Get Mystery Box with random crypto!

በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ፱ ኤጲስ ቆጶሳትን መልምሎ እንዲያቀርብ የተመረጠው ኮሚቴ ሥራው | ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ

በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ፱ ኤጲስ
ቆጶሳትን መልምሎ እንዲያቀርብ የተመረጠው
ኮሚቴ ሥራውን በማከናወን ላይ ነው።
****
ሰኔ ፪ ቀን ፳፻ ፲ወ ፭ ዓ.ም
****
አዲስ
አበባ -ኢትዮጵያ
"""""""""""""""""""""
የግንቦት ፳፻ ፲፭ ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ የርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ በኦሮሚያና በደቡብ ኢትዮጵያ የሚሾሙ ፱ አባቶችን መልምሎ የሚያቀርብ ኮሚቴ ማቋቋሙ ይታወሳል።

ይህን ተከትሎ የተቋቋመው ኮሚቴ ግንቦት ፳፫ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የመጀመሪያ ስብሰባውን በተሳካ ሁኔታ ያከናወነ ሲሆን ግንቦት ፳፰ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም ባኬሔደው ስብሰባ የኮሚቴው ሰብሳቢ እንዲሆኑ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስን የመረጠ ሲሆን የኮሚቴው ጸሐፊ በመሆን እንዲያገለግሉ ደግሞ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስን በመምረጥ ሥራውን በይፋ ጀምሯል።

ኮሚቴው ምልመላውን ለማከናወን የሚያስችለውን መስፈርት በማዘጋጀት ከሐሙስ ከሰኔ ፩ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ጀምሮ ጥቆማ በማከናወን ላይ ይገኛል።

የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ዶ/ርም በአስረጂነት በኮሚቴ ውስጥ የሚሳተፉ ሲሆን ለኤጲስ ቆጶስነት የሚታጩ መነኮሳትም በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተሳትፎ በመጠቆም ላይ ናቸው።


https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero
https://t.me/OrthodoxAmero