም በየአካባቢያችሁ የመንግሥት ባለሥልጣናትን፤ ታዋቂ ግለሰቦችን፣ አድባራት እና ገዳማት፣ ማኅበራትን፣ የሰንበት ትምህርት ቤቶችን ሽምግልና እየላኩ ለመሾም የሚሞክሩ ሰዎችን አይታችሁ እና ሰምታችሁ ዝም ካላችሁ(የማታጋልጡ ከሆን) ቤተ ክርስቲያን ስትዘረፍ፣ እሳት ሲለኮስባት፣ ቅርሷ ሲወድም አይቶ ዝም ከማለት ጋር እኩል ስለሆነ እንዲህ አይነት ግለሰቦችን ለማጋለጥ ተዘጋጁ፡፡
በመጨረሻም መታወቅ ያለበት ጉዳይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከ1600 ዓመታት በላይ በአንድ ጳጳስ የኖረች ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡ አሁን ከ50 በላይ ጳጳሳት አሉ፡፡ ችግራችንም የጳጳሳት ቁጥር ማነስ ሳይሆን ያሉት እንደሚገባ አለማገልገል እንደሆነ ባለፈው በችግሩ ጊዜ ከጳጳሳቱ አንደበት ሰምተናል፤ ስለዚህ ቤተ ክርስቲያንን ወደባሰ ችግር የሚወስድ ስለሆነ በአሁኑ ሰዓት ለፖለቲካ ማስፈጸሚያ የሚካሄደው የጵጵስና ሹመት አያስፈልግም የሚለውን ከሊቅ እስከ ደቂቅ በአንድነት ማስተጋባት እና ቤተ ክርስቲያንን ማስከበር የዛሬ ሥራችን ነው፡፡
‹‹በመምህር አምላክ በሚመጣው ግንቦት ሢመተ ጵጵስና እንዳይፈጸምብን››
መ/ር ኀይለ ማርያም ዘውዱ ዘቦሩ ሜዳ
ሚያዝያ 25/2015 ዓ ም


https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebed
4.2K views£itsum, edited  06:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 20:42:54 ተጨማሪ ነገር....

ከወራት በፊት አንድ ቀን ከአንድ ወዳጄ ቤት ለሆነ ጉዳይ ሔድሁ። ልጁ ዲያቆን ነው። ከደጅ ወጣ ብሎ መስቀል ተሳለመ። የ4 ዓመት ሕፃን ልጁም ሮጦ መጣና መስቀል ተሳለመ። ባለቤቱ በቅርቡ የወለደች አራስ ናት። ውድ ባለቤቷና ልጇ መስቀል ሲሳለሙ እርሷ ግን በር ላይ ቊማ ዝም አለች።

እኔ ነገሩ ገብቶኛል። «እንዴት ሰነበትሽ? እየጠነከርሽ ነው? ዐዲስ የተወለደው ሕፃንስ እንዴት ነው?» አልሁና የሚገባውን ጥያቄ ጠየቅሁ። ከዚያው ራቅ እንዳለች በሚገባ መልስ ሰጠችኝ። «ታዲያ ለምንድን ነው መስቀል ያልተሳለምሽ?» አልኋት። «አይ የማይፈቀድ መስሎኝ ነው እንጅ» አለች። «ኸረ ይቻላል! ማን ከለከለ?» ስላት ቀልጠፍ ብላ መጥታ ተሳለመች።

ሴቶች እኅቶቻችንና እናቶቻችን ሲወልዱ ከካህናት እጅ መስቀል መሳለም የማይቻል ይመስላቸዋል። ይህ ብቻ አይደለም ጠበል ካልተረጩ ወደ ቤተ ክርስቲያን መሔድ፣ ጸሎት ማድረግ፣ መጽሐፍ ቅዱስ ማንበብ እና የመሳሰሉ አገልግሎቶች ላይ መሳተፍ የማይቻል ይመስላቸዋል። ክርስትና እስከሚያስነሡ ድረስ (40/80 ቀን ሙሉ) ቤተ ክርስቲያን ድርሽ ማለት የማይችሉ ይመስላቸውና በዚያው ተዳፍነው ይከርማሉ።

በመሠረቱ ወሊድ ከባድ ነው። ሰውነታቸው እስከሚጠነክር ድረስ ቤተ ክርስቲያን መሔድ ላይሆንላቸው ይችላል። ዐቅም ካለ ግን ቤተ ክርስቲያን መሔድና ከውጭ ሆኖ ማስቀደስ ቢቻል መልካም ነው። አራስ ናትና ቤተ ክርስቲያን መሔድ አትችልም ማለት ግን ሌላ ውንጀላ ነው። «ክርስትና ሳታስነሽ ለምን ቤተ ክርስቲያን መጣሽ?» ብለው በጥያቄ የሚስድቧትም አሉ። በጣም ትልቅ ስሕተት ነው።

አስረግጦ መናገር ይገባል። የወለደችው አራስ ቤተ ክርስቲያን መሔድ ትችላለች። ቤተ ክርስቲያን ደርሳ ከቅጽረ ግቢው ውጭ ሆና አምልኮቷን መፈጸም መብቷ ነው። የጸሎት መጽሐፍ ይዛ መጸለይ፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ፣ ጠበል መጠጣት፣ እምነትን መቀባት፣ ከካህናት እጅ መስቀል መሳለም ትችላለች። በተቻለ መጠን ታጥባና ንጽናዋን ጠብቃ  ከውጭ ያሉ አገልግሎቶችን መካፈል መብቷ ነው።

Getnet Aytenew
_

https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebed
741 views£itsum, edited  17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 20:42:25
698 views£itsum, 17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 19:50:01 ሰው ሲወለድ ሙስሊም ነበር ይላሉ ሙስሊሞች በተጨማሪ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ «እኔ ጌታ ነኝ አምልኩኝ አላለም ፣ መጽሐፍ ቅዱስ ተበርዞዋል ይላሉ» እንግዲህ ለእያንዳንዱ ከሙስሊም ለሚመጣ ጥያቄ አጥጋቢ መልስ ለማግኘት ከፈለጉ ይህን ቻናል ይቀላቀሉ  ። የተበረዘው መፅሐፍ ቅዱስ ነው ወይ ቁርአን ? አንድ ቅጂ ብቻ አለው  ፍፁም ከፈጣሪ ነው ተብሎ በሙስሊሞች የሚታመነው ቁርአን በዚ በኛ ዘመን 4 ዓይነት ቅጂዎች አሉት.....read more
785 views£itsum, 16:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 09:22:27 "የአንተ መጽሐፍ ወደ እኔ ቤት ሲገባ መጽሐፎቼ ሁሉ ከደጅ ወጥተው በግእዝ ሐዊሳ ሐዊሳ እያሉ እጅ ነሥተው ተቀብለውታል:: ሐዊሳ እንኩዋን ደህና መጣህ ማለት ነው"

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ጥር 8/ 2012 ዓ ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
1.4K views£itsum, 06:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ