Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የሰርጥ አድራሻ: @orthodoxamero
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 49.24K
የሰርጥ መግለጫ

ዲያቆን ፍፁም ከበደ
ሀሳብ ካሎዎት @Fisumkeb
facebook Link...
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 46

2023-01-01 07:24:10
ከ60 second በኋላ ሰለሚጠፋ አሁኑኑ JOIN በማድረግ ተቀላቀሉ በቴሌግራም ምርጥ ከተባሉ ኦርቶዶክሳዊ የPDF መጽሐፎች መገኛ ቻናል ውስጥ አንዱ ነው በእርግጠኝነት ይወዱታል። ይቀላቀሉን
80 viewsዲያቆን አቤንዔዘር ሙሉ, 04:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-31 19:49:19 "የክርስቶስ በዓላት 9 ናቸው (አበይት በዓላቱን ማለቱ ነው)፤ የማርያም ግን 33 ናቸው። በምን ያህል እንደሚበልጡ እዩ ወገኖቼ . . ." ይላል አንዱ ፓስተር ዩቲዩብ ላይ። አቤት! ሕዝቡን እንዴት ነው የሚዋሹት?
ሰንበተ ክርስቲያን (የክርስቶስ ትንሣኤ መታሰቢያ በዓል) የማን በዓል ናት? በዓመት ስንት የሰንበት እሁዶች ይከበራሉ? (55) ንዑሳን የጌታ በዓላትስ? በዓመት ስንት በዓለ ወልድ ይከበራል? (12) አማኑኤል? ኢየሱስ?
ውይ! የጌታን በዓላት መቁጠር ጀመርን እንዴ? ወደ እነርሱ ስንፍና አስገቡን! የእመቤታችንን ጨምሮ የቅዱሳን በዓላት ያለ ቅዱስ ቁርባን ይከበራሉ? በፍጹም! ቅዱሳን ሁሉ በራሳቸው በዓላት እንኳ ክብራቸው በመሠዊያው ላይ የሚገለጠው ክርስቶስ መሆኑ ይታወቅ! ክርስቶስ የማይከብርበት የቅዱሳን በዓል የለም! አትዋሹ! ሕዝቡን በድንቁርና እና በውሸት ይዛችሁ መቀጠል የማትችሉበት ጊዜ መጥቷል። የክርስቶስን ቅዱስ ሥጋ እና ክቡር ደም ወደሚቀበልባት፣ ከቅዱሳን ጋር ኅብረት ወደሚፈጥርባት ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሚመለስበትን ጊዜ ብታስረዝሙት እንጂ አታስቀሩትም!
***
"የመንጋዬም ቅሬታ ካባረርኋቸው ምድር ሁሉ ወደ በረታቸው ሰብሰቤ እመልሳቸዋለሁ፤ እነርሱም ያፈራሉ ይበዙማል። የሚጠብቋቸውን እረኞች አስነሣላቸዋለሁ፥ ዳግመኛም አይፈሩምና አይደነግጡም፥ ከእነሱም አንድ አይጐድልም፥ ይላል እግዚአብሔር።" (ኤር. 23÷3-4)

~በረከት አዝመራው~

https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
1.2K viewsሞቱማ ቸርነት, edited  16:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-30 21:35:53 “ለሥዕሏ ያልሰገደ ከቆመበት ቦታ ይጥፋ” ይባላልን?

በአጭሩ ቤተ ክርስቲያን የአማኞች ስብስብ ናት ። በአማኞች ዘንድ ከእምነታቸው ጋር ኅብረት የሌለው ሰው ሲኖር ከጉባኤው መለየቱ የየትኛውም ኅብረት ጠባይ ነው። ይህ ደግሞ መሠረቱን የጣለው ገና ቀድሞ በብሉይ ኪዳኗ ጉባኤ ነው። ለምሳሌ ያህል “ማናቸውም ሰው ከዘራችሁ በትውልዳችሁ ርኵሰት እያለበት የእስራኤል ልጆች ለእግዚአብሔር ወደሚቀድሱት ወደ ቅዱስ ነገር ቢቀርብ፥ ያ ሰው ከፊቴ ተለይቶ ይጥፋ፤ እኔ እግዚአብሔር ነኝ” /ዘለ 22 ፤ 3/። “ከመጀመሪያውም ቀን አንሥቶ እስከ ሰባተኛው ቀን እርሾ ያለበትን እንጀራ የሚበላ ነፍስ ከእስራኤል ተለይቶ ይጥፋ” /ዘጸ 12 ፤ 15/። እንዲህ ያሉ ቃላትን እጅግ የብዙ ብዙ ሆነው እናገኛቸዋለን። በተለይ በኦሪቱ ተራ በሚመስሉን ነገሮች ሁሉ ከጉባኤው ተለይቶ ይጥፋ የሚለው ትዕዛዝ ተደጋግሞ ታዝዟል። ይህ የሆነበት ምክንያት የእግዚአብሔርን ጉባኤ ንጽሕና እና ቅድስና እንዲገባን እና በማንኛውም ሁኔታ ከጉባኤው የተለየ ሰው ካለ መለየት የሚገባው ስለሆነ ነው።

በሐዲስ ኪዳንም ቅዱስ ጳውሎስ “ይህን ሥራ የሠራው ከመካከላችሁ ይወገድ” /1ኛ ቆሮ 5 ፤2/። “በውጭ ባሉቱ ግን እግዚአብሔር ይፈርድባቸዋል። ክፉውን ከመካከላችሁ አውጡት” /1ኛ ቆሮ 5 ፤ 13/።ሲል ደጋግሞ የገለጸው በጉባኤው ውስጥ ልዩ እምነት ያለ ሰው ሁልጊዜም መለየት እንዳለበት የሚያመለክት ነው።

በተለይ ከነገረ ክርስቶስ ጋር በተገናኘ ማለትም ክህደቱ ወይም ኑፋቄው የክርስቶስን ቤዛነት የሚነካ ሲሆን በእጅጉ እንጸየፈዋለን። ከጥንት ጀምሮ ነገረ ማርያም እና ክብረ ድንግል ማርያም ላይ ጥያቄ የሚያነሱ ሰዎች ለጥያቄያቸው መነሻቸው ክርስቶስ ላይ ያላቸው እምነት ነው። ንስጥሮስ ወላዲተ አምላክ አትባልም ያለው ክርስቶስም አምላክ አይደለም ብሎ ስለሚያምን ነበር። ልክ እንዲሁ የእመቤታችን ሥዕል የሚጠሉት ሰዎች ክርቶስ ከእርሷ ሰው ሆኑ በእርሷ መልክዕ መገለጡን የማይረዱ ናቸው። እንዲህ ያለው ሰው ከቆመበት ይጥፋ የተባለው ያቀለለው የክርስቶስን መልክእ በመሆኑ ነው። የእመቤታችን ሥዕል በተለይም ምስለ ፍቁር ወልዳ (ከተወደደው ልጇ ጋር) የምንለው ሥዕል በቤተ ክርስቲያችን የሚኖረው ክርስቶስ ፍጡር ሳይሆን ሰው የሆነ አምላክ ነው። ሰው የሆነው ደግሞ የድንግልና ወተቷን እያጠጣች እንዲህ ታቅፋ ካሳደገችው ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ነው ለማለት ነው። ስለዚህ ለሥዕሏ ያልሰገደ ማለት ክርስቶስ ከእርሷ ሰው ሆኖ የተገለጠ አምላክ መሆኑን የማይቀበል ነውና ከጉባኤው ይለይ የተባለው ለዚህ ነው።

እንዲህ ያለውንማ ቅዱስ ዳዊትም እንዲህ ይለዋል። “የኃጢአተኛ አፍና የተንኰለኛ አፍ በላዬ ተላቅቀውብኛልና፤ በሽንገላ አንደበትም በላዬ ተናገሩ፤ በጥል ቃል ከበቡኝ፥ በከንቱም ተሰለፉብኝ። በወደድኋቸው ፋንታ አጣሉኝ፥ እኔ ግን እጸልያለሁ። በመልካም ፋንታ ክፉን፥ በወደድኋቸውም ፋንታ ጠላትነትን መለሱልኝ። በላዩ ኃጢአተኛን ሹም፤ ሰይጣንም በቀኙ ይቁም። በተምዋገተም ጊዜ ተረትቶ ይውጣ፤ ጸሎቱም ኃጢአት ትሁንበት። ዘመኖቹም ጥቂት ይሁኑ፤ ሹመቱንም ሌላ ይውሰድ። ልጆቹም ድሀ አደግ ይሁኑ፥ ሚስቱም መበለት ትሁን። ልጆቹም ተናውጠው ይቅበዝበዙ ይለምኑም፥ ከስፍራቸውም ይባረሩ። ባለዕዳም ያለውን ሁሉ ይበርብረው፥ እንግዶችም ድካሙን ሁሉ ይበዝብዙት። የሚያግዘውንም አያግኝ፤ ለድሀ አደግ ልጆቹም የሚራራ አይኑር። ልጆቹ ይጥፉ፤ በአንድ ትውልድ ስሙ ይደምሰስ። የአባቶቹ ኃጢአት በእግዚአብሔር ፊት ትታሰብ፤ የእናቱም ኃጢአት አትደምሰስ። በእግዚአብሔር ፊት ሁልጊዜ ይኑሩ፤ መታሰቢያቸው ከምድር ይጥፋ” /መዝ 109 ፤ 2 - 15/።

ይህ ከላይ የምታዩአቸው ሥዕላት ጨረቃ ላይ በማረፍ በዐለም ቀዳሚ የሆኑት የሩሲያ አስትሮኖመሮች (ሳይንቲስቶች) ሕዋ ላይ ይዘዋቸው የወጧቸውን ሥዕላት እዚያው ሕዋ ውስጥ ሆነው ነው። በነገራችን ላይ በዓለም የሕዋ የምርምር ጣቢያው ውስጥ ትልልቅ የሕዋ ምርምር ጣቢያ የገነቡት ሩሲያ እና አሜሪካ ቢሆኑም ለሁሉም የምርምር ጣቢያዎች ልብ ሆኖ የሚያገለግለው ግን የሩሲያው የምርምር ጣቢያ ነው። ይህም ማለት ሩሲያ ራሷን ከስምምነቱ ብታገልል እና ብትወጣ የአሜሪካን ጨምሮ የሌሎቹ የምርመር ጣቢያዎች የሩሲያ ጣቢያ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች የሚተካ ሥራ እስከሚሠሩ ድረስ ከሕዋ መውረድ ግዴታቸው ይሆናል ማለት ነው። ይህ የቆመው ደግሞ እንደምታዩት የእመቤታችንን እና የሌሎች ቅዱሳን ሥዕላት በያዙ ተመራማሪዎች ነው። በርግጥም ለሥዕሏ የማይሰግድ ወደ ኦርቶዶክስ ከመጣ የእርሱ ቦታው አይደለምና ከቆመበት ቦታ ይጥፋ። በረከቷ ይደርብን፤ አሜን።

(~መምሕር ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ~)

https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
1.2K views✞£iŧsûm✞, edited  18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-30 21:35:15
1.1K views✞£iŧsûm✞, 18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-29 18:50:21 አስተርአያ ገብርኤል

ስለ ወንድሜ አዲሱ ዝማሬ የተወሰነ ።

በሰባኪነቱ በመላእክት ዓለም የሚታወቀው የአምላክን ሰው መሆን የስጋዌውን የተዋህዶን የቤተክርስቲያንን ከጥላ ወደ አካልነት ከሰባኪዎች ሁሉ አስቀድሞ የሰበከው መላኩ ቅዱስ ገብርኤል እመቤታችን በቤተ መቅደስ ሳለች የብስራቱን ዜና መናገሩን ሊቁ ቅዱስ ያሬድ እንዲህ ይቃኛል ።

*ወእንዘ ትፈተል ወርቀ ወሜላተ
አስተርአያ ገብርኤል ለማርያም*

የመዝሙሩ የመጀመርያ የወረቡ መነሻው የዜማውም ግጥም ይህ ነው ።

የመዝሙሩ ግጥሞች የሰው ልጆችን አምላክ በስጋ ማርያም ተገልጦ ማዳኑን ከእመቤታችን በመላኩ የመበሰር ዜና ይጀምራል ።

አዝ *2* ሁለቱ ሐረጎች

"ያንን ታላቁን ዜና ለድንግል ያበሰረ
የዓለሙን መድኃኒት መወለድ የነገረ..."

መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እመቤታችንን አምላክን የመፅነሷን ዜና የነገራት ሶስት ጊዜ ነው በቤተ መቅደስ ዙርያ ከተሰበሰቡ ደናግለ እስራኤል ሐርና ወርቅ እያስማማች እየፈተለች ሳለ አምላኳን እንደምት ፀንሰው መልአኩ ከመንገሩ በፈት ሁለቴ ተገልጦ ነግሯት ነበር የመጀመርያው ውሃ ልትቀዳ በውሃ ምንጭ አጠገብ ሳለች ነበር ።

እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እናት ላልነበራቸው ለዮሴፍ ልጆች እናት ልትሆናቸው ውኃ ልትቀዳላቸው ሄደች ምክንያቱም ለዮሴፍ የታጨችበት አንዱም ምክንያት ይህ ስለነበር ። የሙት ልጅ ሆኖ ውሃ ሚቀዳለት አጥቶ ለዘመናት ሲጠማ ለኖረው የሰው ልጅ "የሙት ልጅ ትሆኑ ዘንድ አልተዋቹም ያለው አምላክ " በሞተችው እናታችን በቀዳማዊት ሔዋን ፈንታ ዳግሚት ሔዋንን ዳግማዊው አዳም ክርስቶስ በመስቀል ስር ለሁሉ እናት ትሆን ዘንድ እስኪ ሰጠን ድረስ ለዮሴፍ ልጆች እናት ሆና ውሃ እድትቀዳ አደረጋት ። አብዛኞቹ የቀደሙት እናቶች የታጩትም በውሃ አጠገብ ነው ሲፓራ እርብቃ እንደ እናቶቿ አሷንም በውሃ አጠገብ አጫት ። ፀጋን የሞላብሽ ሆይ እያለ ሲያመስግናት መልአኩ ገብርኤል አምና አልተቀበለችም ነበር ድንግል ማርያም ። (ሕይወተ ማርያም ሊቀ ሊቃውንት ስማ ኮነ መላአክ)

ምክንያቱም ቅዱሳት መጻሕፍት በቤተ መቅደስ እያየች ስላደገች ቀድሞ ሔዋንን በከንቱ ውዳሴ ያሳታት ሴጣን ይሆንን ብላ ። ይህን ቅዱሳት መጻሕፍትን ማወቋን ሊቁ ቅዱስ አብሮስ እንዲህ ይላል ። "ብዙ መጻሕፍት ፣ ብዙ ነቢያት ፣ ብዙ መላእክት ከእርስዋ ጋር ሆነው እንደምን ለብቻዋ ትሆናለች? በሕልምዋ ሳይቀር ቅዱሳት መጻሕፍትን ትሰማ ነበር" ይላል። (የብርሃን እናት ዲያቆን ሔኖክ ሐይሌ)

ለሁለተኛ ጊዜ የተገለጠላት ደግሞ ወደ ዮሴፍ ቤት ሄዳ ውሃ የያዘችበትን ማሰሮ ስታወርድ ቃሉን ደገመላት ትፀንሻለሽ ባላትም ጊዜ ቃሉን ባለመለወጡ ይህስ የእግዚአብሔር መላአክ ቢሆን ነው እንጂ ቃሉን ይለውጥ ነበር ብላ በቤተመቅደስ ሆና ቃሉን ልትሰማ ሔደች ። ይህን ሶስተኛውን ዜና መንገሩን ነው ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ሐርና ወርቅ ስትፈትል ቅዱስ ገብርኤል ተገለጠላት ያለው ። የቤተክርቲያናችን ሊቃውንት ሲተረጉሙ ወርቅ የመለኮት ሐር የትብስዕት ምሳሌ ብለው ያስተምራሉ ። መልአኩም ቅዱስ ገብርኤል ትርጉምም ሰው እና እግዚአብሔር ማለት ነው በዚህም ምክንያት ነው እመቤታችንን ሊያበስር የተላከው ። በሁሉ ዘንድ ጌታ የሆነ አብርሃም ለይስሐቅ ሚስት በፈለገ ጊዜ ወደድሃይቱ ርብቃ መልእክተኛ እያውብርን ልኮ ነበር ። ርብቃ ቤት ኢያውብር መላኩ ቅዱስ ገብርኤል የእመቤታችን ቤት መላኩ ። ርብቃም ምንም እንኳን ባይስማሙ የሁለቱ ሕዝብ መገኛናት እመቤታችንም የሁለቱ የኅሕብ እና የአሕዛብ መገኛ ናት ። ልጇም ሕዝብና አሕዛብን ሊያድን ነውና የመጣው። " አብርሃም የእግዚአብሔር አብ ኢያውብር ፡ የቅዱስ ገብርኤል ይስሐቅ የመለኮት ፡ ርብቃ ፡ የትብስእት" ፡ (የሉቃስ ወንጌል እንድምታ ትርጓሜውም)
ወርቅ የወንጌል ሐር የብሉይ በመሆኑ እመቤታችን ሐርና ወርቅን ስታስማማ አለ ። ድንግል ማርያም የብሉይ ኪዳን ፍፃሜ የሐዲስ ኪዳን የወንጌል መግቢያ በር መግቢያ መሆናን መንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ተናግሯል ብለው ተርጉመውታል ።

በመጨራሻም ወንድሜ ፀጋውን ያብዛልህ ለኔም ስላረገልኝ "የጪጩ ገብርኤል " ለኔም ያደረገው ብዙ ነው በዝማሬ እላለሁ ።

( ~ ዲያቆን ፍፁም ከበደ ~)

https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
1.0K views✞£iŧsûm✞, edited  15:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-29 18:50:09
955 views✞£iŧsûm✞, 15:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-29 11:40:49 የማንንን ስብከት ፈልገው አጥተዋል ሁሉንም በአንድ ቻናል ይዘንላችሁ መጥተናል ከ15ሽ በላይ ተከታይ ያለው ቻናል ከፍተናል።

የመምህር ምህረተአብ አሰፋ ስብከት

የዲያቆን ሔኖክ ኃይሌን ስብከት

የመጋቤ ብሉይ ወሐዲስ አባ ገብረ ኪዳንን ስብከት

የቀሲስ ዶክተር ዘበነ ለማን ስብከት

የመጋቤ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ ትምህርቶች

የዲያቆን ዳንኤል ክብረትን እይታ

የሊቀ ሊቃውን ዕዝራ ሐዲስ ስብከት

ቻናሉን ለመቀላቀል ሰማያዊውን ይጫኑ

@Orthodox_Sibket
@Orthodox_Sibket
@Orthodox_Sibket
264 viewsዲያቆን አቤንዔዘር ሙሉ, 08:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-29 11:22:37
ከ60 second በኋላ ሰለሚጠፋ አሁኑኑ JOIN በማድረግ ተቀላቀሉ በቴሌግራም ምርጥ ከተባሉ ኦርቶዶክሳዊ የPDF መጽሐፎች መገኛ ቻናል ውስጥ አንዱ ነው በእርግጠኝነት ይወዱታል። ይቀላቀሉን
173 viewsዲያቆን አቤንዔዘር ሙሉ, 08:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-29 09:05:21
ጉባኤ ቴኦቶኮስ

በአዶላ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ከ21 እስከ 24 ቀን ድረስ የሚቆይ ወርኃዊ ጉባኤ ተዘጋጅቷል
እርሶም በጉባኤው በመገኘት ከወንጌሉ ድግስ ከዝማሬው ወይን እንድትበሉና እንድትጠጡ መንፈሳዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን!

ጉባኤ ቴኦቶኮስ!!! ተናፋቂዋ ጉባኤ
636 viewsወሰንየለው ባህሩ, 06:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-28 17:51:07 † አንድ መልአክ በአንድ ጊዜ ሁሉም ቦታ እንዴት ይገኛል?

" እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆም ገብርኤል ነኝ።"

" I am Gabriel l stand in the presence of God " ሉቃ 1፥19

★ ሼር በማድረግ ሰዎች እንዲማሩበት አድርጉ ★

አንዳንድ ሰዎች አንድ መልአክ በአንድ ጊዜ ሁሉም ቦታ መገኘት እንዴት ይችላል? ይህ የፈጣሪን ሥልጣን መጋፋት ነው ይላሉ።ተሳስተዋል።ረቂቁን የመላዕክት ተፈጥሮና ከአዕምሮ በላይ የሆነውን የረቂቁን መንፈሳዊ ዓለም አሠራር በሥጋዊ ውስን አዕምሮ መገደብና በውስን ተፈጥሯዊ የማሰብ ብቃታችን ረቂቁን የመላዕክት ባሕርይና የመንፈሳዊው ዓለም አሰራርን መርምሮ ለመድረስ መሞከር ፍጹም ሞኝነት ነው።

አንድ ነገር በጣም ልናስተውል ይገባል መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለካህኑ ዘካርያስ በተገለጠለት ጊዜ " እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆም ገብርኤል ነኝ" ብሎታል ይህንን ቃል መልአኩ ለምን ተናገረው ብንል ስለ ሁለት ነገር ነው አንደኛው ሚስትህ ኤልሳቤጥ ትጸንሳለች ወንድ ልጅ ትወልዳለች ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ ሲለው ዘካርያስ ለመልአኩ ሚስቴ እርጅታለች እንዴት ሊሆን ይችላል ባለ ጊዜ " እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆም ገብርኤል ነኝ።"አለ "መቆም" ማለት መማለድ መለመን ማለት ነው።በተለያየ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል መቆም መማለድ እንደሆነ ተገልጿል።" የተመረጠ ሙሴ በመቅሰፍት ጊዜ በእግዚአብሔር ፊት ባይቆም ኖሮ እስራኤልን ያጠፋቸው ዘንድ ተናገረ።" ተብሎ ተጽፏል መዝ 105፥ 23 ።ስለ ቅዱስ ገብርኤል ስለ አንተና ባለቤት በእግዚአብሔር ፊት ለምኜ፣ማልጄ ነበር ማለቱ ነው።

ሁለተኛ በእግዚአብሔር ፊት የምቆም ገብርኤል ነኝ ማለቱ እግዚአብሔር ባለበት ቦታ ሁሉ መላዕክቱም አሉ የእግዚአብሔር ፊት ወዴት ነው ? ብንል እግዚአብሔር ረቂቅ ስለሆነ በሁሉም ቦታ ሁሉ አለ ስለዚህ እግዚአብሔር ባለበት ቦታ ሁሉ ቅዱሳን መላዕክቱ አሉ።ይህም እንደ እርሱ አምላክ የሚያሰኛቸው ሳይሆን በመለኮት ሥልጣን፣ከእግዚአብሔር በተሰጣቸው መንፈሳዊ ረቂቅ ጸጋ እርሱ ባለበት ቦታ ሁሉ እነርሱም አሉ።

‹‹የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙርያ ይሠፍራል፤ ያድናቸውማል›› (መዝ. 33፥7)

የሚገርመው ግን እግዚአብሔርን ለማይፈሩ፣በኃጢአትና በበደል ለሚመላለሱ ሰዎች ግን እንኳን በአንድ ጊዜ ለሁሉም ባሉበት ቦታ ሊደርስ ሁሉም ሰዎች ተሰብስበው መልአኩ ወዳለበት ቢመጡ እንኳ አይረዳቸውም።

የእንግሊዘኛውን ቨርዥን ብንመለከተው በደንብ ግልጽ ያደርገዋል "l am Gabriel l stand in the presence of God" ይህም ማለት እግዚአብሔር ባለበት ቦታ ሁሉ መልአኩም አለ።እግዚአብሔር ረቂቅ አምላክ ነው እነርሱም ረቂቃን ናቸውና እርሱ ባለበት ሁሉ እነርሱም አሉ።

ስለዚህ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሥርዓቷ ሁሉ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ስለሆነ አልተሳሳተችም።በአንድ ቀን በተለያየ ሃገርና ቦታ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልን ስናከብር የእግዚአብሔርን ክብር እያወጅን ስለሆነ በሁሉም ቦታ እግዚአብሔርም መልአኩም በክብር ነበሩ።

አንድ ቅዱስ መልአክ ክብሩ ከፀሐይ ክብር ይበልጣል እንጂ አያንስም አንዲቷ ፀሐይ በአንድ ጊዜ የተለያየ ቦታና የተለያየ ሀገር የመድረስ ተፈጥሯዊ ፀጋ አላት የእግዚአብሔር መልአክ ደግሞ ከፀሐይ በላይ ሥልጣን ስላለው በአንድ ጊዜ ሁሉም ጋር መገኘት ይችላል።ይህ ማለት የእግዚአብሔርን ሥልጣን መጋፋት ሳይሆን እግዚአብሔር ባለበት ቦታ ሁሉ መልአኩም እንደሚገኝ ማስረገጥ ነው። "በእግዚአብሔር ፊት የምቆም ነኝ" ያለውም እግዚአብሔር ባለበት ቦታ ሁሉ መልአኩም እንደሚኖር ማረጋገጫ ነው።እግዚአብሔር ደግሞ የሌለበት ቦታ የለም።

" ታላቅ ስልጣን ያለው ሌላ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፥ ከክብሩም የተነሣ ምድር በራች።"
(የዮሐንስ ራእይ 18:1)

ከነፋስ ይልቅ ነፍስ ትረቃለች፤ ከነፍስ ይልቅ ደግሞ መላእክት ይረቃሉ፤ ከመላእክት ደግሞ ሥላሴ ይረቃል ።በውስን አዕምሯችን ረቂቃኑን ለመገደብ አንሞክር።ከአዕምሮ በላይ የሆነብንን ነገር ዕፁብ ድንቅ ብለን ማለፍ ክርስቲያናዊ ጠባይ ነው።

በምድራዊ ቴክኖሎጂ እንኳ ብንመለከት አንድ የኮምፒውተር ሰርቨር በተለያዩ ሀገር ያሉ በሚሊየን የሚቆጠሩ ኮሚፒውተሮችን በተመሳሳይ ሰዓትና ደቂቃ የሰከንድ ልዩነት ሳይኖር መረጃ ይሰጣል መረጃም ይቀበላል።ሰው የፈጠረው ሰርቨር በአንድ ጊዜ ሁሉም ጋር መሥራት ከቻለ እግዚአብሔር የፈጠረው አንድ ቅዱስ መልአክማ ከሰዎች የእጅ ሥራ ውጤት በሰባት እጥፍ እንደሚበልጥና አንዱ ለሁሉ መድረስ እንደሚችል በእምነት ልንረዳ ይገባል።አሁን የምንጠቀምበትን የፌስቡክ አፕልኬሽን የሚቆጣጠረው አንድ ሰርቨር ነው።በዓለም ዙሪያ ያሉ የፌስቡክ ተጠቃሚዎችን በሙሉ የሚቆጣጠራቸው አንድ ሰርቨር ነው።የሰው ልጅ የእጁ ሥራ ዓለምን እንዲ መቆጣጠርና በአንድ ጊዜ ለሚሊየኖች ተደራሽ መሆን ከቻለ አንድ ቅዱስ መልአክ ከዚህ በላይ ሊሰራ እንደሚችል መንፈሳዊ አዕምሮ ያለው ሰው በቀላሉ የሚረዳው ሐቅ ነው።

ቅዱስ ገብርኤል አንድ ሲሆን ከእግዚአብሔር በተሰጠው ፀጋና ሥልጣን በዓለም ዙሪያ ላሉ ሰዎች ሁሉ ከዓይን ጥቅሻ ባነሰ ፍጥነት ደርሶ ይራዳል።

የመልአኩ ፈጣን ተራዳኢነት ከሁላችን ጋር ይሁን።

መ/ር ታሪኩ አበራ

እባካችሁ ለሌሎችም ሼር አድርጉት

https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
2.3K views✞£iŧsûm✞, 14:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ