Get Mystery Box with random crypto!

Telkhis (هذه عقيدتنا)

የቴሌግራም ቻናል አርማ telkhis — Telkhis (هذه عقيدتنا) T
የቴሌግራም ቻናል አርማ telkhis — Telkhis (هذه عقيدتنا)
የሰርጥ አድራሻ: @telkhis
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.09K
የሰርጥ መግለጫ

((( @IbnusirajBot )))

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-31 22:36:56 መስጂድ መስገድ ከፊል ግዴታ ነው ወይም የጸና ሱንና ነው ብሎ መናገር መስጂድ ማስዘጋት የሚመስላችሁ ወንድሞች ሆይ
ፓኪስታን አፍጋኒስታን፣ኢንዶኔዥያ፣ባንግላድሽ ያሉ መስጂዶች ከኛዎቹ በሺ%የተሻለ ሰጋጅ የላቸውም ወይ?
በተለያዩ ሀገራት የተበተኑ ፓኪስታኒ፣ አፍጋኒ፣ እና ባንጋሊዎችስ በጀመዓ ላይ ያላቸው ተሳትፎ እንዴት ነው?
በእነዚህ ሀገራት በጀመዓ መስገድ ሱንና እንደሆነ ነው በአደባባይ የሚነገረው። ሆኖም ግን ሱንና ነው ተብለው መማራቸው ከጀመዓ ሶላት አያግዳቸውም።

የጀመዓ ሶላትን ትሩፋት መናገር
የሰለፎችን ታሪክ በዝርዝር ማስረዳት ግዴታ ነው ብሎ ከማመን ያነሰ ቀስቃሽ ነውን?
463 views19:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 22:14:28 ለምንሰማቸው ተደጋጋሚ አዛኖች ምላሽ መስጠት ይወደዳል። ለአዛን ምላሽ የመስጠት ምንዳውን እንድናገኝ ያስችለናል። ምክንያቱም ነብዩ صلى الله عليه وسلم ሁለት አዛን አድራጊዎች ነበሯቸው። የአንደኛውን አዛን ብቻ እንድመልሱ የሌላኛውን ግን እንዲተዉት አልመከሩም ባልደረቦቻቸውን። ነገር ግን ሙአዚኑ አዛን ሲያወጣ እየተከተሉ ምላሽ መስጠቱ ግዴታ አይደለም።

T.me/telkhis
526 views19:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 07:40:59 የትኛውም ቦታ (ብቻህን ስትሰግድም ይሁን ከቤተሰብና ጓደኛ ጋር ስትሰግድ) አዛንና ኢቃማ ማለትን አትዘንጋ። ግዴታ አይደለም ቢባልን እንኳ ተወዳጅ ተግባር መሆኑ ግን አሳማኝ ነው።

መስጂድ ስትገባ ሰጋጆቹ ተበትነው ብታገኛቸውና መስጂድ መስገድ አለብኝ ብለህ ካመንክ አዛን እና ኢቃማ አድርገህ ብቻህን ስገድ። ይህ ነው በላጩ አሰጋገድ። አዛን እና ኢቃማ የማድረግን አጂር ታገኛለህ።

ኢብኑ አቢ ሸይባና ኢብኑ ሙንዚር በትክክለኛ ሰንሰለት እንደዘገቡት
አነስ رضي الله عنه መስጂድ ሲገባ ተሰግዶ ስላገኘ አዛን እንድያደርጉለት አዘዘ ከዚያም ኢቃማ አስደረገና አብረውት የነበሩትን ባልደረቦቹን አሰገዳቸውም።

(ሸይኽ አልባኒ ብቻውን በሚሰግዱ ሙስሊም ላይ ሳይቀር አዛን ግዴታ ነው ይላሉ።)

T.me/telkhis
663 views04:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 09:52:33 በቁመታቸው መካከለኛ ናቸው።
ቦርጭ የላቸውም። ቀጫጫ(ከሲታ)ም አይደሉም።
ደልደልና ሞላ ያለ ሰውነት አላቸው። ጭንቅላታቸው ሚጥጥዬ አይደለችም።
ሁሉም አካላቸው ተመጣጥኖ በልኩ በልኩ የተሰራላሸው ነብይ ናቸው ዉዱ ነብይ صلى الله عليه وسلم።

T.me/telkhis
905 views06:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 07:46:43 አዛንን በሚሰሙበት ጊዜ ምላሽ መስጠቱ ግዴታ አይደለም።
ሶሀባዎች رضي الله عنهم የጁሙዓ ቀን ሙአዚኑ አዛን በሚያደርግበት ጊዜ እርስበርሳቸው ያወሩ እንደነበረ

ዑስማንም رضي الله عنه አዛን እየተደረገ እሱ ስለአንዳንድ መረጃዎችና ስለገበያ ዋጋ ሰዎችን ይጠይቅ እንደነበረ።

ነብዩም صلى الله عليه وسلم አንድን አዛን አድራጊ ሲያደምጡ ምላሽ በመስጠት ፋንታ "አሏህ አክበር፣ አሏህ አክበር" ሲል
ይህ ሙአዚን በፊጥራ (ኢስላም ላይ መሆኑን መሰከረ) ሲሉ ሁለቱን የሸሀዳ ቃላቶች ሲያወጣ ደግሞ ከእሳት ነጻ ወጣህ ብለው ሲመልሱ እንደነበረ ተዘግቧል።
الثمر المستطاب

T.me/telkhis
794 views04:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 02:56:31 አንድን ጉዳይ አንድ ጊዜ የተመለከተ በተመለከተው ነገር ውበት ሊደነቅ ይችላል።
ሁለት ሶስት ጊዜ ደጋግሞ ሲመለከተው ግን የነገሩ ትክክለኛ ማንነት ይታወቃል። እንከኖቹና አቃቂሮቹ ብቅ ብቅ ማለት ይጀምራሉ።
መደጋገም መፍትሄ ነው።

(ثم ارجع البصر كرتين):

فيه إشارةٌ إلى أنَّ تَكرار النظر في الشيء مدعاةٌ لمعرفة دقائقه ورؤية خلله إن وجد.
و(كرتين) تثنيةٌ يراد بها التكثير مثل: لبيك وسعديك.

https://t.me/yasirhamid
755 views23:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 21:43:01 #እንድህም_አለ

የሌሊትም ይሁን የቀን የሱና ሶላቶችን በእያንዳንዱ ሁለት ረከዓ ላይ እያሰላመቱ መስገድ በጣም በላጩ እና አዘውትረን ልንተገብረው የሚገባ ነብያዊ ሱንና ነው።

ሆኖም ግን አራት ረከዓዎችን አያይዞ መስገድም ይቻላል። ወንጀለኛ አያስደርግም። ሶላቱም ውድቅ አይሆንም። ምክንያቱም ቲርሚዚይ በዘገቡትና ሸይኽ አልባኒ ሐሰን የሚል ደረጃን በሰጡት ሀዲስ ነብዩ صلى الله عليه وسلم ከዐስር ሶላት በፊት አራት ረከዓን በአንድ ላይ አያይዘው ሰግደዋል። በመካከል ላይ አተሂያቱን በመቅራት ነው የሰገዱት። ይህም ማለት የሱንናውን ሶላት ልክ እንደ ዐስር ሶላት አስመስለው ሰግደዋል ማለት ነው።

ቡኻሪና ሙስሊም በዘገቡት ሀዲስ እናታችን ዐኢሻም رضي الله عمها ስለነብዩ የሌሊት ሶላት አሰጋገድ ስትገልጽ 4 ረከዓዎች ይሰግዳሉ። ስለማማራቸውና ስለ አረዛዘማቸው አትጠይቀኝ (በጣም ዉብ ሶላቶች ናቸው።) ከዚያም ሌላ ተጨማሪ ያማሩና ረጂም ጊዜ የወሰዱን 4 ረከዓዎችን ከሰገዱ በኋላ ዊትራቸውን 3 ረከዓ ጨምረው ያጠናቅቃሉ ብላ ተናግራለች። ይህን ሀዲስ ምንም እንኳ ብዙሀኑ ምሁራኖች ዐኢሻ رضي الله عنها አራቱን በአንድ ላይ የጠቀሰችው በየአራት ረከዐዎቹ ላይ ረፍት ስለሚያደርጉ ነው በሚል ቢተረጉሙትም ሀዲሱን በቀጥታ ትርጉሙና በግልጽ መልእክቱ ስንረዳው ግን ነብያችን صلى الله عليه وسلم አራቱንም ረከዓ አያይዘው ይሰግዱ እንደነበር ጠቋሚ ነው። ይህ የሀነፊያዎችን የከፊል ሰለፎች ምርጫ ነው።

T.me/telkhis
745 views18:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 18:37:04 አላህን የወደደ በፍጹም አላህን አያምጽም የሚለው ስንኝ
تَعصي الإِلَهَ وَأَنتَ تُظهِرُ حُبَّهُ
هَذا مَحالٌ في القِياسِ بَديعُ
لَو كانَ حُبُّكَ صادِقاً لَأَطَعتَهُ
إِنَّ المُحِبَّ لِمَن يُحِبُّ مُطيعُ
የዐቂዳ እንከንን ያዘለ መልእክት አለው።

ይህም ማለት አላህን ያመጸ ሁሉ አላህን አይወድም ማለት ነው። አላህን የማይወድ ደግሞ ከእስልምና ይወጣል የሚል ግልባጭ መልእክት አለው። ይህ ደግሞ የኸዋሪጆች እምነት ነው። ከላይ ያሉት የግጥም ስንኞች እንከን እንዳለባቸው የገለጹ የዚህ ዘመን ምሁራኖች አሉ። ምሳሌ
የመካው ሙፍቲ ሙሀመድ ዑመር ባዝሙል
እንድሁም
ሸይኽ ሱለይማን ሩሀይሊይ
በርግጥ ይሄ ሲባል ይህችን ግጥም ለምንም ነገር መጠቀም አይቻልም ማለት አይደለም። ወንጀሎችን በአይነት በአይነቱ እየተዳፈሩ አላህን እንወዳለን ለሚሉ ሰዎች ይህ ድርጊታቸው አላህን ከመወውደድ ጋር አብሮ እንደማይሄድ ለማሳየት መጠቀም ይቻላል።

ወንጀልና ኢማን ወይም ወንጀልና የአላህ ዉዴታ በፍጹም አብረው አይኖሩም ለማለት በማሰብ ከሆነ ግን ይህ የኸዋሪጅነት እይታ ነው።
814 views15:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 16:59:36 በዒባዳ ላይ የቱንም ያክል ብትሳነፍ በስነምግባርህ ግን እንዳትዘቅጥ። ምናልባትም የጀነትን ከፍ ያለችዋን ደረጃ የምትጎናጸፈው በመልካም ስነምግባርህ ሊሆን ይችላል።
"ኢብኑል ቀዪም"

T.me/telkhis
768 views13:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 10:30:30 አንድ ሰው አባቱን በመካድና በመራቅ እስካልሆነ ድረስ ወደእናቱ ተጠግቶ መጠራቱ ሀራም አይሆንም።

በርካታ ሶሃባዎች በእናታቸው በኩል ይጠሩ ነበር። ነብዩም صلى الله عليه وسلم ስማችሁን አስተካክሉ ብለው አላረሟቸውም። እንዳውም እርሳቸውም በእናታቸው ስም ይጠሯቸው ነበር።
ከታች ያሉት በአባት ስም ቦታ የእናታቸውን ስም ተጠቅመው የሚጠሩ ሶሃባዎች ነበሩ።

ዐብዱላህ ቢን #ኡሚ_መክቱም
ኢብኑ #ቡሀይናህ
ሀሪስ ቢን #በርሷእ
የዕላ ቢን #ሙንያህ
رضي الله عنهم

ስለዚህ
ሙሀመድ ሰዒድ
ሙሀመድ ፋጢማ
በሁለቱም መጠራት ወይም መጥራት ሀራም አይደለም። አደቡ ግን ወደአባት መጠጋቱ ነው ይላሉ ብዙዎቹ።

T.me/telkhis
908 views07:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ