ከአንተ ፡ ማን ቀደመ ነኝ ያልከው አንተ ፤ እርሱን ማን ገደመ ። በዚያ ፡ የህሊና ፡ ሰላም ዘር የለም ፡ የስጋ ደም ። ላይጠልቅ ፡ እንደ ወጣ ፀሐይ ፡ ፍቅር ላትጠግብ ፡ ጠጣ። ባሕር ነው ፡ ውቅያኖስ እኔነትን ውጦ ፡ ሰውነት ሲቀመስ ። !! ሰው ከመሆን በፈት ተሰርተህ ስትቆም ከአምላክ ፈት ፤ በምንነት ፡ ጠራህ? የትኛውን ጎሳ ነኝ ፡ ብለህስ ሰማህ ። ? ሰው ነው መጠሪያ አልሆንከውን ሆንኩኝ ያለከው ፡ አንተ ነህ እርያ። ሰውነት ፡ ቀለለ መልአክ መሆን ምችል ፤ ፍቃድህን ሸጥከው ለጨለማ ፡ ምስል ። ዲያቆን ፍፁም ከበደ ሰኔ 3 2015 ዓ.ም https://www.facebook.com/100035541834298/posts/974895263705192/?app=fbl 1.2K views£itsum, edited 14:35