Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የሰርጥ አድራሻ: @orthodoxamero
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 44.89K
የሰርጥ መግለጫ

ዲያቆን ፍፁም ከበደ
ሀሳብ ካሎዎት @Fisumkeb
facebook Link...
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-04-24 14:15:18 ጥዑም ዝማሬ

" ልቤ ያውቀዋል "

ልቤ ያውቀዋል ያደረክልኝ ነገር
የሰራህልኝን ስራ
መዳኒዓለም አወጣህኝ ከመከራ
በቃል ጉልበት አይወራ (2)

አዝ

መስቀል ተሸክመህ በደም ርሰህ
እኔን በመከራ ዳግም ወልደህ
በክብር ተሻገርኩ ክሰህልኝ
በህይወት አቆምከኝ ወድቀህልኝ

አዝ

የበደሌን ጋራ አቀበቱን
የባርነት ሰነድ እዳ ክሱን
አጥፍተህው ጌታ መድሀን ሆነ
እርቃኔ በእርቃንህ ተሸፈነ

አዝ

በፍቅርህ መአዛ እርክቷል ልቤ
በማይቆም መውደድህ ተከብቤ
የህይወቴ ወደብ መስቀልህ ነው
ወጀብ እና ንፍስ የማይነቅለው (2)

አዝ

የእሾህ አክሊል ደፍተህ ኤልሻዳይ
እፎይ አለ ልቤ ከስቃይ
ሆኖልኛል መዳን አንተ ተማህ
ነፃ ወጣሁ ሸክሜን አንተ ተሸክመህ

አዝ

ዙፍንህን አስተወህ የኔ ፍቅር
ከሰማይ ሀገርህ መጣ በምድር
ታየህ ስትፈልገኝ ልጄ ብለህ
ፈራጅና አስዳቂ አምላኬ ነህ (2)



ሊቀ ዲያቆን ዘማሪ ነብዮ ሳሙኤል

ttps://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede
3.2K views£itsum, edited  11:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 19:42:34 ሞታችንን ለትንሣኤ

የ'#ቤተ_ክርስቲያን መከራ የማይጠፋ የልብ ቁስል ነው፡፡
ልቡ የቆሰለ ሰው በየትኛው ልቡ ማረፍ ይችላል? ልብ የሚለበልብ የጥቃት አረመጨት እጅጉን ያማል፡፡እንዴትስ ማረፍ ይቻላል፡፡
ከቤተ ክርስቲያን መከራ ይልቅ የአልጋ ቁራኛ የደዌ ዳኛ መሆን ይቀላል፡፡

ቁስሉ ፈውስ ይፈልጋል ፡፡ ፈውሱም ከአምላካችን እና ከእኛ ከኦርቶዶክሳውያን ብቻ ነው ያለው፡፡ ቁጭ ብሎ ከማንጋጠጥ ለፈውስ መላላጥ ይሻላል፡፡ እነሱ አቆሰሉን። እኛ ግን በዚያው ቆስለን መቅረት የለብንም። ዋናተኛ ባህሩን የሚቀዝፈው እና የሚዋኘው እጁን በዘረጋው ልክ ነው፡፡ መሆን የምንፈልገውን የምሆነው ህሊናችን በፈቀደው ልክ ነው፡

ቁስላችንንን ለመድኃኒት፦
ምታችንን ለትንሣኤ ፦
መገፋታችንን ለእረፍት፦...... እንጠቀመው፡፡

ወንድሜ ሆይ እኅቴ ሆይ እንደ ምስል ቁሞ መመልከት ሕያውነትን አይገልጽም ሕያው የመሆናችን ምልክቱ መንቀሳቀሳችን ነው፡፡የሚበላ እና የሚጠጣ በእርጥብ ሥጋ የተጠቀለለ ሰውነት ብቻ ልንሆን አይገባም ፡፡

"#ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ፥ ጎልምሱ ጠንክሩ።" ፩ኛ ቆሮ. ፲፮፥፲፫ ብሎ ሐዋርያው የመከረንን አንዘንጋ።

''ሰነፍ እጆቹን ኮርትሞ ይቀመጣል" መክ. ፬፥፭

ሰነፍ ያው ሰነፍ ነው በጥቂቱ ትጋቱን የማይገልጥ የፀሐይ ልጥ ነው፡፡ ብጥስጥስ አንድነት ማገር አይሆንምና፡፡ ከሞት ለማምለጥ የሚደረግ የማያስመልጥ መንፈራገጥ ነው፡፡ የሚሞት ሰው ደግሞ አይፈራም። የእኛ ጊዜ አሁን ብቻ ነው። ነገን የሚወስናት አሁን በኦርቶዶክሳዊ አንድነት በምንሠራው ተግባር ነው፡፡

ነጻ አውጪ የሚፈልግ ሰው ነጻ አይወጣም ፡፡

ትልቁ ችግር ባሪያነቱን የማያውቅ የጥፋት ባሪያ ነው፡፡በኦርቶዶክሳውያን ላይ እስከ አሁን የነበረው ካፊያ ነው የወደፊቱ ግን ዶፍ የእልቂት ዝናም ይሆናል፡፡

ገብረ መድኅን እንየው


https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede
3.3K views£itsum, edited  16:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 15:13:37 "በሃይማኖተኛው" ትውልዳችን ውስጥ ሁለት ጉዳዮች ያሳስቡኛል፦
1. ብዙዎች ውድ ዋጋ ከሚከፍሉለት ማኅበረሰባዊ ኃላፊነት ነጻ የሚያደርግ የውሸት መንፈሳዊነት (pseudo-spirituality)፣
2. የሃይማኖት ተቋማት ከሰውነት ክብር በላይ የተለየ ክብር የማይገባቸው ይልቁንም አታላይ እና ብልጣብልጥ የሆኑ ብዙ ሰዎች በመሪነት የሚሠየሙባቸው እየሆኑ መምጣታቸው።
***
ነገሮች የበለጠ ሳይበላሹ ግልጽ ውይይት እና መፍትሔ ያስፈልገን ይመስለኛል።
329 views£itsum, 12:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 10:16:04 #የመታደስ በዓል(Hanukkah) እና እኛ

ይኽ የመታደስ በዓል የተጀመረው በመቃብያን ዘመን ነው።  የሚከበርበትም ምክንያት የሶርያ መሪ የኾነው አንጥያኮስ በ170 ቅ.ል.ክ ኢየሩሳሌምን አሸንፎ በግዕ በሠውበት እርያ(አሳማ) ሠዋ ሥዕለ ኪሩብ ባቆሙበት ሥዕለ ፀሓይ አቆመ፤በዚህ ጊዜ በካህኑ ማታቲያስ መሪነት መቃብያን ከ(166-142) ቅ.ል.ክ ውጊያ ካደረጉ በኋላ ሐገራቸውን  ከሶርያውያን በ165(164)  ቅ.ል.ክ  ቤተመቅደሱን ከጣዖት መመለኪያ ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር መለሱት(አደሱት) ይህን ቀን እስከ አሁን ድረስ  የመታደስ(Hanukkah) በዓል እየተባለ ይከበራል።


እንግዲህ  ይህን የመታደስ በዓል ወደኛ ሕይወት አምጥተን ብንመለከተው ቀጥታ አሁን ያለንበትን ልክ እንደ መስታዎት ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው፤ ልክ በማርያም ዘናይን ፊት እንደ ነበረው መስታወት።

አሁን ሁላችንም  የእግዚአብሔር መቅደስ በተባለው ሰውነታችን ላይ እርያ የተባለውን ዘረኝነት እየሠውን ነው የምንገኘው።እርያ(ዘረኝነት) የአንድ ኦርቶዶክስ መገለጫ አይደለም ሊኾንም አይችልም ምክንያቱም እርሱ ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያን ነውና።ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያን ደግሞ ልክ እንደ አቤል ወንድም ቃኤል መሬት የሚያርስ(በዚህ ዓለም ቅዠት ማለትም በዘረኝነት የሚመላለስ) መኾን የለበትም።


አንጥያኮስ በእግዚአብሔር ቤተመቅደስ እርያ እንደ ሠዋ እንዲሁ  ሰይጣንም በኛ ሰውነት ዘረኝነት እየሠዋ ነው፤ ይህንን ደግሞ በትንሣኤ ጊዜ መልአኩ ዲንጋዩን አንከባሎ በላዩ እንደ ተቀመጠ እንዲሁ በልባችን ላይ የተጋረጠውን የዘረኝነት ድንጋይ እንዲያንከባልልና በዘባነ ልቡናችን ኢትዮጵያዊነትን እንዲያስቀምጥልን መልአኩን ወደኛ መጥራት ይገባናል።

ወንድሜ ምናልባት ለኔ ዘር መቆርቆሬ ነው ማሰቤ ነው ልትለኝ ትችላለህ ነገር ግን እናት ቅድስት ሰቀሌኔቂ የተናገረችው አስታውስ  ''ሰይጣን ሰውን ከአቅም አብልጦ በጾም የጸና ተጋድሎን እንዲይዝ ሰውን ያነሳሳዋልና ያማረ መካከለኛ መንፈሳዊ ተጋድሎን እንለይ ''

ብላለች ወንድሜ እንኳን ዘረኝነት ጾምን እንኳን ሴይጣን ካነሳሳህ ፍራ ሴይጣን ወደራሱ ጎትቶ የሚያመጣበት ወጥመድ ውስጥ እየገባህ መኾኑን መገንዘብ አለብህ ልክ ዮሴፍ ለጲጢፋራ ሚስት ጨርቁን ትቶ ክርስቶም ለመቃብሩ መግነዙን ትቶ እንደ ሔደ አንተም አዲሱን ልብስ በመልበስ አሮጌውን የዘረኝነት ልብስ ልትጥለው ይገባል።
በዘባነ ልቡናህ ላይ ኦርቶዶክሳዊነትን አንግሥ።


(ዲያቆን ሞቱማ ቸርነት)



https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede
870 views£itsum, edited  07:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 20:48:28 #ዕለተ_ሰንበተ_ክርስቲያን ( እሁድ)

#ዳግማይ_ትንሳኤ

ዳግማይ ትንሣኤ (ሁለተኛው ትንሳኤ) ማለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ በተነሳ በስምንተኛው ቀን በዕለተ እሑድ ደቀ መዛሙርቱን በአንድነት ተሰብስበው ሳሉ ለሁለተኛ ጊዜ ተገልጦ ትንሳኤው ምትሐት እንዳይደለ ፍጹም አማናዊ እንደሆነ እና የተጠራጠረውን ቅ/ቶማስና እንዲዳስሰውና በማድረግ ያሳመነበት ዕለት ነው፡፡ዳግማይ (ሁለተኛ) ያሰኘው መገለጡን ይዞ ነው፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ትንሳኤ ባለፈ የሚመጣውን እሑድ ሰይማ ታከብረዋለች፡፡ /ዮሐ20፤24-30/

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሐዋርያቱ ቀድሞ በተዘጋ ግንብ ገብቶ ሰላም ለእናንተ ይሁን ብሎ ተገልጦላቸው ነበር ዳግመኛም ሐዋርያው ቶማስ ባለበት ተገለጠላቸው ስለምን ቢሉ..

#ካልዳሰስኩ_አላምንም_ያለ_ሐዋርያው_ቶማስን_ሊያሳምነው

ቶማስን ደቀመዛሙርቱ መጥተው ጌታችንን በመካከላችን ተገልጦ አየነው ብለው ሲነግሩት ‹‹የችንካሩን ምልክት በእጄ ካላየሁ ጣቱንም ወደ ተቸነከረበት ካልጨመርሁ እጄንም ወደ ጎኑ ካላገባሁ አላምንም ›› ብሎ ነበርና ና ንካኝ ብሎ አሳምኖታል፡፡ቶማስ ለምን ተጠራጠረ ብንል ሰዱቃውያን ወገን ስለነበረ ነው፡፡ ሰዱቃውያን ትንሳኤ ሙታን የለም ብለው ያምናሉ /በማቴ.ወ22፤23-33/ ሃይ.አበው 48፤8-13 ገጽ255/ እርሱም ከሞት በኋላ ሕይወት አለ ብሎ አያስብም ነበር፡፡

የጌታችንን ጎን የነካች የቶማስ እጅ በኋላ ላይ ሳትበሰብስ በሕያውነት ለብዙ ዘመናት ኖራለች፡፡ሀገረ ስብከቱና ሰማዕትነት በተቀበለባት በሕንድ ሀገር ከታቦት ጋር ከመንበሩ ላይ ያኖሯት ነበር፡፡በዓመት በዓመት በእመቤታችን በዓል በአስተርዕኦ ሊያጥኑ ሲገቡ የሚሾመውን ወጥታ ቀኝ እጁን ትይዘዋለች ዓመት አገልግሎ ያርፋል በዓመቱ ሊያጥን ሲገባ ትይዘዋለች እንዲህ እያለች ትኖራለች፡፡

ሌላው ቶማስን ‹‹ ና ጎኔን ንካ›› ሲለው በኋላ በዓለም ዞሮ ወንጌልን የሚሰብክ ነውና ሐዋርያ ከሆነ ዘንድ ደግሞ ‹‹ሐዋርያት እንዳሉት ጌታችን ተነስቷል›› ብሎ ያስተምር ዘንድ አይገባውም ይልቁንም እንደ ወንጌላዊው ዮሐንስ ‹‹በጆሮአችን የሰማነውን በዓይኖቻችንም ያየነውንን የተመለከትነውን እጆቻችን የዳሰሱትን እንነግራችኋለን ሕይወት ለእኛ ተገልጻለችና አየናት›› 1ኛዮሐ1፤1-2 እንዳለው ቶማስን ና ንካኝ ብሎታል፡፡በእርግጥ ‹‹ሐዋርያት እንዲህ አለ›› ብሎ ማስተማር ስህተት ሆኖ አይደለም ምክንያቱም እነ ጳውሎስ ጌታችን ሲነሳ አላዩም ግን እንደ ሐዋርያት በዓለም ወንጌልን አዳርሷል ፡፡ነገር ግን ቶማስ ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ ስለሆነ ግድ ሆኖበታል፡፡

#ሰንበትን_ሲያጸናልን

የክርስቲያኖች ሰንበት የምንላት ዕለተ እሑድ ጌታችን ሞትን ድል አድርጎ የተነሳባት በመሆኗ የእረፍት የመንግስተ ሰማይ አምሳል ብለን እናከብራታለን፡፡ የዕለቲቱንም ክብርትነት እንድናስብና ዕለተ እሑድ በመጣች ቁጥር ጌታችን የተነሳባትና ለሐዋርያቱ ትንሳኤውን ደግሞ የገለጠባት እንደሆነ እንድናስብ ለአክብሮተ ሰንበት ደግሞ ተገለጠላቸው፡፡አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ‹‹የእሑድ ቀን የክርስቶስ ቀን ናት እሑድ ሰንበትም ተባለች›› መጽ.ምስ ገጽ296

#ትንሳኤው_ምትሐት_እንዳልሆነ_ለማስረዳት

ጌታችን ራሱ የተገለጠበትን ዓላማ ሲነግራቸው ‹‹እጄን እግሬን እዩ ዳስሱኝም እኔ እንደሆንኩ ዕወቁ በእኔ እንደምታዩት ለምትሐት አጥንትና ሥጋ የለውምና›› ሉቃ24፤39 እንዳላቸው የጌታችን ትንሳኤ ምትሐት ያይደለ አማናዊ በቀደመው ተዋሕዶ ባለመለወጥ እንደተነሳ ለማጠየቅ ተገለጠላቸው፡፡ሲገለጥም በተዘጋ ግንብ መግባቱ መለኮት አለመለየቱንና ወደ ሥጋ መለወጥ እንዳላገኘው ያስረዳል፡፡

በረከተ ትንሣኤውን ያሳድርብን
ሀገራችንን ሰላም ያድርግል


https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede
699 views£itsum, edited  17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 20:45:57
ዳግም ትንሣኤ

ወእምድኅረ ሰሙን መዋዕል እንዘ ሀለዉ ካዕበ አርዳኢሁ ውስጠ ወቶማስኒ ሀሎ ምስሌሆሙ እንዘ ዕጽው ኆኅት መጽአ እግዚእ ኢየሱስ ወቆመ ማእከሎሙ ወይቤሎሙ፦
ሰላም ለክሙ።
ዮሐንስ ፳:፳፮


https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede
695 views£itsum, edited  17:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 11:07:27 --------- ቅዳሜ † ቅዱሳት አንስት --------
ክርስቶስ ተንስአ እሙታን ……… በዓቢይ ኃይል ወስልጣን
አሰሮ ለሰይጣን ………….አግአዞ ለአዳም
ሰላም ………………………እም ይእዜሰ
ኮነ………………………………ፍስሐ ወሰላም
••••••••••••••••••• † •••••••••••••••••
ከትንሳኤ በኋላ ያለው እለተ ቅዳሜ ቅዱሳት አንስት ተብሎ ይጠራል። ይህም ስያሜ በስቅለት ዕለት በልቅሶና በዋይታ የሸኙትን ፤ (ሉቃ. ፳፫፥፳፯) በዕለተ ትንሣኤ ሽቱና አበባ ይዘው ወደ መቃብር የገሰገሱትን ፤ ከሁሉም ቀድሞ ጌታችን በዕለተ ሰንበት ተነሥቶ ለተገለጸላቸው ማርያም መግደላዊት ፤ የታናሹ ያዕቆብ እና የዮሳ እናት ማርያም፤ የዘብዴዎስም የልጆቹ እናት ሰሎሜንም መታሰቢያ ለማድረግ ነው። ከዚህ ባለፈም የቅድስና ስራ የሰሩ ሴቶች ሁሉ በዚህ ዕለት ይታሰባሉ።

«ከሳንምንቱ በመጀመሪያዩቱ ቀን ያዘጋጁትን ሽቶ ይዘው እጅግ ማልደው ወደ መቃብሩ ሄዱ ፤ ሌሎች ሴቶችም አብረዋቸው ነበሩ (ሉቃ. ፳፬ ፥ ፩ )፡፡ በዚህም ምክንያት ቤተክረስትያናችን ዕለቱን ቅዱሳት አንስት ብላ ሰይመዋለች።

ከትንሳኤውም በፊት ከትንሳኤውም በኋላ የሴት ቅዱሳንን የፅድቅ ስራ በዚህ እለት እንዘክራለን። ሴት ቅዱሳን ከትንሣኤ እስከ መስቀል ፍለጋ ድረስ የፅድቅ ስራቸው ሲታወስ ይኖራል።

በመጀመሪያዋ ሔዋን ሞት መጣ ፤ በሁለተኛዋ ሔዋን በድንግል ማርያም አለም ዳነ። የመጀመሪዋ ሔዋን የሞትን ዜና በጆሮዋ ሰማች ፤ እናታችን ድንግል ማርያም ጸጋን የተመላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ የሚለውን የቅዱስገብርኤልን ብስራት ሰማች። የአለም መድኃኒት ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሰው ሆነ። መድኃኔዓለም ከዳዊት ልጅ ከሴት ተወለደ። ለፍጥረቱ መዳን ተራበ ፥ ተጠማ ፥ መከራን ተቀበለ ፤ ስጋውን ቆረሰ ደሙን አፈሰሰ። በመስቀል ተሰቅሎ ሞተ ፣ ሞትንም ድል አድርጎ ተነሳ!

ቅድስት መግደላዊት ማርያም የጌታን ትንሳኤ ለመመስከር ተመረጠች። ለሐዋርያት ለአለም ትንሳኤውን አበሰረች። ከፈርኦን አምልጠው የኤርትራን ባህር ሲሻገሩ የሙሴ አህት ማርያም ከበሮ አንስታ እንደ ዘመረች ዛሬም የቅድስት መግደላዊት ማርያምን የትንሣኤ ብስራት የሰሙ ሴቶች 'ንሴብሆ' ብለው እየዘመሩ ትንሣኤውን ለአለም ያበስራሉ።

የመስቀሉ ፍቅር ከሁሉ የበዛላት ቅድስት እሌኒ በግፍ ተቀብሮ የኖረውን መስቀሉን አገኘች። የመስቀሉን ዜና ለአለም አበሰረች።

በዚህ እናትነት በዚያ ቅድስና ሰማዕትነት ምንኩስና ድንግልና ለሴቶች የተሰጠ ድንቅ የፈጣሪ ስጦታ ነው።
ቅዱሳኑ ሁሉ የእናቶቻችን ፍሬ ናቸው። ነብያት ፣ ሐዋርያት ፣ ጳጳሳት ፣ ሰማዕታት ፣ ደናግል ፣ መነኮሳት ፣ ቅዱሳን ከእናቶቻችን ተገኙ። ከእናትነት አልፈው ቅድስት ፣ ሰማዕት ፣ ደናግል ፣ መነኮሳያት ለመሆን የተመረጡ እናቶች በአለም እጅግ ብዙ ናቸው፡፡ እናታችን ቅድስት እሌኒ ፣ ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ፣ ቅድስት መስቀል ክብራ……..እናትነትን ከቅድስና ጋር ያስማሙ ናቸው። ከሰማዕታት የትውልዱ መመኪያ እናታችን ቅድስት አርሴማ አንዷ ናት። ሌሌችም ብዙ....ቅድስት ዲቦራ ፣ ቅድስት ሶፍያ...

በመጀመሪያዋ ሔዋን ሞት መጣ፣ በሁለተኛዋ ሔዋን በድንግል ማርያም አለም ዳነ! ዛሬም አለም ያለ ድንግል ማርያም አይድንም! በጥንት ዘመን እንደ ጥፋተኛ ይታዩ የነበሩት ሔዋኖች በሙሉ በድንግል ማርያም እንባቸው ታበሰ! ለምን? የፍጠረት ሁሉ መመኪያ ድንግል ማርያም ስለሆነች። የሁሉን መጋቢ ጡቶቿን አጠባችው። ሁሉን የያዘውን በክንዶቿ አቀፈችው ፤ በጀርባዋ አዘለችው። ፍጥረት በፊቱ መቆም የማይችለውን ሳመችው። እንዲሁም አለም በተስፋ የሚጠብቀውን ዳግም ምጽዓት ሳትጠብቅ ድንግል ማርያም ከሞት ተነስታ አርጋለች።

ከጌታ ትንሣኤ በኋላ ባለው በዚህ በዕለተ ቅዳሜ የቅድስና ስራ ያላቸው ሴቶች በሙሉ ይታሰባሉ። ተዋህዶ ለሴቶች ክብር እንደሌላት የሚናገሩ ሁሉ የሴቶች ቀን ከመከበሩ አስቀድማ ቤተ ክርስቲያናችን የቅዱሳን ሴቶች መታሰቢያ ዕለት አላት።

ዛሬስ? የእመቤታችን ሴቶች ልጆች ህይወታችሁ ማንን ይመስላል? የእመቤታችንን እውነተኛ ልጆች ህይወታችሁ እንዲሆን ቃልኪዳኗ ይርዳን ይርዳችሁ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር



https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede
1.4K views£itsum, edited  08:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 21:23:43 የንስሐ ትምህርት ለ45 ቀናት በተከታታይ

  እሄን  ትምህርት በደንብ ተማሩት   ብዙ ለውጥ  እንደ እግዚአብሔር ፍቃዱ ታመጣላቹው በዚህ 45 ቀን  ውስጥ በደንብ ተምረን እራሳችንን መለወጥ አለብን  ከዛም መንፈሳዊ ጉዞ እናደርጋለን።  ለዛም ተዘጋጀው ዝም ብሎ ሰውን ሁሌም ከመጠየቅ  እራስን ማስተማር የተሻለ ነው።
የእኔን መንፈሳዊ ሕይወት የቀየረ ትምህርት እናተም የማትቀየሩበት  ምንም ምክንያት የለም።  ብቻ 45 ቀን ብቻ  ስጡኝ።

እግዚአብሔር ያክብረልኝ

፩  ንስሀ ምንድን ነው?

ንስሀ፦ነሰሐ ከሚል የግዕዝ ግስ የወጣ  ቃል ነው።የቃሉ ፍቺ ሐዘን፣ ፀፀት፣ ቁጭት፣ ምላሽ፣መቀጮ፣ቅጣት፣ቀኖና፣የኃጢያት ካሣ ማለት ነው።

(የአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት)አንድ ሰው ንስሐ ገባ ሲባልም ዐዘነ፣ተፀፀተ፣ክፉ አመሉን ተወ፣ጠባዩን ለወጠ ማለት ነው...ሙሉውን ለማንበብ



https://t.me/+1LcnvYVTKTxhYjNk
https://t.me/+1LcnvYVTKTxhYjNk
637 viewsዲያቆን አቤንዔዘር ሙሉ, 18:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 20:47:26
#አፍሮ_አይገባ_መስቀል!  ከንጹህ ወርቅ የተሰራ ሲሆን ሰባት ኪሎ አካባቢ ይመዝናል፡፡ በብቸኝነት የሚገኘው ከላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት በግዝፈቱ ቀዳሚ በሆነው በቤተ መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነው። መስቀሉ አፍሮ አይገባ የሚለውን ስያሜ ያገኘው “የተጣሉትን በማስታረቅ፣የታመሙትን በመፈወስ” በሚፈጽመው ተዓምር ነው፡፡ አፍሮ አይገባ በ1989 ዓ.ም. ተሰርቆ ወደ ቤልጅየም ተወስዶ ነበር፡፡ ከሁለት ዓመት በኋላ ግንቦት 21 ቀን 1991 ዓ.ም  በከፍተኛ ጥረት ከቤልጅየም ወደ ኢትዮጵያ ተመልሶ በነበረበት መቅደስ ለመቀመጥ ችሏል፡፡

https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede
841 views£itsum, edited  17:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 18:14:39
"ሚሊየን መፅሀፍ የተሸከመች አህያ ያው አህያ ናት አትማርም፤ ሚሊየን አመት ውቅያኖስ ውስጥ የኖረ ድንጋይ ያው ድንጋይ ነው አይዋኝም!!!"

ይሄን ምን አሳሰበኝ ሁለት፣ ሶስት ዲግሪ ጭነው፣ ተምረው ተመራምረው፣ እልፍ መፅሀፍ አንብበው፣ ራሳቸው ፅፈው አሳትመው፣በየዩኒቨርሲቲው እና በሚዲያ ሌክቸር ሰጥተው፣ ነገር ግን እውቀት አእምሯቸውን ጥበብ ልባቸውን ያልነካው፣ በጥላቻ የተሞሉ፥ ለወንድሞቻቸው እንጥፍጣፊ ፍቅር የሌላቸው፣ የተማሩ መሳይ ቅብ-ምሁር፥ ፋቅ ፋቅ ቢያደርጓቸው ድንቁርናቸው ያገጠጠ፥ ፊደል እንጂ ጥበብ ያልቆጠሩ የትውልድ ሸክሞች ናቸው።
 
( Book for ALL facebook page )

~ዲያቆን ፍፁም ከበደ~


Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede
1.2K views£itsum, edited  15:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ