Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የሰርጥ አድራሻ: @orthodoxamero
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 44.89K
የሰርጥ መግለጫ

ዲያቆን ፍፁም ከበደ
ሀሳብ ካሎዎት @Fisumkeb
facebook Link...
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-06-08 19:04:19 ለልጅዎ የግእዝ ስም ማውጣት ከፈለጉም እነሆ
ግእዝ__አማርኛ
፩) መዓርዒር__ጣፋጭ
፪) አሜር__ፀሐይ
፫) አርያም_ሰማይ
፬) አምኃ_እጅ መንሻ
፭) ብሥራት___የምስራች
፮) ሰሎሜ_ሰላም
፯) አሜን__እውነት/ይሁንልኝ
፰) ሠዊት__እሸት
፱) ጸገየ___አበበ
፲) አስካል____ፍሬ
፲፩) ልዑል____ከፍ ያለ
፲፪) ሣህሉ____ይቅርታው
፲፫) ቀጸላ_አክሊል
፲፬) ሐመልማል___የለመለመ
፲፭) ከሃሊ_የሚችል ቻይ
፲፮) ጸዳሉ_መብራቱ
፲፯) ፈትለ ወርቅ____የወርቅ ፈትል
፲፰) ፊደል_ፊደል
፲፱) ማኅተም____ማተሚያ
፳) ሥዩም__የተሾመ ሹም
፳፩) ስብሐት____ምስጋና
፳፪) ስቡሕ_ምስጉን
፳፫) ተቅዋም_መቅረዝ
፳፬) ንጹሕ_የነጻ
፳፭) ሰላማ__ሰላም
፳፮) አዳም__ያማረ
፳፯) ዳግም_የደገመ
፳፰) ግሩም_ተፈሪ
፳፱) ጥዑም____የሚጣፍጥ
፴) ፍጹም__የተቀባ
፴፩) ይኄይስ____ተሻለ
፴፪) ሐዳስ/ሐዲስ___አዲስ
፴፫) ሕዳሴ__መታደስ
፴፬) ሰንኮሪስ_መምህር
፴፭) መቅደስ_ማመስገኛ
፴፮) ሞገስ__ባለሟል የተወደደ
፴፯) ትዕግሥት_መቻል
፴፰) ንጉሥ__የነገሠ
፴፱) ወራሲ__ወራሽ
፵) ውዳሴ__ምስጋና
፵፩) ጌራወርቅ____የወርቅ ሥራ
፵፪) ማኅደር_ማደሪያ
፵፫) ምሕረት_ይቅርታ
፵፬) መሓሪ__ይቅር ባይ
፵፭) ሠምረ__ወደደ
፵፮) ሥሙር_ተወዳጅ
፵፯) ሥምረት____መወደድ
፵፰) ነጸረ__ተመለከተ
፵፱) ምሥጢሩ____ምሥጢሩ
፶) መራሒ____መሪ
፶፩) ፍሥሓ_ደስታ
፶፪) አእመረ____አወቀ
፶፫) አእምሮ____እውቀት
፶፬) ፍቅር__መውደድ
፶፭) ክቡር__የከበረ
፶፮) ደብሩ__ተራራው
፶፯) ተግባር_ሥራ
፶፰) ረቂቅ__ረቂቅ
፶፱) መብረቁ____መብረቁ
፷) ነጸብራቅ__ነጸብራቅ

፷፩) ይባቤ___እልልታ
፷፪) ጥበቡ___ብልሃቱ
፷፫) መሠረት__መሠረት
፷፬) ብሑት___ስልጡን
፷፭) ትሕትና___ትሕትና
፷፮) ተከሥተ__ተገለጠ
፷፯) ሃይማኖት_ሃይማኖት
፷፰) በየነ__ፈረደ
፷፱) መኰንን____ገዢ
፸) በጽሐ__ደረሰ
፸፩) መስፍን____የሚገዛ
፸፪) ምስፍና____ግዛት
፸፫) ክርስቲያን____ክርስቲያን
፸፬) ወሰን__ድንበር
፸፭) መዋዒ_አሸናፊ
፸፮) ትንሣኤ_መነሳት
፸፯) ነቅዐ ሕይወት_የሕይወት ምንጭ
፸፰) ገዛኢ__ገዢ
፸፱) ምሕርካ ክርስቶስ___የክርስቶስ ምርኮ
፹) ባራኪ____የሚባርክ
፹፩) መልአክ____አለቃ
፹፪) በረከት____በረከት
፹፫) ህላዌ_መኖር
፹፬) ኂሩት_ቸር የሆነች
፹፭) ልባዌ_ማስተዋል
፹፮) ቤዛዊት_ያዳነች የምታድን
፹፯) ስርጋዌ____ሽልማት
፹፰) ስርጉት____የተሸለመች
፹፱) ተስፋ_ተስፋ
፺) ኬንያ__ብልሃተኛ
፺፩) ኖላዊ__ጠባቂ
፺፪) መርዓዊ____ሙሽራ
፺፫) ማዕዶት____መሻገሪያ
፺፬) ወልታ____መከታ/ጋሻ
፺፭) ሐዋዝ____ያማረ
፺፮) ግእዛን____ነጻነት
፺፯) ሕሊና____ሕሊና
፺፰) ማኅሌት____ምስጋና
፺፱) ኅሩይ__ምርጥ
፻) ሲሳይ__ምግብ
፻፩) ሠናይ____ያማረ
፻፪) ፈታሒ____የሚፈርድ
፻፫) ሐሴት____ደስታ
፻፬) ትርሲት_ሽልማት
፻፭) ተዋናዪ_ተጫዋች
፻፮) ዐቢይ___ከፍ ያለ
፻፯) ትውፊት_ስጦታ
፻፰) ኃያል_የበረታ
፻፱) ጽጌ__አበባ
፻፲) ፍሬሕይወት____የሕይወት ፍሬ
፻፲፩) ምዕዳን_ምክር
፻፲፪) ንኡድ___ያማረ
፻፲፫) ነገደ___ሄደ
፻፲፬) ነጎድጓድ____ነጎድጓድ
፻፲፭) ጸዓዳ_ነጭ
፻፲፮) ሠረጸ_በቀለ
፻፲፯) ደምፀ____ተሰማ
፻፲፰) ሮሐ_ወለወለ/አራገበ/አናፈሰ
፻፲፱) ናርዶስ_ሽቱ
፻፳) እፀ ሕይወት___የሕይወት እንጨት

በትረማርያም አበባው (በነገራችን ላይ በትረ ማርያም ማለት የማርያም ወገን ማለት ነው። በትር ወገን ተብሎ እንደሚተረጎም አስተውል)


በትረማርያም አበባው
2.8K views£itsum, edited  16:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 22:41:59 +++ የጀማሪ ጠባይ +++

መንፈሳዊ ሕይወትን ገና ስትጀምረው ለፍጹምነት ጥቂት የቀረህ ያህል ይሰማሃል። አንተ ጋር ያለው ደስታ እና ሰላም ሌሎች ጋር የሌለ ይመስልሃል። በዚህች ሁከት በሞላባት ዓለም አንተ ብቻ ክርስቶስን እንዳገኘኸው ታስባለህ። የቀረው ሕዝበ አዳም እንዲሁ በከንቱ ሲርመሰመስ የሚውል ባካና ሆኖ ይታይሃል። ታዝንለታለህ፣ አይይይ ይህ ኃጢአተኛ ሕዝብ ምን ይሻለዋል? ትላለህ።

የእውነተኛ መንፈሳዊ እድገት መገለጫ ግን ይህ አይደለም። ሰው ወደ እግዚአብሔር እየቀረበ ሲመጣ ከሌላው ሰው ይልቅ የራሱ ጉድለት ይታየዋል። መንፈሳዊነት የሚገልጥልህ ሰዎችን ተመልክተህ የምትፈርድበትን ውጫዊ ዓይንህን ሳይሆን ራስህን አይተህ የምትወቅስበት የውስጥ ዓይንህን ነው። መንፈሳዊ ሕይወትህ ሲጎመራ "አይ ሰው" ሳይሆን "አይ እኔ!" ያሰኝሃል። አባ ማቴዎስም እንዲህ ይላል "ሰው የበለጠ ወደ እግዚአብሔር ሲቀርብ ይበልጥ ኃጢአተኛ መሆኑ እየታየው ይመጣል። ነቢዩ ኢሳይያስ እግዚአብሔርን ካየ በኋላ ከንፈሮቼ የረከሱብኝና የጠፋሁ ሰው ነኝ እንዳለ።"

ከብቃት ደርሰህ መላእክት ሲወጡና ሲወርዱ ቢታዩህ እንኳን ሁሉ እንዳንተ ስለሚመስልህ እንደ ዮሐንስ ሐጺር "ሚካኤል ይበልጣል ወይስ ገብርኤል?" እያልህ ከአጠገብህ የቆመውን ትጠይቃለህ እንጂ "አይይ አንተ እንኳን ገና አልበቃህም። ብዙ ይቀርሃል" ብለህ ወዳጅህን አታናንቅም። ይልቅ "ለእኔ ብቻ ገልጦ ለሌላው እንዲሰውር የሚያደርገው ምንም ቁም ነገር የለኝም" በማለት ከወንድምህ የተሻልህ እንዳልሆንክ በፍጹም ልብህ ታምናለህ።

ለመንፈሳዊ ሕይወት አዲስ ስትሆን ገና ጥቂት ጸልየህ፣ ጥቂት ጾመህ፣ ጥቂት መጽውተህ ሳለ ግን ሩጫህን ወደ መጨረሱ የተቃረብህ ይመስልሃል። ጉዞህን በግማሽ እርምጃ ከመጀመርህ ከፍጻሜው ላይ የደረስህ ያህል ይሰማሃል። "እኔን ምሰሉ" ማለት ያምርሃል። ነገር ግን መንፈሳዊ ሕይወት የቱንም ያህል ብትሮጥበት ሁል ጊዜ እንደ ጀማሪ የሚያደርግ ረጅም ጎዳና ነው። ሰማንያ ዓመት በገዳም ሲጋደል የነበረው አባ ሲሶይ ነፍሱ ከሥጋው ልትለይ በቀረበች ጊዜ ብዙ መነኮሳት በአልጋው ዙሪያ ከበውት ሳለ ቅዱሱ "አምላኬ ሆይ፣ እባክህ ለንስሐ የሚሆን ጥቂት ጊዜን ስጠኝ?" እያለ በልቅሶ ሲማጸን ሰሙት። በዚህ የተገረሙት መነኮሳቱ አባ ሲሶይን "አባታችን አንተ እድሜ ልክህን በንስሐ የኖርህ መምህረ ንስሐ ሆነህ ሳለ እንዴት አሁን ጥቂት የንስሐ ጊዜን ትለምናለህ?" ቢሉት፣ ቅዱሱም "ልጆቼ ይህን መንፈሳዊ ጥበብ (ንስሐን) ገና አሁን መጀመሬ ነው" አላቸው።

ጌታ ሆይ መንፈሳዊ ሕይወት እኖር ዘንድ አስጀምረኝ፤ ገና ጀማሪ ሳለሁ ደርሻለሁ ከማለትም ሰውረኝ። እንድቆም አትፍቀድልኝ፤ ወደ አንተ ሳበኝ፣ አሳድገኝ።



ዲያቆን አቤል ካሳሁን
3.0K views£itsum, 19:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-06 08:55:00 ➦ የሰኔ ጾም የቄሶች ጾም ነውን
➦ የ2014 ፆመ ሐዋርያት(የሰኔ ፆም) መቼይገባል
➦ ለምንስ ይፆማል
➦ የሰኔ ፆም የሚጾምበት ጊዜያት
➦ ፆመ ሐዋርያት ለምን የቄሶች ፆም በመባል ይጠራል
➦ በሰኔ ፆም ሐዋርያት ሲፆሙ ይጠቀሙበት የነበረው ህግ ምን ነበረ
➦ ፆመ ድኅነት ከትንሳኤ እስከ ጰራቅሊጦስ ለምን አይጾምም ......ሙሉውን መልስ ለማግኘት

አስገራሚ ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፎችን ፣ ምክረ አበው ፣ ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን የምትማሩበት በአንድ ዓመት ብቻ ከ62,000 ተማሪዎችን ያፈራውን ቻናል ለመቀላቀል!!
                         
https://t.me/+7Itsth8QSrY2Y2Q0
https://t.me/+7Itsth8QSrY2Y2Q0

            𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘  
የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር
ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍ በPDF
       ኦርቶዶክሳዊ ግጥም
          የግእዝ ትምህርት
           𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘 ‌‌
3.2K viewsዲያቆን አቤንዔዘር ሙሉ, 05:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 18:08:18
#መልካም ዜና
የቤተ ክርስቲያን እውነተኛ አባት የሆኑት ግፈኛው ግዞተኛ መ/ር ኃይለ ማርያም በ20 ሺ ብር ዋስትና እንዲለቀቁ ፍርድ ቤቱ በዛሬው እለት ውሳኔ አስተላልፏል።
3.5K views£itsum, edited  15:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 12:54:09 #ጾመ ሐዋርያት

#በወርኃ ሰኔ የሚጾም በመሆኑ ይህ ጾም በተለምዶ የሰኔ ጾም በመባል ይታወቃል፡፡ ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ለስብከተ ወንጌል ከመሰማራታቸው በፊት የጾሙት ጾም ነው፡፡ ጾመ ሐዋርያትን ለመጀመሪያ ጊዜ የጾሙት ቅዱሳን ሐዋርያት ሲሆኑ የጾሙበትም ዋና ምክንያት በሃምሳኛው ቀን ሀብተ መንፈስ ቅዱስ ስለተቀበሉና እግዚአብሔር ስላደረገላቸው መልካም ነገር ለማዘከር ነው፡፡

ጾመ ሐዋርያት በዓለ ጰራቅሊጦስ በመጀመሪያው ሰኞ ይውላል፡፡ ጌታችን አምላካችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌው ደቀ መዛሙርቱን ይህን ጾም እንደሚጾሙት እንዲህ ተናግሮ ነበር፡፡ ‹‹በዚያን ጊዜ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ወደ እርሱ ቀርበው። ‹‹እኛና ፈሪሳውያን፥ ብዙ እንጾማለን፥ ደቀ መዛሙርትህስ ለምን አይጾሙም? አሉት፡፡›› (ማቴ.፱፥፲፬) ደቀ መዛሙርቱ ይህንን በጠየቁት ጊዜ ጌታችን እንዲህ ብሎ መልሶላቸው ነበር፡፡ ‹‹ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፤ የሙሽራው ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ አይችሉም፤ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፤ ያንጊዜም ይጾማሉ፡፡›› (ማቴ.፱፥፲፭)

በቅዱሳን ሐዋርያት ላይ ያደረው ጸጋ መንፈስ ቅዱስና ሀብተ መንፈስ ቅዱስ በእኛም ላይ እንዲያድር፣ ከቅዱሳን ሐዋርያቱ በረከት እንድንሳተፍ፣ አገልግሎታችን በስኬት እንዲቃና እና ወርኃ ክረምቱ በሰላም ያልፍልን ዘንድ ጾመ ሐዋርያትን መጾም አስፈላጊ ነው፡፡ ከጸሎትና ምጽዋትን መንፈሳዊ እድገትን በጾም አስምረን ከራሳችንን እና ከእግዚአብሔር አምላካችን ጋር የምንታረቅበት እንዲሆንልን የቅዱሳን አባቶቻችን ሐዋርያት በረከትና ጸሎትም አይለየን፡፡

የአምላካችን እግዚአብሔር ቸርነት፣ የቅድስት ድንግል ማርያም እና የቅዱሳን ሐዋርያት አማላጅነትና ተራዳኢነት አይለየን፤ አሜን!
#ከማሕበር ቅዱሳን ቴሌግራም የተወሰደ!!
4.2K views£itsum, 09:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-04 17:17:14
3.7K views£itsum, 14:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-04 17:04:00
የቦሩ ሜዳ ደብረ ብርሃን ሥላሴ እና የደብረ ታቦር ደ/ልዑላን መድኃኔ ዓለም ጉባኤ ቤቶች 49 ደቀ መዛሙርቶቻቸውን አስመረቁ።

ቦሩ ሜዳ ደብረ ብርሃን ሥላሴ 27 ማለትም 10 የብሉይ ኪዳን፣ 17 ሐዲስ ኪዳን መምህራን ብፁዕ አቡነ አትናቴዎስ የደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት፣ ሊቀጳጳስ እና የሀገረ ስብከቱ ልዩ ልዩ የመምሪያ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

ደብረ ታቦር ደ/ልዑላን መድኃኔ ዓለም የካቲት 25/2011 ለመጀመሪያ ጊዜ ያስተማራቸውን 22 መምህራንን ብፁዕ አቡነ ሚካኤል የደ/ጎንደር ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት አስመርቋል።

በትናንትናው ዕለትም ተመራቂዎቸ ለመመረቂያ ሃይማኖታዊ ፍልስፍና እና ውዳሴ ማርያም በመጽሐፍ ቅዱስ የሚሉ ጥናታዊ ጽሑፎች አቅርበዋል።

የደብረ ታቦር ጉባኤ ቤት ጉባኤውን ለማስፋፋትና ለማጠናከር ኘሮጀክት ቀርጾ እየሠራ በመሆኑ ሁሉም የበኩሉን አስተዋጽዖ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።።
3.5K views£itsum, 14:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-04 14:58:29
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ አሁንም ግፍን እያወገዙ ነው።

ቅዱስነታቸው በተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች አቡዳቢ ደብረ ሰላም መድኃኔ ዓለም የመቃረቢያ ቤተ ክርስቲያን የምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ በአስተላለፋት አባታዊ መልእክት ላይ እንዲህ ብለዋል።

". . . [ልጆቻችን] እናት ዕድለኞች ናችሁ። ለዚህም እግዚአብሔርን ልታመሰግኑ ይገባል። [ይህ] አሁን በሀገራችን ካለው የተለየ ነው። በሀገራችን ያሉት [ልጆቻችን] ይህን ዕድል አላገኙም። [እነርሱ] ዜግነታቸው፣ መብታቸውና ንብረታቸው ሁሉ ተወስዷል። የማይገባ ሥራ እየተሠራ ነው። ተገቢም ያልሆነ ነገር እየተሠራ ነው። የሰው ሀገር መቶ ፕርሰንት ይመቻል ባይባልም፤ እናተ ግን በሰው ሀገር በጃችሁም አልበጃችሁም ቢያንስ በሰላም ትኖራላችሁ ። ይህ ልዮነት የለውም ? እኛ እንኳን በሀገራችን ሁሉ ተውስዶብናል። መብቱ፣ ዜግነቱ፣ ሀብቱ፣ ንብረቱ ሁሉ ተወስዷል። ለምን ቢባል ማነው ተጠያቂው ? ማን ጠያቂ፤ ማን ተጠያቂ ይሆናል። በጭራሽ የሚቻል አልሆነም። . . . "

ግንቦት 25 ቀን 2015 ዓ.ም
በተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች አቡዳቢ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን


ዲያቆን ታደሰ ወርቁ
3.0K views£itsum, edited  11:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-04 01:13:15 እውነትም ድንቅ ልጅ "የቀደሙ አባቶች እጃቸው ታስረው ነበረ የሚሾሙት...ዘንድሮ ግን!

ኮሜዲያን እሸቱን ጭንቅላቱን ያስያዘው ድንቅ ኦርቶዶክሳዊ ልጅ

ግቡና እዩት SUBSCRIBE LIKE SHARE እንዳይረሳ የተዋህዶ ልጆች









2.3K viewsዲያቆን አቤንዔዘር ሙሉ, 22:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-03 13:16:53
“የሐሰት ምስክሮችና ዓመፀኞች ተነሥተውብኛልና ለጠላቶቼ ፈቃድ አትስጠኝ።”
— መዝሙር 27፥12

Facebooke link
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.keb
3.0K views£itsum, edited  10:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ