Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የሰርጥ አድራሻ: @orthodoxamero
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 44.89K
የሰርጥ መግለጫ

ዲያቆን ፍፁም ከበደ
ሀሳብ ካሎዎት @Fisumkeb
facebook Link...
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 49

2022-12-21 21:17:40 ~ ተአምረ ማርያም ያጽናናዋል ~


ተአምርዋን የሰማ ሥጋ ወደሙን እንደተቀበለ ይሆንለታል’ የሚለውን ቃል በመጥቀስ ‘እንዴት የክርስቶስ ሥጋና ደም ከተአምረ ማርያም ጋር ሊተካከል ይችላል?’ የሚል ጥያቄ ነው፡፡ ይህም ጥያቄ ከፕሮቴስታንት አቅጣጫ መነሣቱ በጣም አስገራሚ ነው፡፡ እኔ መረጃ አጥሮኝ ካልሆነ በቀር ከመቼ ወዲህ ነው አንድ ፕሮቴስታንት የሥጋ ወደሙ ተቆርቋሪ የሆነው? የአስተምህሮ ለውጥ ተደርጎ እንደሆነ አላውቅም፡፡ በብዙ ለዘመናት ጸንቶ እንደተቃወመው ግን ፕሮቴስታንቲዝም በክርስቶስ ሥጋና ደም አማናዊነት ጨርሶ አያምንም፡፡ ጌታችን ‘ይህ ሥጋዬ ነው ይህ ደሜ’ ነው ብሎ የሠጠውን ምሥጢረ ቁርባንም ‘አብሮ ከሚበላ የመታሰቢያ ማዕድነት ያለፈ ፋይዳ የለውም’ በሚል አቋም የፕሮቴስታንቱ ዓለም ከካቶሊክና ኦርቶዶክሱ ዓለም ጋር ሲሟገት የአምስት መቶ ዓመት ዕድሜውን እንዳሳለፈ ሁላችን የምንስማማባቸው የታሪክ መዛግብት ያስረዳሉ፡፡ እነርሱ እንደሚሉት ሥጋ ወደሙ ተራ የመታሰቢያ ማዕድ ከሆነ ደግሞ እውነትም ከመብላት መስማት የተሻለ ጥቅም አለውና ይህንን ቃል ሊቃወሙ የሚችሉበት መሠረት አይኖራቸውም፡፡

የተአምረ ማርያም መቅድም ግን ጉዳዩን የሚጀምረው ተአምርዋን መስማት ምንኛ ከሥጋ ወደሙ ያነሠ መሆኑን በመግለጽ ነው፡፡ ሰው ‘ሥጋውንና ደሙን ይቀበል ፤ ሥጋ ወደሙን ለመቀበል የሚከለክል የታወቀ ምክንያት ከገጠመው ግን ተአምርዋን ሰምቶ ይሒድ’ የሚለው ንግግር ሥጋ ወደሙን ለመቀበል የማይችል ሰው ተአምርዋን መስማት እንደሚችል ያስረዳል፡፡ ተአምረ ማርያም ከሥጋ ወደሙ እኩል ቢሆን ኖሮ ሰውዬውን ሥጋ ወደሙን ከመቀበል የከለከለው ምክንያት ተአምርዋንም ከመስማት ይከለክለው ነበር፡፡ ለምሳሌ ‘በአካል መጥተህ እንድታገኘኝ ነገር ግን በአካል ለመምጣት ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ባትችል ቢያንስ በስልክ ደውልልኝ ፤ ከደወልህልኝ እንደ መጣህ እቆጥረዋለሁ’ ብለህ ለወዳጅህ ነገርኸው፡፡ ይህ ዓረፍተ ነገር በአካል መምጣትና በስልክ መደወልን እኩል ያደርጋል ማለት አይደለም፡፡

በአጭሩ ዓረፍተ ነገሩ ሥጋ ወደሙን ዘወትር በመቀበል ሕይወት የሚኖርን ክርስቲያን የሚመለከት ቃል ነው፡፡ ይህ ክርስቲያን ፍጹም መንፈሳዊ ሕይወትን እየኖረ እንዳለ ምስክር የሚሆነው ሥጋ ወደሙን ከመቀበል የሚከለክለው ደዌ ወይም የታወቀ ምክንያት እንጂ አልቆርብም የሚል የኃጢአት ሰበብ አይደለም፡፡ እንዲህ ላለው ትጉሕ ቆራቢ ሰው ሁልጊዜ ወደ ቤተ ክርስቲያን እየገሠገሠ መቁረብ ልማዱ ነውና አስቀድሶ አለመቁረብም ኀዘን ይሆንበታል፡፡ ለዚህ ሰው መቅድመ ተአምረ ማርያም ያጽናናዋል፡፡ ‘የታወቀ ምክንያት ወይም ሕመም ስለከለከለህ ባለመቁረብህ አትዘን ቢያንስ ተአምርዋን ሰምተህ ሒድ ፤ በዚያ ዕለት ልትቆርብ ተመኝተሃልና ሰምተህ በመሔድህ ያን ቀን ብትቆርብ የምታገኘውን በረከት አላስቀርብህም’ ነው፡፡ ይህ ግን ንስሓ አልገባም አልቆርብም ተአምርዋን ሰምቼ ይበቃኛል የሚል ብልጣ ብልጥ ትዕቢተኛ ሰው የሚሠራ አይደለም፡፡ ምክንያቱም ይህንን ዓይነቱን ሰው ከመቁረብ የሚከለክለው ‘የታወቀ ምክንያት ወይም ደዌ ሳይሆን’ የኃጢአት ፍቅር ነው፡፡



ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

+ ተአምረ ማርያምና አንዳንድ ጉዳዮች +
(ክፍል አንድ)

የተወሰደ ።
2.0K views✞£iŧsûm✞, edited  18:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-21 19:24:16 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋር ያላትን ግንኙነት ልታቋርጥ እንደምትችል ገለጸች።

ታኅሣሥ 12 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ)

ከሰዓታት በፊት የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ወቅታዊ ጉዳይን አስመልክቶ እንደሚሰጥ መግለጻችን ይታወሳል። ነገር ግን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤትና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊና የኒውዮርክና አካባቢው አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ቢገኙም ጉባኤው ሳይካሄድ ቀርቷል።

ከመግለጫው መቅረት በኋላ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት ብፁዕ አቡነ አብርሃም እና ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ መግለጫ ሰጥተዋል።

የጉባኤውን መቅረት አስመልክቶ በትናንትናው ዕለት በተካሔደው በኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የቦርድ ስብሰባ ተገኝተው የነበሩት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ እንደገለጹት የውይይቱ አጀንዳ 'በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ እየተካሔደ ያለው ሃይማኖታዊ ማኅበራዊና ታሪካዊ ጥቃት ' በሚል እንደነበር የጠቀሱ ሲሆን በዛሬው ዕለት ታኅሣሥ 12 ቀን 2015 ዓ.ም በጉባኤው  በላይ ጠባቂ አባቶች በወቅታዊ ጉዳይ የሰላም ጥሪና መግለጫ እንዲሰጥ ወስነው እንደነበር አስረድተዋል።

ነገር ግን በዛሬው ስብሰባ ከኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ተወካይ  በቀር እስልምናን  ጨምሮ የማንም ቤተ እምነት ተወካዮችአልተገኙም። በዚህ ምክንያት መግለጫው ሳይሰጥ ቀርቷል ብለዋል።

አክለውም ይህ የቤተ ክርስቲያንን ኅልውና የሚፈታተን ሆኖ አግኝተነዋል ብፁዕ ሊቀ ጳጳሱ።

ብፁዕ አቡነ አብርሃም በበኩላቸው የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሥራው ሃይማኖቶች ሌላውን ሳይተቹ በጋራ በፍቅር ለአንዲት ሀገር የሚቆሙበትን መንገድ ለመፍጠር የእንደሆነ ጠቅሰው የተደረገው ድርጊት እንዳሳዘናቸው ገልጸዋል።

ቤተ ክርስቲያን ብዙ ፈተና ቢያደርሱባትም እንደእናት እየታገሰች እስከዛሬ ድረስ ጥራለች ሲሉም አክለዋል።

ሁሉም የሃይማኖት ተቋማት በአንድ አይነት ድምፅ ተናብበው በመቅረታቸው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ያዩበት ዐይን ጤናማ እንዳልሆነ ተገንዝበናልም ብለዋል።

በዚህ ሁኔታ የሚቀጥል ከሆነ ቤተ ክርስቲያን ከሀይማኖት ተቋማት ጋር ያላት ግንኙት ይቋረጣል።  ምክንያቱም የቤተ ክርስቲያንን ክብር ከምንም አላዩትም ያሉት ብፁዕ ሥራ አስኪያጁ ቤተ ክርስቲያን ሲፈልጉ የሚያከብሯት ሌላ ጊዜ ደግሞ የሚያዋርዷት ቤተ ክርስቲያን እንድትሆን አንፈልግም ሲሉም ጠቅሰዋል።

በመጨረሻሞ ወጣቶች ጉዳዩ ስሜታዊ ቢያደርግም ሰዎች በሚፈልጉት መንገድ እንዳንጓዝ ያስፈልጋል። ቤተ ክርስቲያን ጸብ እንድታጭር የሚፈልጉ አሉ ስለዚህም መጠንቀቅ ያሻል ሲሉም አሳስበዋል።

ምንጭ

ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል
እውነተኛ የተዋሕዶ ድምፅ
2.0K views✞£iŧsûm✞, 16:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-21 19:24:01
1.5K views✞£iŧsûm✞, 16:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-21 19:19:51 ሰይጣን አንዱን ኃጢአት ስልችት ብሎን ስንጠላውና ከዚያ ለመውጣትም ስንጣጣር ከተመለከተ አንድ የሚያከናውነው ስልት እንዳለው ሊቃውንት ይናገራሉ። ለምሳሌ ስድብ የሚያስቸግረው ሰው ቢኾንና ከዚህ መውጣት ቢፈልግ፥ ሰውዬው ሳይታወቀው የሚሳደብበትን መንገድ ያዘጋጅለታል። መንፈሳዊ ትምህርት እንዲማር፣ መንፈሳዊ መጻሕፍትን እንዲያነብ፣ ከሌሎች የበለጠ እንዲያውቅ ሹክ ይለዋል። ይህ ሰው መጀመሪያ ሲያስበው ከስድቡ የሚወጣበት መንገድ እንደ ኾነ ነው የሚታየው!

ችግሩም መማሩ፣ ማንበቡ፣ ይበልጥ ማወቁ አይደለም። ይልቅስ ስድቡን አሁን መንፈሳዊ ስድብ ያደርገዋል። ለሃይማኖቱ ቀንቶ፣ ምእመናን ከምግባር ድቀት እንዲወጡ ብሎ የሚያደርገው ስለሚመስለው የስድቡን ስም ቀይሮ "ተግሣጽ" የሚል ማዕረግን ይደርብለታል።

ራስን ማየት፣ የምንናገረው ነገር ስድብ ይኹን የእውነት ተግሣጽ ራስን መመርመር፥ ከዚያም መንፈሳዊ ሕክምና መውሰድ ሠናይ ነው።
1.5K views✞£iŧsûm✞, 16:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-21 17:28:36 አዲስ መንፈሳዊ ትረካ ሕማማት ክፍል 9 "የዮና ልጅ ስምዖን"











Subscribe like share ማድረግ እንዳትረሱ መንፈሳዊ ቻናሎችን እንደግፍ
1.2K viewsዲያቆን አቤንዔዘር ሙሉ, 14:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-21 17:28:36 አዲስ መንፈሳዊ ትረካ ሕማማት ክፍል 8 "እነዚህ ይሂዱ ተዉአቸው"











Subscribe like share ማድረግ እንዳትረሱ መንፈሳዊ ቻናሎችን እንደግፍ
391 viewsዲያቆን አቤንዔዘር ሙሉ, 14:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-21 07:36:18
#ቅዱስ_ሚካኤል_

#እንኳን_አደረሳችሁ  ታህሳስ  12

   #ሚካኤል ማለት በዕብራይስጥ ቋንቋ ሚ-መኑ' ካ-ከመ' ኤል- አምላክ ማለት ሲሆን በአንድነት ሲነበብ መኑ ከመ አምላክ (እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው) ማለት ነው፡፡ አንድም ለእግዚአብሔር አሸናፊ ድል አድራጊ የቸርነትና የርህራሄ መገኛ መዝገብ ማለት ነው፡፡

ቅድስት አፎምያን ቅዱስ ላሊበላ እና ባህራንን የረዳቸውና ያዳናቸው ቅዱስ ሚካኤል ክክፉ ሁሉ ይጠብቀን ከሚሰማውና ከሚታየው መከራ ይሰውረን ።

      #የቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት ከክፉ ሁሉ ይጠብቀን
ሊቀ መላእክት #ቅዱስ_ሚካኤል ከክፉ ሁሉ ይሰውራችሁ!!

~ዲያቆን ፍፁም ከበደ~
2.5K views✞£iŧsûm✞, edited  04:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-20 22:30:20 ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እየተፈጸመባት ያለው ሕገ ወጥ ድርጊት እልባት እንዲያገኝ ለሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት አቤቱታዋን አቀረበች።

ታኅሣሥ 11 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ)

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነትና ሥርዓቷ ላይ እየተፈጸመ ያለው ሁከት ቀስቃሽ ድርጊት በሕግና በሥርዓት እልባት እንዲያገኝ አቤቱታዋን ለሚመለከታቸው አካላት አቅርባለች።

ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ባገኘነው መረጃ መሠረት ቤተ ክርስቲያን የደረሰባትን በደል ለሰላም ሚኒስቴር ፣ ለኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን፣ ለኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ እንዲሁም ለኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ   በደብዳቤ እንዳሳወቀች ተገልጿል።

በተለይም ለኢፌዴሪ የመገናኛ ብዙኃን በጻፈችው ደብዳቤ በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ መሠረት ማንኛውም ሃይማኖት ተኮር ሚዲያ በሃይማኖቶች መካከል አለመቻቻል እንዲፈጠር የሚያደርግ መሆን እንደሌለበት ቢደነግግም ፓስተር ዮናታን አክሊሉና ነቢይ ኢዩ ጩፋ የተባሉ ግለሰቦች የቤተ ክርስቲያንን ክብር መንካታቸውና ስሟንም ማጉደፋቸው ተጠቅሷል።

በመሆኑም ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ጉዳዩን በአግባቡ አጢኖ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወስድና አስቸኳይ መፍትሔ እንዲሰጥ ጠይቃለች።


ምንጭ

ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል
እውነተኛ የተዋሕዶ ድምፅ
2.5K views✞£iŧsûm✞, 19:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-20 22:29:45
2.1K views✞£iŧsûm✞, 19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-20 21:47:44
~የእግዚአብሔር ሀብት ነውና አንሱት~

ወንድሞቼ! ከእናንተ መካከል አንድ ዐይነ ሥውር ሰው ወደ ጉድጓድ ገብቶ ሊወድቅ ሲል እጁን ዘርግቶ የማይደግፈው ማን ነው ? ታዲያ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በልቡናቸው ታውረው ወደ ሲዖል ጉድጓድ ለዘላለም ሲወድቁ እንድምን እጃችን የበለጠ አይዘረጋም ? ወገኖቼ! በነፍስም በሥጋም የታመመ ሰው ስታዩ " የእኔ ሥራ አይደለም፣ የቀሳውስቱና የመነኮሳት ሥራ እንጂ። " አትበሉ። አንድ ትልቅ በወርቅ የተሞላ ሳጥን ወድቆ ብታዩ " ይህ እኔን አይመለከተኝም ሌሎች መጥተው ያንሡት እንጂ " ትላላችሁን ? ግራ ቀኛችሁን አይታችሁ በፍጥነት የምታነሱት አይደለምን ? ይህ ወደ ዘላለም ጉድጓድ እየወደቀ ያለው ወንድማችሁም ከዚያ ወርቅ በላይ ውድ የእግዚአብሔር ሀብት ነውና አንሡት እንጂ የበለጠ እንዲወድቅ አትደግፉት።

    (~ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ~)

ሰማዕትነት አያምልጣችሁ
ተርጓሚ ገብረእግዚአብሔር ኪደ
2.4K views✞£iŧsûm✞, edited  18:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ