Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxamero — ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
የሰርጥ አድራሻ: @orthodoxamero
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 44.89K
የሰርጥ መግለጫ

ዲያቆን ፍፁም ከበደ
ሀሳብ ካሎዎት @Fisumkeb
facebook Link...
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.kebede

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-06-03 10:38:04
የአቡዳቢ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም መቃኞ ቤተ ክርስቲያን በዛሬው ዕለት ግንቦት 26 ቀን 2015 ዓ.ም ተመረቀ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች 19 ያህል አብያተ ክርስቲያናት ሲኖሯት የግንባታ ቦታ አግኝታ በራሷ ስትገለገል ይህ የመጀመሪያዋ ነው ።

በሥነ ሥርዓቱ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፤ብፁዕ አቡነ ድሜጥሮስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅድስት ሥላሴ ዮኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ፣የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት እና ምእመናን በተገኙበት ተከብሯል፡፡

https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
3.1K views£itsum, 07:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-01 17:55:57
ቅዱስነታቸው ዱባይ በሰላም ገብተዋል።
**
ግን
ቦት ፳፬ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም
""""""""""""""""""""""""""""
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ዱባይ በሰላም ገብተዋል። ዱባይ አየር መንገድ ሲደርሱ በዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ የኢትዮጵያ አምባሳደር የሆኑት አምባሳደር ዑመር ሁሴን፣የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዲሜጥሮስ፣የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎችና በዱባይ የሚገኙ ምዕመናን ተወካዮች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ቅዱስ ፓትርያርኩ ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ጋር ለሐዋርያዊ አገልግሎት ዛሬ ማለዳ ወደ ዱባይ መጓዛቸውን
መዘገባችን ይታወሳል።


https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
3.5K views£itsum, 14:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 22:55:29 "ወደ ገሊላ ይቀድማችኋል" ማቴ 28፥7
   
ጌታችን ሞትን ድል አድርጎ ከተነሣ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ ብዙ እና ጥቂት ሆነው ሳለ በተለያየ ጊዜ ራሱን ገልጦ አሳይቷቸዋል። አሁን ደግሞ አስቀድሞ በሴቶች በኩል "ወደ ገሊላ ይቀድማችኋል" ብሎ ያስነገረውን ትንቢት ሊፈጽም፣ ዓሣ ለማጥመድ ወደ ገሊላ ባሕር ለወረዱ ለጴጥሮስና ለስድስቱ ወንድሞቹ የተገለጠበትን ሦስተኛ ታሪክ ዮሐንስ ይጽፍልናል።(ዮሐ 21፥1)

ቅዱስ ጴጥሮስ "ሰላም ለእናንተ ይሁን" የሚለውን የትንሣኤውን ጌታ ድምጽ ከሰማ ፣ የተጠራጠረው ቶማስ እጁን በጎኖቹ አግብቶ "ጌታዬ አምላኬ" ብሎ ሲያምን ከተመለከተ በኋላ "ዓሣ ላጠምድ እሄዳለሁ" ብሎ ሲናገር እናገኘዋለን።(ዮሐ 21፥3) ክርስቶስ ተላልፎ በተሰጠበት በሐሙስ ምሽት ከእሳት ዳር ተቀምጦ ያደረገውን ሊረሳውና ራሱን ይቅር ሊል ስላልቻለ፣ ጌታው ቀድሞ የሰጠውን የወንጌል መረብ ተወና የዓሣውን መረብ ጨብጦ ወደ ገሊላ ባሕር ሮጠ።(ማቴ 4፥19) በኃጢአት ምክንያት የተሰማው ኃፍረትና መሸማቀቅ ሐዋርያነቱን ትቶ በድሮ ማንነቱ ውስጥ ራሱን እንዲደብቅ አደረገው። የካደን ማን ለምስክርነት ይፈልገዋል በሚል ዓይነት ስሜት ለወንድሞቹ  "ዓሣ ላጠምድ እሄዳለሁ" አላቸው።

ደስ የሚለው ነገር ግን ይህን አስቀድሞ የሚያውቅ ይቅር ባይ አምላኩ ጴጥሮስን "በገሊላ ቀድሞት ነበር"። በበደሉ ተሸማቆ የተወውን ሐዋርያነት ሥልጣን በፍቅሩ መማለጃነት መልሶ ሊሰጠው፣ አይገባኝም ብሎ ያስቀመጠውን የወንጌል መረብ ዳግመኛ ሊያሲዘው በገሊላ ባሕር ዳር ቀደመው። እኛም አንድ ኃጢአት ይኖረናል። መርሳት ያልቻልነው፣ ንስሐ እንኳን ብንገባበት ራሳችንን ይቅር ለማለት የተቸገርንበት፣ "ከዚህ በኋላማ..." እያሰኘ የድሮ መረብ አስይዞ ወደ ገሊላ የሚመልስ አንድ በደል ይኖረናል። ነገር ግን ጌታ ለቅዱስ ጴጥሮስ እንዳደረገው ለእኛም እንዲሁ ያደርጋል። ከባሕሩ ዳር ይጠብቀናል፣ "ትወደኛለህ" ብሎ ይጠይቀናል፣ ከዚያ በማይለወጥ ፍቅሩ ወልውሎ ሰንግሎ አፍረን ወደ ሸሸነው መንፈሳዊነት ይመልሰናል።

+++ ጌታችን በገሊላ ይቀድመናል! +++

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
911 views£itsum, 19:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-15 20:29:06 ጥፋቱ የማን ነው?

(መምህር ገብረ መድኅን እንደጻፉት
ከየንታ ገብረ መድኅን)



ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የጠራ ትምህርት የታወቀ ሥራዓት ያላት በምድር ያለች ሰማያዊት ዓለም ናት።
ዘመን በወለደው ንጉሥ በወደደው መሄድ አትችልም፦ከአባቶቿ በተቀበለችው እውነት ጸንታ ትኖራለች እንጂ።

የማይናወጽ ዶግማ ፣ዶግማዊ ቀኖና፣ይትበሀል ሥርዓት፣ቅዱስ ትውፊት ያላት እንደመሆኗ መጠን ተመቸኝ ብለን የምንለውጠው አይደለም። ይልቁንም ፦ከትናንት ተቀብለን የምንጠብቀው ለመጻኢው ትውልድም የምናስረክበው ነው እንጂ።

ሐዋርያት የሠሩትን ሠለስቱ ምእት የወሰኑትን አፍርሼ የአበውን ሃይማኖት ይጃለሁ ማለት አይቻልሞ።
ምን አልባት እግዚአብሔር በቸርነቱ ከቅዱሳኑ ማኅበር ቢያደርሰን አባቶቻችንም ለምን የሠራነውን አፈረሻችሁ ብለው ቢጠይቁን መልስ እናገኝ ይሆን? ልጆቻቸው እኛ በስንፍናችን ማፈር አንፈልግም።

ቤተ ክርስቲያን ርትዕት የምትባለውም ባልተቋረጠ ርቱዕ ቅብብሎሽ የመጣች ሐዋርያዊት ስለሆነች ነው።
የሐዲስ ኪዳን ነቅዕ ተቀባዮች ሐዋርያት እና ሐዋርያትን የመሰሉ አበው በውግዘት የሠሩትን ሥርዓት ማስጠበቅ ካንድ ኦርቶዶክሳዊ ሰው የግድ የሚጠበቅ ነው።

ቅዱስ ሲኖዶስም ይሄንን
የመቀበል፣የመጠበቅ፣ለሚመጣው ቅዱስ ጉባኤ የማስረከብ ሀለፊነት አለበት።ይሄንን የሚጋፋ ሲመጣም በጥብዓት አርዓያ በመሆን ምሥክርነትን ሊቀበል ይገባዋል።
አማኞችም ከላይ ከቅዱሳን የወረደውን ፦መቀበል፣መጠበቅ፣መስጠት ይኖርባቸዋል።የጉባኤው አካል ናቸውና በኦርቶዶክሳዊ ሐዋርያዊ ቅብብሎስ ቀኖና የማያገባቸው ምእመናን የሉም።

አንሳሳትም እኛን ብቻ ስሙን የሚባል ከሆነ ስፍር ቁጥር የሌለው ይሄ ሁሉ ስህተት ከየት መጣ?
ያለግዘት በተሠሩ ቀኖናዎች ላይ ግን ቅዱስ ሲኖዶስ የመቀበል ብቻ ሳይሆን የማሻሻልም ሥልጣንም አለው ይሄ ማለትም ሐዋርያት ይለይ ይወገዝ ብለው የሠሩትን ያሻሽላል ማለት አይደለም።

በዚህ ዓመት የገጠመን ግን ሐዋርያት እና ሦስቱ ዓለም አቀፍ ጉባኤ አውግዞ የሰጠንን አትቀበሉ የተባልነውን ከሐዋርያት ይልቅ ጠቅላዩ ያሉት ይበልጣልና ይሁን ተቀበሉ የሚል ስለሆነ በተቃውሞ ላይ እንገኛለን።

በራሳቸው ተሹመናል ብለው ከነበሩት አንድ ሰው እንኳን ወደዚህ ቅዱስ ጉባኤ መግባት አይችልም። ቢገባ ግን ከሐዋርያት እና ከቅዱሳን ሊቃውንት አባቶቻችን ጉባኤ መለየታችን እንደሆነ መታወቅ አለበት።

ዘመን ተመችቶናል በማለት ሞትም ሕይወትም እጃችን ላይ ነው ፣እረፉ በማለት በማስፈራራት ዝም በሉ የሚሉን ግን ፦ለእናንተው ይብሳል እንጂ ለእኛ የአባቶቻችን ውጉዝ ቀኖና ፈርሶ ከምናይ ሰማዕትነትን በናፍቆት እንጠብቃለን።

ይሄንን ነውር ካልተቃወምን ምኑን መምህር ሆንነው? ምኑንስ አስተማርነው?
ቤተ ክርስቲያን እንዲህ ተዋርዳ ከማየት ሺህ ጊዜ መሞት ሺህ ጊዜ መታሠር ይሻለናል።
መምህሬ ኃይለ ማርያም የታሠሩትም ይሄንን ስላሉ ነው

#ለመሆኑ ጥፋቱ ማን ነው?
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.keb
2.0K views£itsum, edited  17:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-15 10:34:07 የቤተክርስቲያን ምሰሶ፣የኦርቶዶክሳዊነት አባት

የኦርቶዶክሳዊነት ጠበቃ ይሉታል ሊቃውንት፣በሕይወት ዘመኑ ሁሉ የተገለጠውን እውነት ለመጠበቅ ሲጋደል የኖረ እጅግ ጠንካራ የቤተክርስቲያን እና የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ታላቅ ጠበቃ ነውና፡፡ቤተክርስቲያን ስትጠራው የቤተ ክርስቲያን ሐኪም (Doctor of the Church)፤ የኦርቶዶክሳዊነትአባት(Father of Orthodoxy)፣ሐዋርያዊው፤ የሕይወት ምንጭ" ትለዋለች:: በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ከሐዋርያት ቀጥሎ የእርሱን ያህል ስለ አንዲቷ ፍጽምት ሃይማኖት የተዋጋ እና የተጋደለ ቅዱስ ፈልጎ ማግኘት ይከብዳል።ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ።

ቤተ ክርስቲያን ከግማሽ ምዕተ ዓመት ለሚበልጥ ዘመን ከአርዮሳውያን ጋር ላደረገችው እልህ አስጨራሽ ትግል መለያ ግርማና ወካይ መገለጫው ቅዱስ አትናቴዎስ ነው፡፡ ዘመን ገጠሙ የነበረው ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናንዙ የቅዱስ አትናቴዎስን ተጋድሎ በተመለከተ ሲናገር‹‹ አትናቴዎስን ሳመሰግን የማመሰግነው የመልካም ተጋድሎ ሕይወትን ነው፤ ስለ እርሱ መናገርና ስለ መልካም ተጋድሎ ሕይወት መናገር አንድ ናቸውና፣ ምክንያቱም እርሱ የመልካም ተጋድሎ ሕይወትን በምልዓት ገንዘብ አድርጓልና ›› ያለው ለዚህ ነበር፡፡

ቅዱስ አትናቴዎስ በዘመኑ ሁሉ በቤተ ክርስቲያን የተቃጣዉን ሃይማኖታዊና ፖለቲካዊ ዘመቻ ሲዋጋ የኖረ ታላቅ የቤተ ክርስቲያን አርበኛ ነዉ፡፡ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናንዙ አትናቴዎስን ‹‹ የቤተክርስቲያን ምሶሶ›› ይለዋል፡፡ አትናቴዎስ ሃይማኖተኛ፤ ጀግና፤ ዘዴኛ፤ ታላቅ የትህትና አባት እና የሚያስደሰት ጥበብን አሟልቶ የያዘ ታላቅ አባት ነው፡፡

በዚያ ዘመን የነበረዉ በቅዱስ በአትናቴዎስና በ አርዮሳውያን መካከል የተካሄደዉን እልህ አስጨራሽ ተጋድሎ ‹‹አትናቴዎስ ከዓለሙ ጋር፤ ዓለሙም በአትናቴዎስ ላይ›› "Athanasius against the world." ሲሉ ይገልጹታል፡፡ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊው ስለ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ብዙ ተጋድሎ: ብዙ ስቃይንም ተቀብሎ ግንቦት 7 ቀን በ373 ዓ/ም አካባቢ አርፏል::

አትናቴዎሳዊነትና አትናቴዎስ ለቤተክርስቲያን በብርቱ የሚያስፈልጉበት ጊዜ እና ዘመን ላይ ነን።ለእውነት በጥብአት እስከሞት በኦርቶዶክሳዊ ፍኖት ለኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖት መጋደልና መቆም።ይህንን ለማድረግ ቤተክርስቲያንን እና ትምህርቷን በሚገባ ማወቅ፣መረዳትና መኖር ይጠይቃል።ኦርቶዶክሳዊ እቅበተ እምነት በስሜት የሚፈጸም ሳይሆን የቤተክርስቲያንን ትምህርት ከመጠንቀቅ ባሻገር ልክ እንደ ቅዱስ አትናቴዎስ የዘመኑን ፍልስፍ፣ፖለቲካና እና መልስ የሚሰጡበትን የክህደት ትምህርትና ፍልስፍናም በትክክል መረዳት ይፈልጋልና።

ምንጭ

ዲ/ን ያረጋል አበጋዝ(2000) ቅዱስ አትናቴዎስ ሕይወቱና ትምህርቱ

በረከቱ ለቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ትሄሉ ምስሌነ።አሜን!
2.0K views£itsum, 07:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-15 10:34:05
1.6K views£itsum, 07:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-14 15:44:30 ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው።

"ራስህን በእውነት አስጊጥ፣ በሁሉም ጉዳይ እውነትን ብቻ ለመናገር ሞክር፣ የሚጠይቅህ ማንም ይሁን ማን ለሐሰት ድጋፍ እትስጥ። አንተ እውነቱን በመናገርህ የሚናደድብህ ሰው ቢኖር እንዳትዝን፤ ይልቁንም "ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና /ማቴ 5፥ 10/ በሚለው የጌታህ ቃል ራስህን አጽናና ። /ቅዱስ ገናዲየስ ዘቁስጥንጥንያ /

መምህር ኃይለ ማርያም የታፈኑት እውነት በመናገራቸው ነው።
መምህር ኃይለ ማርያም የታፈሩት ክህነት መነገጃ ለሚያደርጉት አይሰጥ በማለታቸው ነው።
መምህር ኃይለ ማርያም የታፈኑት ቤተ ክርስቲያንን ቤተ ክርስቲያን ከሚያሰኙት ዋናው ሥርዓተ ክህነት በቀኖና ቤተ ክርስቲያን ይፈጸም በማለታቸው ነው።
መምህር ኃይለ ማርያም የታፈኑት በመምህር አምላክ ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት ይዘግይ በማለታቸው ነው።

መምህር ኃይለ ማርያም ሥራቸውን ከመሥራት ኃላፊነታቸውን ከመወጣት፣ ቃለ እግዚአብሔር ከማስተማር እና ለቤተ ክርስቲያን ጥብቅና ከመቆም ውጭ ወንጀል የሚፈጽሙ ሰው አይደሉም።

ስለዚህ ያሳፈኗቸው አሁኑኑ ጵጵስናን በጫና ማሰጠት የሚፈልጉ፣ እውነት ስትነገር የሚደነብሩ፣ ክህነትን ለፖለቲካ እና ለጥቅም መነገጃ ማድረግ የሚፈልጉ እና ይህም እንዲፈጸም የጥቅም ትስስር ባላቸው አካላት ጥቆማ መሆኑን ለመረዳት አያስቸግርም።

እንኳን በዚህ ዘመን እና በእኛ ሀገር ይቅር እና በየትኛውም ዘመን እና ሁኔታ የተፈጸመ ድብቅ ምክር እና ተንኮል ሁሉ መገለጡ አይቀርም። የማይገለጥ የተከደነ፣ የማይታወቅ የተሠወረ የለም ተብሏልና። ስለዚህ መምህሩን ፍቷቸው። እውነትንም አጥብቃችሁ አታሳድዷት። ሐሰትንና ተንኮልንም አታክብሯት። በኋላ ለፍርድ አሳልፈው ይሰጧችኋልና።


(ብርሃኑ አድማስ)

https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.keb
2.2K views£itsum, edited  12:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-14 15:44:21
1.9K views£itsum, 12:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-13 21:09:13
የቅድስት ድንግል ማርያም የፀሎት ፕሮግራም ላይ በሺዎች የሚቆጠሩ የካቶሊክ እምነት ተከታዮች ተገኝቷል አውሮፓ ፖርቹጋል!!

ፋጢማ እመቤታችን
OUR LADY OF FÁTIMA

https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.keb
2.4K views£itsum, 18:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-13 14:51:22
ሰበር

የታላቁ ቦሩ ሜዳ ጉባኤ ቤት የሐዲስ ኪዳን መምህር በመሆን በርካታ ሊቃውንትን ያፈሩት መምህር ኃ/ማርያም ዘውዱ ባሕር ዳር ከተማ በጸጥታ ኃይሎች መወሰዳቸው ተሰማ።

መመህር ኃ/ማርያም ዘውዱ ሰሞኑን ሢመተ ጵጵስናን በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ ሕገ ቤተ ክርስቲያንን እንዲያስጠብቅ፣ ምእመናንም የተሰጣቸውን ድርሻ እንዲወጡ እድል እንዲሰጣቸው በማኅበራዊ ሚዲያ በተከታታይ በልጅነት ሲጠይቁ ከነበሩ መምህራነ ቤተ ክርስቲያን አንዱ ናቸው።

በማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥንም ከ3 ዓመት በላይ የሐዲስ ኪዳን ትርጓሜን በየሳምንቱ እያስተማሩ ይገኛሉ።



https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero

Facebook Link   follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/deaconezemarefitsume.keb
2.7K views£itsum, edited  11:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ